KETBEB_MENDER Telegram 3522
​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​♥️♡:。.。 እዮሪካ 。.。:♡♥️

ክፍል 23

ደራሲ - አብላካት



እኔም ከእነሱ መሀል እየነጠልኩኝ ማውራት ስለ ማልፈልግ አቤልንም ከዚህ በኋላ እኔን ብሎ እንዳይመጣ ነገርኩት.... ምክንያቱም ሳባን አውቃታለው ማናቸውም እንዲያዋሩኝ አትፈልግም እሱንም ከምታኮርፈው እኔው ብሸሽ ይሻለኛል። ሰዓቴን አመቻችቼ ስራዬንና ትምህርቴን እኩል ማስኬድ ችያለው። ገንዘቡ ያስፈልገኛል ሁሉም የእናቴን እጅ ነው እሚጠብቁት ሰርቶ እንኳን ይሄንን ልቻል እሚል የለም ሁሌም ብር ባስፈለጋት ቁጥር ከእንጀራ አባቴ ጋር መጨቃጨቋ ሰላሜን ይነሳኛል... አባቢ በህይወት እያለ ደልቶን ባንኖር እኔ እና እናቴ ግን የጎደለብን ምንም ነገር አልነበረም ምንም ሰርቶ ቢሆን እኔን ከጓደኞቼ እኩል እናቴንም ከጎረቤቶቿ አያሳንሳትም ነበር። ዛሬ ላይ ግን የየአማን እና የሊድያ የትምህርት ክፍያ ሲደርስ የወር አስቤዛ ሲያልቅባት ማጠፊያው ሁሉ ያጥራታል.....ለአንድ ለራሴ አላንስም ግን ደግሞ እናቴን በዚህ ሁኔታ እራስሽ ተወጪው ልላት አልችልም ፤ ገና ድሮ ለማግባት ስትወስን ትክክለኛው ሰው እንዳልሆነ ደጋግሜ ስነግራት የሷን ኑሮ ይኖሩላት ይመስል ሁሉም ጎረቤት የምን እራስ ወዳድነት ነው... ያንቺ አባት ከሞተ እናትሽ ህይወቷን አትኑር እንዴ እያሉ አፍ አፌን ይሉኝ ነበር....የኔ ፍራቻ ይሄ ነበር ዛሬ እናቴ ያለችበት ሁኔታ ለእሷ አይገባትም። ድሮ አግቢ አግቢ ብለው ገፋፍተው እዚህ መናጢ ላይ የጣሏት ሰዎች ዛሬ አንድ ኪሎ ሽንኩርት አይገዙላትም። ለምንድነው በሰው ህይወት ፈላጭ ቆራጭ እምንሆነው..... እናቴን የተመቀኘኋት ይመስል ሀሳቤን ሲያጣጥሉ ነበር አሁን ግን ብቻዋን ናት ያኔ ምን ነበር ያላችሁት ብዬ ዛሬ ላይ ብጠይቃቸው እርግጠኛ ነኝ መልሳቸው እሚሆነው ለሷ ብለን እንጂ አላስገደድናት ነው እሚሉኝ።

የኔን ህይወት እምኖረው እኔ ነኝ እናት እና አባቴ እንኳን የተሻለ እንዲገጥመኝ መመኘት እና መጥፎ እና ጥሩውን ሊነግሩኝ እንጂ ሊወስኑልኝ አይገባም.....የሰዎችን ሀሳብ አላጣጥልም እቀበላለው ግን ደግሞ ማንም የወሰነልኝን አልኖርም.... ነገ እኔ ብቸገር አብሮኝ እሚቸገር የለም እንዲህ አድርጊ እንዲህ ሁኚ ያለኝ ሁሉ ከንፈር ከመምጠጥ የዘለለ ምንም አያደርግልኝም። ውሳኔያችን ነጋችን ላይ ችግር እንደማይፈጥር ቆም ብለን ማሰብ አለብን ሰው ስላለን ስላበረታታን ብቻ የነሱን ሀሳብ ተቀብለን መተግበር የለብንም ባይ ነኝ። ፈረስ ያደርሳል እንጂ አይዋጋም ሰውም በል በል ብሎ ከመሀል ያደርስል እንጂ አብሮ አይዘልቅም።

ከክላስ በኋላ ወደ ስራ ሄጄ ስራዬን ስጨርስ ማይለፍ እራት ጋብዞኝ ደስ የሚል ጊዜ አሳለፍን....ወደ ቤት ሸኝቶኝ ሲመለስ ሊድያን ከሆነ መኪና ስትወርድ አየኋት። ሰውየውን እንደምንም ለማየት ስሞክር በእድሜ ገፋ ያለ ሰው ነው....ሹገር ዳዲ እሚባለው አይነት.... ለተራ ገንዘብ ብሎ እራስን ክብርን እንደ መሸጥ ምን ውርደት አለ ..... አንዳንዴ እንደ እህት ብትቀርበኝ እና ይህ ነገር እንደማይጠቅማት ብነግራት ብዬ እመኛለው.....እራሷን ስታጣ ዝም ብዬ መመልከቴን ሳስብ ክፉ የሆንኩ ይመስለኛል....ምንም ቢሆን የእናቴ ልጅ ናት ክፉዋን ማየት መስማት አልፈልግም። መኪናው ከሄደ በኋላ ወደ ግቢ ልትገባ ስትል እጇን ያስኳት....

"ያምሻል እንዴ አስደነገጥሽኝ እኮ! ምንድነው ?" አለችኝ...
"ማነው ሰውየው ?" አልኳት....
"ማንም አደለም ደሞ ማንስ ቢሆን ምን ያገባሻል!?"
"እሱ እኮ አባትሽ ይሆን ገና ልጅ እኮ ነሽ ለምን እንደ እድሜ አትሆኚም !"
"እራስሽን እንደ ታላቅ እህት ቆጥረሽ እየተቆጣሽኝ ባልሆነ ። ትሰሚኛልሽ የፈለኩትን ከፈለኩት ሰው ጋር መሆን እችላለው ይሄ አንቺን አይመለከትም " አለችኝ.....
"እዮልሽ ሊድያ ከዚህ እምታተርፊው እራስን ማጣት ነው እባክሽን እንደዚህ መሆንሽን አቅም"
"ነገርኩሽ እማይመለከትሽ ነገር ውስጥ ጥልቅ አትበይ። ምነው አንቺ ከዚህ የተሻለ ውሎ እምትውዪ አስመሰልሽው ከማንም ጋር ስትልከሰከሺ አደል እንዴ እምትውይው!" ብላ ንግግሯን ልትቀጥል ስትል ገፍትሬያት ወደ ውስጥ ገባሁኝ።



ይቀጥላል....

ቀጣዩ ክፍል 100❤️ ሲደርስ ይለቀቃል እያነበባችሁ አስተያየታችሁን አድርሱኝ...


ለአስተያየት - @Yetomah_Bot


✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯
@Ketbeb_Mender
@Ketbeb_Mender
✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯



tgoop.com/Ketbeb_mender/3522
Create:
Last Update:

​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​♥️♡:。.。 እዮሪካ 。.。:♡♥️

ክፍል 23

ደራሲ - አብላካት



እኔም ከእነሱ መሀል እየነጠልኩኝ ማውራት ስለ ማልፈልግ አቤልንም ከዚህ በኋላ እኔን ብሎ እንዳይመጣ ነገርኩት.... ምክንያቱም ሳባን አውቃታለው ማናቸውም እንዲያዋሩኝ አትፈልግም እሱንም ከምታኮርፈው እኔው ብሸሽ ይሻለኛል። ሰዓቴን አመቻችቼ ስራዬንና ትምህርቴን እኩል ማስኬድ ችያለው። ገንዘቡ ያስፈልገኛል ሁሉም የእናቴን እጅ ነው እሚጠብቁት ሰርቶ እንኳን ይሄንን ልቻል እሚል የለም ሁሌም ብር ባስፈለጋት ቁጥር ከእንጀራ አባቴ ጋር መጨቃጨቋ ሰላሜን ይነሳኛል... አባቢ በህይወት እያለ ደልቶን ባንኖር እኔ እና እናቴ ግን የጎደለብን ምንም ነገር አልነበረም ምንም ሰርቶ ቢሆን እኔን ከጓደኞቼ እኩል እናቴንም ከጎረቤቶቿ አያሳንሳትም ነበር። ዛሬ ላይ ግን የየአማን እና የሊድያ የትምህርት ክፍያ ሲደርስ የወር አስቤዛ ሲያልቅባት ማጠፊያው ሁሉ ያጥራታል.....ለአንድ ለራሴ አላንስም ግን ደግሞ እናቴን በዚህ ሁኔታ እራስሽ ተወጪው ልላት አልችልም ፤ ገና ድሮ ለማግባት ስትወስን ትክክለኛው ሰው እንዳልሆነ ደጋግሜ ስነግራት የሷን ኑሮ ይኖሩላት ይመስል ሁሉም ጎረቤት የምን እራስ ወዳድነት ነው... ያንቺ አባት ከሞተ እናትሽ ህይወቷን አትኑር እንዴ እያሉ አፍ አፌን ይሉኝ ነበር....የኔ ፍራቻ ይሄ ነበር ዛሬ እናቴ ያለችበት ሁኔታ ለእሷ አይገባትም። ድሮ አግቢ አግቢ ብለው ገፋፍተው እዚህ መናጢ ላይ የጣሏት ሰዎች ዛሬ አንድ ኪሎ ሽንኩርት አይገዙላትም። ለምንድነው በሰው ህይወት ፈላጭ ቆራጭ እምንሆነው..... እናቴን የተመቀኘኋት ይመስል ሀሳቤን ሲያጣጥሉ ነበር አሁን ግን ብቻዋን ናት ያኔ ምን ነበር ያላችሁት ብዬ ዛሬ ላይ ብጠይቃቸው እርግጠኛ ነኝ መልሳቸው እሚሆነው ለሷ ብለን እንጂ አላስገደድናት ነው እሚሉኝ።

የኔን ህይወት እምኖረው እኔ ነኝ እናት እና አባቴ እንኳን የተሻለ እንዲገጥመኝ መመኘት እና መጥፎ እና ጥሩውን ሊነግሩኝ እንጂ ሊወስኑልኝ አይገባም.....የሰዎችን ሀሳብ አላጣጥልም እቀበላለው ግን ደግሞ ማንም የወሰነልኝን አልኖርም.... ነገ እኔ ብቸገር አብሮኝ እሚቸገር የለም እንዲህ አድርጊ እንዲህ ሁኚ ያለኝ ሁሉ ከንፈር ከመምጠጥ የዘለለ ምንም አያደርግልኝም። ውሳኔያችን ነጋችን ላይ ችግር እንደማይፈጥር ቆም ብለን ማሰብ አለብን ሰው ስላለን ስላበረታታን ብቻ የነሱን ሀሳብ ተቀብለን መተግበር የለብንም ባይ ነኝ። ፈረስ ያደርሳል እንጂ አይዋጋም ሰውም በል በል ብሎ ከመሀል ያደርስል እንጂ አብሮ አይዘልቅም።

ከክላስ በኋላ ወደ ስራ ሄጄ ስራዬን ስጨርስ ማይለፍ እራት ጋብዞኝ ደስ የሚል ጊዜ አሳለፍን....ወደ ቤት ሸኝቶኝ ሲመለስ ሊድያን ከሆነ መኪና ስትወርድ አየኋት። ሰውየውን እንደምንም ለማየት ስሞክር በእድሜ ገፋ ያለ ሰው ነው....ሹገር ዳዲ እሚባለው አይነት.... ለተራ ገንዘብ ብሎ እራስን ክብርን እንደ መሸጥ ምን ውርደት አለ ..... አንዳንዴ እንደ እህት ብትቀርበኝ እና ይህ ነገር እንደማይጠቅማት ብነግራት ብዬ እመኛለው.....እራሷን ስታጣ ዝም ብዬ መመልከቴን ሳስብ ክፉ የሆንኩ ይመስለኛል....ምንም ቢሆን የእናቴ ልጅ ናት ክፉዋን ማየት መስማት አልፈልግም። መኪናው ከሄደ በኋላ ወደ ግቢ ልትገባ ስትል እጇን ያስኳት....

"ያምሻል እንዴ አስደነገጥሽኝ እኮ! ምንድነው ?" አለችኝ...
"ማነው ሰውየው ?" አልኳት....
"ማንም አደለም ደሞ ማንስ ቢሆን ምን ያገባሻል!?"
"እሱ እኮ አባትሽ ይሆን ገና ልጅ እኮ ነሽ ለምን እንደ እድሜ አትሆኚም !"
"እራስሽን እንደ ታላቅ እህት ቆጥረሽ እየተቆጣሽኝ ባልሆነ ። ትሰሚኛልሽ የፈለኩትን ከፈለኩት ሰው ጋር መሆን እችላለው ይሄ አንቺን አይመለከትም " አለችኝ.....
"እዮልሽ ሊድያ ከዚህ እምታተርፊው እራስን ማጣት ነው እባክሽን እንደዚህ መሆንሽን አቅም"
"ነገርኩሽ እማይመለከትሽ ነገር ውስጥ ጥልቅ አትበይ። ምነው አንቺ ከዚህ የተሻለ ውሎ እምትውዪ አስመሰልሽው ከማንም ጋር ስትልከሰከሺ አደል እንዴ እምትውይው!" ብላ ንግግሯን ልትቀጥል ስትል ገፍትሬያት ወደ ውስጥ ገባሁኝ።



ይቀጥላል....

ቀጣዩ ክፍል 100❤️ ሲደርስ ይለቀቃል እያነበባችሁ አስተያየታችሁን አድርሱኝ...


ለአስተያየት - @Yetomah_Bot


✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯
@Ketbeb_Mender
@Ketbeb_Mender
✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯

BY የብዕር ጠብታ✍📒📖




Share with your friend now:
tgoop.com/Ketbeb_mender/3522

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Telegram channels enable users to broadcast messages to multiple users simultaneously. Like on social media, users need to subscribe to your channel to get access to your content published by one or more administrators. Your posting frequency depends on the topic of your channel. If you have a news channel, it’s OK to publish new content every day (or even every hour). For other industries, stick with 2-3 large posts a week. Ng Man-ho, a 27-year-old computer technician, was convicted last month of seven counts of incitement charges after he made use of the 100,000-member Chinese-language channel that he runs and manages to post "seditious messages," which had been shut down since August 2020. But a Telegram statement also said: "Any requests related to political censorship or limiting human rights such as the rights to free speech or assembly are not and will not be considered." A new window will come up. Enter your channel name and bio. (See the character limits above.) Click “Create.”
from us


Telegram የብዕር ጠብታ✍📒📖
FROM American