tgoop.com/S4i6l/76
Last Update:
ከእግዚአብሔር አብ ከመደኃኒታችንም ኸጌታ
ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ምህረት ሰላምም
ይሁን።
በጌታችን በመደኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ትንሣኤ የቀረበልን ስጦታ እና በረከት፦
ሁለተኛው፦ዘላለማዊ ሕይወትን መናፈቅ ነው።
ሐዋርያው ቅ.ጳውሎስ ይህን አስመልክቶ
ሲናገር"....ልሄድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር
እናፈቃለሁ ከሁሉም የሚበልጥ ነውና.... "
ፊልጲ1:23። "...ከሥጋ ተለይተን በስደት መኖር በጌታ ማደር ደስ ይለናል። "2ኛ ቆሮ
5:8።ይህ ሐዋርያ ከሙታን መካከል ተለይቶ
ከተነሣው ወደ ሰማይ ካረገውና በአባቱ ቀኝ
ከተቀመጠው ከርስቶስ ጋር ለመሆን ይናፍቅ
ነበር። ይህ ክርስቶስ"...እኔም ከምድር ከፍ ከፍ
ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ። "
ዮሐ 12:32 በማለት የተናገረው ክርስቶስ ነው።
ይህ አባታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኮ እንዲህ ብሎ ተናግሯል ፦"...ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሔዳለሁና ሄጄም ስፍራ
ባዘጋጅላችሁ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ
እንዳትሆኑ ሁለተኛ አመጣለሁ ወደ እኔም አወስዳችኋለሁ። ዮሐ 14 :2-3።
የዘላለም ሕይወት ፍቅር በምድር ላይ ካለው
ሕይወት የሚለቅ ነገር እንዲናፍቁ ቅዱሳን
አባቶቻችን እናእናቶቻችንን አድርጓቸዋል።
ይህ ናፍቆት በምድር ላይ ካለው ምኞትና
ፍላጎት የሚበልጥ ኃይል ያለው ከመሆኑም
በተጨማሪ ከማንኛውም ፍሬ ነገርና መሠረታዊ ጉዳይ ይልቅ የተከበረ ነው። ቅዱስን አባቶች
እና እናቶች ይህችን ምድር የሚመለከቷት እንደ
ኋላ ቀርና ባዕድ ሐገር አድረገው ነው። ራሳቸውን የሚቆጥሩትም እንደ እንግዶችና
እንደ መጻተኞች ነው። "እነዚህ ሁሉ አምነው
ሞቱ የተሰጣቸውን የተሰፋ ቃል አላገኙምና
ዳሩ ግን ከሩቅ ሆነው አይቱና ተሳለሙት
በመድሪቱም እንግዶችና መጻተኞች እንደሆኑ
ታመኑ" ዕብ 11 :13 እንደተባለ።
እነርሱ የሚናፍቁት ሰማያዊዋን ማደርያ ነው።
እነርሱ የሚናፍቁት መንፈሳዊውንና
ዘላለማዊውን ሕይወት ለመምራት ነው።
ከዚህ በተጨማሪ ቅዱሳን የሚናፍቁት ሐዘን
ትካዜ ፣ማቃሰት፣ኃጢአት፣ጥላቻና ዘረኝነት፣
ጠብ የሌሉባትን ሌላ ዓለም ነው። ክፋ ነገር
የሌለበት ምልካም ነገሮች ብቻ የሚገለጡበት
የፍቅር የደስታ የሰላምና የንጽሕና ዓለም ይመጣል። ስለዚህ በትንሣኤው የተገኘውን
በረከት ዘላለማዊ ሕይወትን በመናፈቅ የትንሣኤውን በኣል እየተረዳን እናሳልፍ።
መልካም ጌዜ ይሁንላችሁ።
BY የ እግዚአብሔር እና የድንግል ማርያም ልጆች
Share with your friend now:
tgoop.com/S4i6l/76