tgoop.com/S4i6l/79
Last Update:
የእግዚአብሒር ሰላም ከእናተ ጋር ይሁን።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሣኤው
ከሞት ይበልጥ ኃያል መሆኑን አረጋግጧል።
ይህ በመሆኑም ሞቱና ለፍርድ ሲቀርብ
የገለጠው ዝምታ በውስጡ ካለው ፍርሐት አልመሆኑን እንረዳለን።
ቢናገር ኖሮ አፈቸውን በማስያዝ አድማጮቺን
ማሳመን ይችል ነበር። ይሁን እንጂ የእርሱ ዓለማ ይህ አልነበረም። የእርሱ ዓለማ እኛን ነጻ
ማውጣት ነበር። ስለሆንም ከመሰቀል ላይ
እንዲወርድ በጠየቁት ጊዜ መውረድ
ቢችልም እንኳ ምንም ዓይነት መልስ አልሰጣቸውም። የእርሱ ብቸኛ ዓለማ ስለ እኛ
ሕማምን ተቀብሎ በመሞት የኃጢአትን ዋጋ
በእኛ በመክፈል ለእኛ ስረየትና ድኅነት
ማስገአት ነበር።
የክሮስቶስ ዝምታ ድካም አለመሆኑን ትንሣኤው አረጋግጧል።
የትንሣኤው ኃይል ክርስቶስን በድካም ለሚወነጅሉት ወይም ስቅለቱ የአቅም የማጣቱ
ምልክት እንደ ሆነ አድርገው ለማያስቡ ሰዎች
ሁሉ ብርቱ ምላሽ ነው።
ትንሣኤው ዝምታ የላቁ ዓለማዎች እንዳሉት
አረጋግጧል። እርሱ ዝም ያለው ራሱን ለእኛ
ሊሰጠን ስለ ወደደ ነው። ቢናገር ኖሮ ለፍርድ
ያቀረብት ጠላቶቹን አፍ በማስያዝ አድማጮቹን ማሳመን ይችል ነበር።
ራሱን ቢከላከል ኖሮ የተከሰሰባቸውን ያለ ምንም ጥርጥር ያሸንፍ ነበር።
ከዚህ ሌላ ገና የአስራሁለት ዓመት ብላቴና ሳለ
ይናገራቸው የነበሩት ቃላት ኃይል እነርሱ ራሳቸው በመደነቅ መስክረውለታል።
"ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል
ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጢይቃመቸውም
በመቅደስ አገኙት የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ።" ሉቃ 2:46-
47። አድማጮቹም ቢሆኑ በሥልጣን መናገሩን
በአግራሞት መስክረውለታል። "....ሕዝቡ በትምህርቱ ተገረሙ እንደ ጻፎቻቸው ሳይሆን
እንደ ባለስልጣን ያስተምራቸው ነበረ። " ማቴ
7:28-29። ከዝህ ከፍል የምንረዳው ጌታችን
በአስራሁለት ዓመቱ በአይሁድ መምህራን
መካከል ሲነጋገር እንደ ባለስልጣን ያስተምራቸው የነበረ አምላካችን ነው።
በትንሣኤው ከሞቱ ይበልጥ ኃያል መሆኑን
አረጋግጦልናል። በአንድ ልጅህ በርሱ ያለ ክብርና ጽንዕ ሐአንተ ይገባል ከእርሱ ጋራ
ከመንፈስ ቅዱስም ጋራ ዛሬም ዘወትርም
ለዘላለም ለዘለአለሙ አሜን። መልካም ጊዜ።
BY የ እግዚአብሔር እና የድንግል ማርያም ልጆች
Share with your friend now:
tgoop.com/S4i6l/79