Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/Mereb_2012/--): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 50
Mereb: መረብ@Mereb_2012 P.962
MEREB_2012 Telegram 962
በመጅሊሱ ዑለማዓዎችና ሥራ አስፈጻሚ ቦርዶች ላይ ዛቻ ጭምር በመስጠት የመጅሊሱ አመራር (የክልል መጅሊሶችን ጨምሮ) የጋራ አቋም እንዳይኖረውና እንዲከፋፈል እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ስለሆነም ይህን ተግባር በፅኑ እናወግዛለን፡፡ የመጅሊሱ ዑለማዓዎችና የቦርድ አመራሩም ለእነዚህ አፍራሽ አመለካከት ያላቸው ጥቂት ግለሰቦች ሴራ እንዳይንበረከክ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

6ኛ. አንዳንድ የመጅሊስ አመራሮች ያለ ዑለማዓዎችና ቦርዶች የጋራ ውሳኔና እውቅና የሙስሊሙን አንድነት አደጋ ውስጥ የሚያስገባና ትላንት ሙስሊሙን ሲዘርፉ፣ ሲያሳስሩና ሲያስገድሉ ለነበሩ ሠዎች ደብዳቤ እየፃፉ በመጅሊሱ ማህተም ወጭ በማድረግ በየደረጃው ላለው ለመጅሊስ መዋቅር ሳያሳውቅና የስልጣን ተዋረዱን ሳይጠብቅ ወደ ወረዳ፣ ቀበሌና መስጂድ ደብዳቤ ይልካሉ፡፡ ግለሰቦቹም ከፌደራል መጅሊስ ዳብዳቤ ተሰጥቶናል በማለት ሙስሊሙን ህብረተሰብ እየከፋፈሉና እያተራመሱ ብሎም የሠላምና የፀጥታ ችግር እየሆኑ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም፣ ይሄን ህገ-ወጥ ድርጊት የሚፈጽሙ የፌደራል አመራሮች ከዚህ ከተቋማዊ አሰራር ሥርዓት ውጭ ከሆነ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ እናሳስባለን፡፡

7ኛ. በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ላይ ውስጣዊና ውጫዊ የሆኑ አደጋዎች ተጋርጠውበታል፡፡ መንግስታችን አደጋውን ለመቀልበስና የሀገሪቱን ለውጥ ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ከፍተኛ የሆነ እልህ አስጨራሽ ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ መጅሊሳችን ለሀገራችን ሠላምና እድገት መሣካት ከፍተኛ ሚናና አስተዋፅዖ ማድረግ የሚችል የሠፊው ህዝብ ተቋም ነው፡፡ በመሆኑም፣ መጅሊሱ በተለይም የሥራ አመራር ቦርዱ ከምን ጊዜውም በላይ ከመንግስታችን ጎን ለመቆም ቆርጦ ተነስቷል፡፡ ስለሆነም፣ ከሚመለከተው የመንግስት ቷቋማትና ባለ ድርሻ አካላት ጋር እጅና ጓንት በመሆን ለሀገሪቱ ሠላምና ፀጥታ፣ እድገትና ልማት ቆርጦ ይሠራል፡፡

8ኛ. የሥራ አመራር ቦርዱ የተጣለበትን አስተዳደራዊና የልማት ሥራዎች ላይ በሚያደርገው ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ፣ የሙስሊም ምሁራን እያደረጋችሁልን ላለው ሙያዊ ድጋፍ ምስጋናችንን እያቀረብን ለወደፊቱም አሁን ከገባንበት ችግር ለመውጣት በምናደርገው ጥረት ድጋፋችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን::

9ኛ. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን ህጋዊ ሰውነት በአዋጅ እንዲቋቋም የጸደቀውን አዋጅ መነሻ በማድረግ ማስፈጸሚያ ደንብ እና መመሪያ በማዘጋጀት ወደ ሙሉ ትግበራ እንዲገባ በጋራ እሰራለን::

10ኛ. የተዘጋጀውን ዘመናዊ አደረጃጀት እና የአሠራር ሥርዓት መመሪያዎች እና ማኑዋሎች ተግባራዊ በማድረግ ተቋማችንን ለሁሉም ሙስሊም ህብረተሰብ ያለ አድሎ የሚጠበቅበትን አገልግሎት በቅልጥፍናና በፍትሃዊነት አገልግሎት እንዲሰጥ እናደርጋለን::

11ኛ. የሥራ አመራር ቦርዱ የተሰጠውን አስተዳደራዊ እና የልማት ሥራዎችን የማስተባበር ሚና በሚገባ እየተወጣ ባለመሆኑ በቀጣይ አስተዳደራዊና የልማት ሥራዎችን ሙያውን ተጠቅሞ በብቃት በመምራት ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያለበትን ዘርፈ ብዙ ችግሩች እንዲቀረፉ በጋራ እንሰራለን::

12ኛ. ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተረከብነው አፍሪካ ህብረት አጠገብ የሚገኘው ቦታ አለም አቀፍ ኢስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክት ግንባታውን ለማሳካት ሙስሊሙን ህብረተሰብ በማስተባበር ያለብንን ኃላፊነት በጋራ እንወጣለን::

13ኛ. የ1440 ዓመተ ሂጅራ የሃጅ ሥነ-ሥርዓት ለማከናወን ክፍያ ፈጽመው ነገር ግን ኮታ በመሙላቱ ምክንያት መሄድ ያልቻሉ ምዕመናንን የከፈሉት ገንዘብ ተመላሽ እንዲሆን ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፣ ገንዘቡ በወቅቱ ሊመለስ ያልቻለው ወደ ሳውዲ አረቢያ የመጅሊሱ የሐጅ የባንክ ሂሳብ የተላከው ገንዘብ ወደ ሀገር ተመላሽ እንዲደረግ በተደጋጋሚ በስራ አመራር ቦርዱ ጥረት የተደረገ ቢሆንም እንዲመለስ የማይፈልጉ አመራሮች ምክንያት ሊሳካ ባለመቻሉ ነው፡፡ ይሁንና፣ አሁንም ቢሆን የሙስሊሙን ገንዘብ በአስቸኳይ ተመላሽ እንዲሆን በማድረግ ለባለቤቱ እንዲመለስ የሚመለከተው ሁሉ አስፈላጊውን ጥረት እንዲያደርግ እንጠይቃለን፡፡

14ኛ. እኩል ኃላፊነት ተሰጥቶት ወደ ሥራ የገባው የቦርድ አመራር ዋና ጸሐፊ የጋራ ስምምነት ባልተደረሰበት፣ ምንም አይነት የአሰራር ክፍተት ባልታየበት እና የተቋሙን የአሰራር ሥርዓት ባልተከተለ ሁኔታ ከስራ እንዲታገድ በማለት የተፃፈው ደብዳቤ የምናወግዝ መሆኑን እየገለጽን በቀጣይ ዑለማዕ እና ቦርዱ መካከል ያለውን መጓተት በመተው የጋራና የተናጠል ኃላፊነታችንን እንድንወጣ የበኩላችንን ጥሪ እያቀረብን ይህን ድርጊት የፈፀሙ አካላት ከመሰል ድርጊቶች እንዲቆጠቡ እናሳስባለን፡፡

15ኛ. ሙስሊሙ ህብረተሰብ ከመጅሊሳችን ጎን በመቆም በኮቪድ 19 ወረርሽኝ የተጎዱ አካላትን በመደገፍ፤ በሞጣ ጥቃት ድጋፍ ማሰባሰብ፣ በአወሊያ መልሶ ማልማት በተካሄደ የገቢ ማሰባሰብ፣ እንዲሁም በሌሎች የልማት እንቅስቃሴዎች ላይ እያደረገ ላለው ተሳትፎ ያለንን ከፍተኛ ምስጋና እያቀረብን በቀጣይም ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥል እንጠይቃለን፡፡

16ኛ. በትግራይ ክልል የሚገኘው የነጃሺ መስጂድ ላይ የተፈጸመው ጥቃት ሙስሊሙ ላይ ብቻ ሳይሆን በአገራችን ላይ የተቃጣ ጥቃት መሆኑን በመገንዘብ ጥቃቱን እያወገዝን ጉዳቱን ያደረሰው አካል ለህግ እንዲቀርብ እየጠየቅን መንግስትና የሚመለከታቸው አካላት ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ጥገናው እንዲደረግ እንጠይቃለን::

17ኛ. በአገራችን የተለያዩ አካባቢዎች በሠላማዊ ዜጎች ላይ ማንነትንና እምነትን መሰረት አድርጎ እየተፈጸመ ያለውን ጥቃት እናወግዛለን፡፡ በድርጊቱ ላይ የተሳታፉ አካላትም በአስቸኳይ ለህግ እንዲቀርቡ እየጠየቅን ህዝባችን ከምን ጊዜውም በላይ ለአብሮነት ቅድሚያ በመስጠት በሀገራዊ ግንባታ ላይ ንቁ ተሳትፎና ሚናውን አንዲወጣ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

★ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የስራ አመራር ቦርድ እና የክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የስራ አመራር ቦርድ ተወካዮች
★ ጥር 09 ቀን 2013
★ አዲስ አበባ



tgoop.com/Mereb_2012/962
Create:
Last Update:

በመጅሊሱ ዑለማዓዎችና ሥራ አስፈጻሚ ቦርዶች ላይ ዛቻ ጭምር በመስጠት የመጅሊሱ አመራር (የክልል መጅሊሶችን ጨምሮ) የጋራ አቋም እንዳይኖረውና እንዲከፋፈል እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ስለሆነም ይህን ተግባር በፅኑ እናወግዛለን፡፡ የመጅሊሱ ዑለማዓዎችና የቦርድ አመራሩም ለእነዚህ አፍራሽ አመለካከት ያላቸው ጥቂት ግለሰቦች ሴራ እንዳይንበረከክ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

6ኛ. አንዳንድ የመጅሊስ አመራሮች ያለ ዑለማዓዎችና ቦርዶች የጋራ ውሳኔና እውቅና የሙስሊሙን አንድነት አደጋ ውስጥ የሚያስገባና ትላንት ሙስሊሙን ሲዘርፉ፣ ሲያሳስሩና ሲያስገድሉ ለነበሩ ሠዎች ደብዳቤ እየፃፉ በመጅሊሱ ማህተም ወጭ በማድረግ በየደረጃው ላለው ለመጅሊስ መዋቅር ሳያሳውቅና የስልጣን ተዋረዱን ሳይጠብቅ ወደ ወረዳ፣ ቀበሌና መስጂድ ደብዳቤ ይልካሉ፡፡ ግለሰቦቹም ከፌደራል መጅሊስ ዳብዳቤ ተሰጥቶናል በማለት ሙስሊሙን ህብረተሰብ እየከፋፈሉና እያተራመሱ ብሎም የሠላምና የፀጥታ ችግር እየሆኑ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም፣ ይሄን ህገ-ወጥ ድርጊት የሚፈጽሙ የፌደራል አመራሮች ከዚህ ከተቋማዊ አሰራር ሥርዓት ውጭ ከሆነ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ እናሳስባለን፡፡

7ኛ. በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ላይ ውስጣዊና ውጫዊ የሆኑ አደጋዎች ተጋርጠውበታል፡፡ መንግስታችን አደጋውን ለመቀልበስና የሀገሪቱን ለውጥ ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር ከፍተኛ የሆነ እልህ አስጨራሽ ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ መጅሊሳችን ለሀገራችን ሠላምና እድገት መሣካት ከፍተኛ ሚናና አስተዋፅዖ ማድረግ የሚችል የሠፊው ህዝብ ተቋም ነው፡፡ በመሆኑም፣ መጅሊሱ በተለይም የሥራ አመራር ቦርዱ ከምን ጊዜውም በላይ ከመንግስታችን ጎን ለመቆም ቆርጦ ተነስቷል፡፡ ስለሆነም፣ ከሚመለከተው የመንግስት ቷቋማትና ባለ ድርሻ አካላት ጋር እጅና ጓንት በመሆን ለሀገሪቱ ሠላምና ፀጥታ፣ እድገትና ልማት ቆርጦ ይሠራል፡፡

8ኛ. የሥራ አመራር ቦርዱ የተጣለበትን አስተዳደራዊና የልማት ሥራዎች ላይ በሚያደርገው ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ፣ የሙስሊም ምሁራን እያደረጋችሁልን ላለው ሙያዊ ድጋፍ ምስጋናችንን እያቀረብን ለወደፊቱም አሁን ከገባንበት ችግር ለመውጣት በምናደርገው ጥረት ድጋፋችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን::

9ኛ. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን ህጋዊ ሰውነት በአዋጅ እንዲቋቋም የጸደቀውን አዋጅ መነሻ በማድረግ ማስፈጸሚያ ደንብ እና መመሪያ በማዘጋጀት ወደ ሙሉ ትግበራ እንዲገባ በጋራ እሰራለን::

10ኛ. የተዘጋጀውን ዘመናዊ አደረጃጀት እና የአሠራር ሥርዓት መመሪያዎች እና ማኑዋሎች ተግባራዊ በማድረግ ተቋማችንን ለሁሉም ሙስሊም ህብረተሰብ ያለ አድሎ የሚጠበቅበትን አገልግሎት በቅልጥፍናና በፍትሃዊነት አገልግሎት እንዲሰጥ እናደርጋለን::

11ኛ. የሥራ አመራር ቦርዱ የተሰጠውን አስተዳደራዊ እና የልማት ሥራዎችን የማስተባበር ሚና በሚገባ እየተወጣ ባለመሆኑ በቀጣይ አስተዳደራዊና የልማት ሥራዎችን ሙያውን ተጠቅሞ በብቃት በመምራት ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያለበትን ዘርፈ ብዙ ችግሩች እንዲቀረፉ በጋራ እንሰራለን::

12ኛ. ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተረከብነው አፍሪካ ህብረት አጠገብ የሚገኘው ቦታ አለም አቀፍ ኢስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክት ግንባታውን ለማሳካት ሙስሊሙን ህብረተሰብ በማስተባበር ያለብንን ኃላፊነት በጋራ እንወጣለን::

13ኛ. የ1440 ዓመተ ሂጅራ የሃጅ ሥነ-ሥርዓት ለማከናወን ክፍያ ፈጽመው ነገር ግን ኮታ በመሙላቱ ምክንያት መሄድ ያልቻሉ ምዕመናንን የከፈሉት ገንዘብ ተመላሽ እንዲሆን ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፣ ገንዘቡ በወቅቱ ሊመለስ ያልቻለው ወደ ሳውዲ አረቢያ የመጅሊሱ የሐጅ የባንክ ሂሳብ የተላከው ገንዘብ ወደ ሀገር ተመላሽ እንዲደረግ በተደጋጋሚ በስራ አመራር ቦርዱ ጥረት የተደረገ ቢሆንም እንዲመለስ የማይፈልጉ አመራሮች ምክንያት ሊሳካ ባለመቻሉ ነው፡፡ ይሁንና፣ አሁንም ቢሆን የሙስሊሙን ገንዘብ በአስቸኳይ ተመላሽ እንዲሆን በማድረግ ለባለቤቱ እንዲመለስ የሚመለከተው ሁሉ አስፈላጊውን ጥረት እንዲያደርግ እንጠይቃለን፡፡

14ኛ. እኩል ኃላፊነት ተሰጥቶት ወደ ሥራ የገባው የቦርድ አመራር ዋና ጸሐፊ የጋራ ስምምነት ባልተደረሰበት፣ ምንም አይነት የአሰራር ክፍተት ባልታየበት እና የተቋሙን የአሰራር ሥርዓት ባልተከተለ ሁኔታ ከስራ እንዲታገድ በማለት የተፃፈው ደብዳቤ የምናወግዝ መሆኑን እየገለጽን በቀጣይ ዑለማዕ እና ቦርዱ መካከል ያለውን መጓተት በመተው የጋራና የተናጠል ኃላፊነታችንን እንድንወጣ የበኩላችንን ጥሪ እያቀረብን ይህን ድርጊት የፈፀሙ አካላት ከመሰል ድርጊቶች እንዲቆጠቡ እናሳስባለን፡፡

15ኛ. ሙስሊሙ ህብረተሰብ ከመጅሊሳችን ጎን በመቆም በኮቪድ 19 ወረርሽኝ የተጎዱ አካላትን በመደገፍ፤ በሞጣ ጥቃት ድጋፍ ማሰባሰብ፣ በአወሊያ መልሶ ማልማት በተካሄደ የገቢ ማሰባሰብ፣ እንዲሁም በሌሎች የልማት እንቅስቃሴዎች ላይ እያደረገ ላለው ተሳትፎ ያለንን ከፍተኛ ምስጋና እያቀረብን በቀጣይም ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥል እንጠይቃለን፡፡

16ኛ. በትግራይ ክልል የሚገኘው የነጃሺ መስጂድ ላይ የተፈጸመው ጥቃት ሙስሊሙ ላይ ብቻ ሳይሆን በአገራችን ላይ የተቃጣ ጥቃት መሆኑን በመገንዘብ ጥቃቱን እያወገዝን ጉዳቱን ያደረሰው አካል ለህግ እንዲቀርብ እየጠየቅን መንግስትና የሚመለከታቸው አካላት ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ጥገናው እንዲደረግ እንጠይቃለን::

17ኛ. በአገራችን የተለያዩ አካባቢዎች በሠላማዊ ዜጎች ላይ ማንነትንና እምነትን መሰረት አድርጎ እየተፈጸመ ያለውን ጥቃት እናወግዛለን፡፡ በድርጊቱ ላይ የተሳታፉ አካላትም በአስቸኳይ ለህግ እንዲቀርቡ እየጠየቅን ህዝባችን ከምን ጊዜውም በላይ ለአብሮነት ቅድሚያ በመስጠት በሀገራዊ ግንባታ ላይ ንቁ ተሳትፎና ሚናውን አንዲወጣ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

★ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የስራ አመራር ቦርድ እና የክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የስራ አመራር ቦርድ ተወካዮች
★ ጥር 09 ቀን 2013
★ አዲስ አበባ

BY Mereb: መረብ


Share with your friend now:
tgoop.com/Mereb_2012/962

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Hashtags are a fast way to find the correct information on social media. To put your content out there, be sure to add hashtags to each post. We have two intelligent tips to give you: To upload a logo, click the Menu icon and select “Manage Channel.” In a new window, hit the Camera icon. Deputy District Judge Peter Hui sentenced computer technician Ng Man-ho on Thursday, a month after the 27-year-old, who ran a Telegram group called SUCK Channel, was found guilty of seven charges of conspiring to incite others to commit illegal acts during the 2019 extradition bill protests and subsequent months. How to Create a Private or Public Channel on Telegram? 1What is Telegram Channels?
from us


Telegram Mereb: መረብ
FROM American