tgoop.com/Utopitecture/1366
Last Update:
የ 1961/62 ዓም የአዲስ አበባ ካርታ፡፡
በ1950ዎቹ የተጀመረው ዘመናዊው ኪነህንጻ ዘይቤ ጫፍ ነክቶ አዲስ አበባን በአንድ አስርት አመታት ሊቀይራት ችሎ ነበር፡፡
ይህ የ አስርተ አመታት ዘመን የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን፣ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት፣ ማዘጋጃ ቤት፣ ቀኃስ አውሮፕላን ማረፍያ፣ የአፍሪካ ጎዳና (ቦሌ መንገድ)፣ ቸርችል ጎዳና፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቋንቋ ተቋም እና የኬኔዲ ቤተመጻህፍት፣ የካርታ ስራ ድርጅት ህንጻ፣ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ አፓርትመንት 82 ሂልተን ጋር፣ አፓርትመንት 69 ፒያሳ፣ ኪዳኔ በየነ ህንጻ፣ ጽጌ በሻህ ህንጻ፣ ባንኮ ዲሮማ ህንጻ፣ ሻሎም ሸለማይ አፓርትመንት አትክልት ተራ፣ ሞዝቮልድ ህንጻ፣ አድቬንቲስት ቤተክርስትያን፣ የጀርመን ቤተክርስትያን፣ የመካነኢየሱስ እና ሉተራን ቤተክርስትያኖች፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ፖስታ ቤት፣ የቤቶች ባንክ (ሞርጌጅ ባንክ) በድሉ ህንጻ፣ አውራ ጎዳና ህንጻ፣ ጠማማ ፎቅ፣ ራሽያ አፓርትመንት፣ ፍላሚንጎ አፓርትመንት፣ የትምህርት ሚኒስቴር፣ የቤተ ክህነት ህንጻዎች፣ ኢትዮጵያ፣ አፍሪካ ዋቢ ሸበሌ እና ሂልተን ሆቴሎች፣ አክሱም ጺዮን ማርያም ቤተክርስትያን፣ ደብረሊባኖስ ገዳም፣ ቁልቢ ገብርኤል ቤተክርስትያን፣ ስላሴ ካቴድራል መስፋፋት እና እድሳት፣ መስቀል በዓል ከጊዮርጊስ አደባባይ ወደ ራስ ብሩ ሜዳ ወደ መስቀል አደባባይ መምጣት እና የአደባባዩ መሰየም፣ የአሰብ የነዳጅ ማጣርያ፣ የባህርዳር ፖሊቴክኒክ ኢንስቲትዩት፣ የአባይ ግድብ ቦታ ውሳኔ፣ ጎንደር ጎሀ ሆቴል፣ ላሊበላ ሮሀ ሆቴል፣ ባህርዳር ጣና ሆቴል፣ ትግራይ የሀ ሆቴል ወዘተ በፍጥነት እና በጥራት የተሰሩበት አስደናቂ የኪነህንጻ ወርቃማ ዘመን ነበር፡፡
ከታች በፒዲኤፍ የተያያዘውን ካርታ ማውረድ የሚቻል ሲሆን በካርታው ላይ ያሉት አብዛኞቹ በጥቁር የተመለከቱት ህንጻዎች ክ1950፟-60 የተገነቡ የዚህ የወርቃማው ዘመን ግንባታ ውጤት ነበሩ፡፡ እነዚህ አሁን ክ55 አመታት በላይ ያስቅቆጠሩት እድሜ ጠገብ ህንጻዎች አሁንም በውበትና ባረፈባቸው ጥበብ የሚያንጸባርቁ ህንጻዎች ናቸው፡፡
በ50ዎቹ ምን ተገኝቶ ነው ይሄ ሁሉ በብዛትና በጥራት ሊገነባ የቻለው? ከ50ዎቹ በፊት ለምን አልተገነቡም? ብሩ ከየት መጣ? ገፊ ምክንያቶቹስ ምንድን ናቸው? እስከአሁን እጅግም መልስ አልተገኘላቸውም፡፡ እየጠየቅን እንቀጥላለን፡፡
@ethiopianarchitectureandurbanism
BY WETOPIA COMMUNITY (WAC)
Share with your friend now:
tgoop.com/Utopitecture/1366