tgoop.com/S4i6l/75
Last Update:
ከእግዚአብሔር አባታችን ከጌታም ከኢየሱስ
ክርስቶስ ጸጋና ሰለም ለእናተ ይሁን።
"የትንሣኤው በረከት በሕይወታችን ውስጥ"
1/የመጀመሪያው በረከት፦አለመቻል አይኖርም
ሁሉም ነገር ይቻላል! የሚለው ነው። ሰዎች
በሥራ መስኮቻቸው ውስጥ የሚችሉትን ሁሉ
ያደርጋሉ። በእግዚአብሔር ፊት ሲቆሙ ግን
የሚሠሩት ሥራና ያለቸው እውቀት ሙሉ ለሙሉ
ሰለሚቆም ለመሥራት የሚሞክሩት ሙከራ ሁሉ ጥቅም አይኖረውም።
ይህ ከምተ በኋላ በመቃብር ውስጥ ለአራት
ቀናት የቆየው የአልአዛር እህቶች የማርያምና
የማርታ ስሜት ነበር ፡ስለ አልአዛር እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፦"የሞተውም እኅት ማርታ
ጌታ ሆይ ከሞተ አራት ቀን ሆኖታልና አሁን ይሸታል አለቸው"ዮሐ 14:39።
መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ሰው ከሞት ሲያስነሰው የማይችል ነገር እንደሌለ
እርግጠኞች ሆነዋል። ክርስቶስ አልአዛርን ካስነሣው በኋላ ይህ አልአዛር ተመልሶ ቢሞትም እስከ አሁን ድርስ አልተነሳም። ይህ
ይህን እንጂ መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በራሱ ትንሣኤ ሞትን ድል ነሥቶታል አስከ
ዘለዓለም ድረስ አጥፍቶታል። የጌታችን
የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ዘላለማዊ ስለሆነ
ከዚህ ትንሣኤ ቦኋላ ሞት የለበትም።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የዚህን ትንሣኤ ኃይል ስለ ተመለከተ"ሞት ሆይ መውጊያህ የት
አለ? ሲኦል ሆይ ድል መንሣትህ የት አለ? "
1ኛ ቆሮ 15:55 በማለት ተናግሯል።
በእርግጥም ሞት ስለ ተንኮታኮተ ማንኛውም
ነገር የሚችል ሆኗል። ሰዎች ያመኑት ሁሉን
ማድረግ የሚችለውን እግዚአብሔርን ሁሉን
ነገር ማድረግ የሚችል መሆኑን ብቻ ሳይሆን
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረው
ሰዎችም በእርሱ ኃይል ሰጪነት ሁሉንም ነገር
ማድረግ እንደሚችሉ እንዲህ በማለት አስረግጦ ገልጧል፦"ኃይልን በሚሰጠኝ
በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ። " ፊሊጵ 4:13
ከዚህ ቀደም ብሎ ሲናገረም"...እርሱን የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ...."ፊሊጵ 3:10
መጽሐፍቅዱስ ስለ አለመቻል በወጣው
መመሪያ ውስጥ እንዲህ የሚል ተጽፎ እናነባለን"...ለሚያምን ሁሉ ይቻላል... "ማር 9:23 በማለት ጌታ ተናግሯል። ስለዚህ የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ ካለ ቅ.ጳውሎስ
በትንሣኤው የተገኘ በረከት አንዱ ሁሉን መቻል
ነው። ይህንን ያደረግልን አምላካችን የተመሰገነ
ይሁን። መልካም ጊዜ ተባረኩ።
BY የ እግዚአብሔር እና የድንግል ማርያም ልጆች
Share with your friend now:
tgoop.com/S4i6l/75