KETBEB_MENDER Telegram 3514
​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​♥️♡:。.。 እዮሪካ 。.。:♡♥️

ክፍል 21

ደራሲ - አብላካት



ለጋሼም ከአባቴ ሞት በኋላ የገጠመኝንና እየገጠመኝ ያለውን ነገር በሙሉ ምንም ሳላስቀር ነገርኳቸው እሳቸውም ሰለቸኝ ሳይሉ ብሶቴን ሲያደምጡኝ ቆዩና እንዲህ አሉኝ......

"የኔ ልጅ ሁላችንም አነሰም በዛም የውስጣችን ቁስል አለን። ሁላችንም ታመናል ፣ ደምተናል ፣ የመኖር ተስፋችን ጨልሞ ሞታችንን ናፍቀናል። ግና ልጄ አንቺ ዛሬ እያሳለፍሽ ያለውን ችግር እንኳን ሳያሳልፍ መኖር እየፈለገ በአጭሩ እሚቀጭ ስንት አለ ? መናገር እየፈለገ መናገር እማይችል ዲዳ ፣ መስማት እየፈለገ መስማት ያልቻለ ፣ ማየት እየፈለገ ፀሀይ ምን እንደ ምትመስል ፣ የጨረቃ ገፅታ እንዴት ይሆን እያለ ማየቱን እየናፈቀ ማየት የተሳነው ፣ እሮጦ ማምለጥን ተራምዶ መሄድን እሚመኝ አካል ጉዳተኛ ፣ ሀዘኑን ሳቁን ደስታውን ችግሩን እሚካፈለው አለው እሚለው ያጣ የጎዳና ተዳዳሪ በሞላባት ይቺ እደለቢስ አለም ላይ ተቀምጠን ማማረር የፈጣሪን አይን መጠንቆል ነው ልጄ። አላዘንሽም አልተጎዳሽም ሳይሆን የሌላውን ካንቺ የከፋ የገጠመውን አይተሽ ተፅናኚ። ልጄ እማያልፍ ቀን እማይነጋ ለሊት የለም ብቻ በአምላክሽ ተማመኚ ተስፋሽን በሱ አድርጊ የፈጠረን ጌታ ጥሎ አይጥለንም። አንቺ ብቻ በርትተሽ ነገ የተሻለ እንደሚሆን እመኚ ፤ አንድ ነገር ዛሬም ነገም ሲደጋገምብሽ ንቀሽ መተውን ልመጂ። ልጄ የቀን ጎዶሎ ብዙ ያሳያል ያ እንዳይመጣ እራስሽን አበርቺ። ውድቀትን እንጂ ስኬትን እሚመኝ በጠፋበት ጊዜ ንቆ መተውን ችሎ ማለፍን ተማሪ። የኛ ሰው ስትሸነፊ እጅ ስትሰቺ መሄጃ ስታጪ ነው ከንፈር ለመምጠት እና ለመዘባበት እሚመጣው ። ታዲያ ለማን ለየቱ ሰው ብለሽ ነው እራስሽን እምትጎጂ ? ከተሻለሽ ስኬትሽን ሳቅ ደስታሽን አሳዪ ያ ካልሆነ ግን እምባና መከፋት ጉዳትሽን ለራስሽ እና ለፈጣሪሽ ንገሪ። ነገ የተሻለ ይሆንና ዛሬ ላይ እምታሳልፊውን ሁሉ ነበር ብለሽ ታወሪዋለሽ ፤ በነበር ለሚቀር ህይወት እራስሽን ለሽንፈት እና ለውድቀት አሳልፈሽ አትስጪ።" ብለው የአባትነት ለዛ በተሞላበት አንደበታቸው ወደ ራሴ እንድ መለስና ዙሪያዬን እንዳጤን መንገድ ከፍተውልኛል። አንዳንዴ ሰው ባስፈለገን አይዟቹ ባይ ባጣን ጊዜ አለሁ እሚል መካሪ አፅናኝ ወዳጅን እንደማግኘት ምን እደለኝነት አለ። ጋሼ ለኔ በዚህን ሰዓት ከፈጣሪ እንደተላኩ መልዕክ ነው የሆኑኝ ፤ በፊት የነበረኝ ትዕግስተኝነት ጠፍቶ ግልፍተኛ እየሆንኩ በመጣሁበት ጊዜ ነው የደረሱልኝ ፤ እውነት ነው ችሎ ማለፍን እና ንቆ መተውን የመሰለ ምን አለ ? እሱም እኮ መልስ ነው።

ምን አልባት እናቴ የመታችኝ ለነሱ ደግፍ ሳይሆን የኔ እንደዚህ መለወጥ አናዷት ይሆን ? ግራ ገባኝ ግን እናቴ ላይ ቂም ከምይዝ ምክንያቷን ብጠይቃት ቀን ከሌት ከመብሰልሰል እተርፍ ይሆናል። አሁን ተረጋግቻለው ደስም ብሎኛል ምክንያቱም ወደ እራሴ መመለስ ባለብኝ ሰዓት እኚህን የመሰሉ መልካም አባት ስለሰጠኝ ደስ ብሎኛል ፤ ብቻ ለሁሉም ነገር ፈጣሪ ይመስገን። ሀሳቤን ሰብስቤ ጋሼን አመስግኜ ወደ እራሴ ተመልሼ ነገሮችን ለማስተካከል እንደምሞክር ቃል ገባሁላቸው።

ትንሽ ቆይቼ ለእራታቸው እሚሆን ምግብ ልሰራላቸው ወደ ውስጥ ገባሁኝ ስገባ የቤቱ ሁኔታ ልክ አልነበረም እናም እቃዎቹን አንድም ሳላስቀር ወደ ውጪ አወጣኋቸው። ያው ጋሼ እንድሰራ ባይፈልጉም እኔ ግን ከእሳቸውም የባስኩ ደረቅ ስለሆንኩኝ እሳቸውም እያገዙኝ ቤቱን አፅድቼ አስተካከልኩኝ እና ውስጥ ገብተን እራት እየሰራሁላቸው ብዙ ተጨዋወትን። በመሀልም ከጋሼ ውጪ የመታወቂያ ስማቸው ማን እንደሆነ ጠየቋቸው....

" ጋሼ ትክክለኛ ስሞት ግን ማነው ? ማለቴ ቢነግሩኝ ችግር ከሌለው" አልኳቸው
" ምን ገዶኝ የኔ ልጅ እንግዲ ልጅ ጌታ መሳይ ጋሼ ይለኛል እኔም በዛው ለመድኩ እንጂ ስሜስ አባ ያዕቆብ እባላለሁ ከሀገሬ ሳለው ቤተክርስቲያን ስለነበርኩ አባ ይሉኛል ከስሜ ጋር በአንድ አባ ያዕቆብ ነው" አሉኝ
"ታዲያ እኮ ይሄ ነው ደስ እሚለው እኔ ጋሼ ስሎት ይጨንቀኛል ከዚህ በኋላ አባ ያዕቆብ ነው እምሎት " አልኳቸው....
"ደስ ነው እሚለኝ ልጄዋ" ብለውኝ ወደ ጨዋታችን ተመለስን። ወደ አስራ አንድ ሰዓት ገደማ ለማይለፍ ደወልኩለት እና መጥቶ ወሰደኝ።



ይቀጥላል....

ቀጣዩ ክፍል እንዲለቀቅ እያነበባችሁ አስተያየታችሁን አድርሱኝ...


ለአስተያየት - @Yetomah_Bot



✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯
@Ketbeb_Mender
@Ketbeb_Mender
✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯



tgoop.com/Ketbeb_mender/3514
Create:
Last Update:

​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​♥️♡:。.。 እዮሪካ 。.。:♡♥️

ክፍል 21

ደራሲ - አብላካት



ለጋሼም ከአባቴ ሞት በኋላ የገጠመኝንና እየገጠመኝ ያለውን ነገር በሙሉ ምንም ሳላስቀር ነገርኳቸው እሳቸውም ሰለቸኝ ሳይሉ ብሶቴን ሲያደምጡኝ ቆዩና እንዲህ አሉኝ......

"የኔ ልጅ ሁላችንም አነሰም በዛም የውስጣችን ቁስል አለን። ሁላችንም ታመናል ፣ ደምተናል ፣ የመኖር ተስፋችን ጨልሞ ሞታችንን ናፍቀናል። ግና ልጄ አንቺ ዛሬ እያሳለፍሽ ያለውን ችግር እንኳን ሳያሳልፍ መኖር እየፈለገ በአጭሩ እሚቀጭ ስንት አለ ? መናገር እየፈለገ መናገር እማይችል ዲዳ ፣ መስማት እየፈለገ መስማት ያልቻለ ፣ ማየት እየፈለገ ፀሀይ ምን እንደ ምትመስል ፣ የጨረቃ ገፅታ እንዴት ይሆን እያለ ማየቱን እየናፈቀ ማየት የተሳነው ፣ እሮጦ ማምለጥን ተራምዶ መሄድን እሚመኝ አካል ጉዳተኛ ፣ ሀዘኑን ሳቁን ደስታውን ችግሩን እሚካፈለው አለው እሚለው ያጣ የጎዳና ተዳዳሪ በሞላባት ይቺ እደለቢስ አለም ላይ ተቀምጠን ማማረር የፈጣሪን አይን መጠንቆል ነው ልጄ። አላዘንሽም አልተጎዳሽም ሳይሆን የሌላውን ካንቺ የከፋ የገጠመውን አይተሽ ተፅናኚ። ልጄ እማያልፍ ቀን እማይነጋ ለሊት የለም ብቻ በአምላክሽ ተማመኚ ተስፋሽን በሱ አድርጊ የፈጠረን ጌታ ጥሎ አይጥለንም። አንቺ ብቻ በርትተሽ ነገ የተሻለ እንደሚሆን እመኚ ፤ አንድ ነገር ዛሬም ነገም ሲደጋገምብሽ ንቀሽ መተውን ልመጂ። ልጄ የቀን ጎዶሎ ብዙ ያሳያል ያ እንዳይመጣ እራስሽን አበርቺ። ውድቀትን እንጂ ስኬትን እሚመኝ በጠፋበት ጊዜ ንቆ መተውን ችሎ ማለፍን ተማሪ። የኛ ሰው ስትሸነፊ እጅ ስትሰቺ መሄጃ ስታጪ ነው ከንፈር ለመምጠት እና ለመዘባበት እሚመጣው ። ታዲያ ለማን ለየቱ ሰው ብለሽ ነው እራስሽን እምትጎጂ ? ከተሻለሽ ስኬትሽን ሳቅ ደስታሽን አሳዪ ያ ካልሆነ ግን እምባና መከፋት ጉዳትሽን ለራስሽ እና ለፈጣሪሽ ንገሪ። ነገ የተሻለ ይሆንና ዛሬ ላይ እምታሳልፊውን ሁሉ ነበር ብለሽ ታወሪዋለሽ ፤ በነበር ለሚቀር ህይወት እራስሽን ለሽንፈት እና ለውድቀት አሳልፈሽ አትስጪ።" ብለው የአባትነት ለዛ በተሞላበት አንደበታቸው ወደ ራሴ እንድ መለስና ዙሪያዬን እንዳጤን መንገድ ከፍተውልኛል። አንዳንዴ ሰው ባስፈለገን አይዟቹ ባይ ባጣን ጊዜ አለሁ እሚል መካሪ አፅናኝ ወዳጅን እንደማግኘት ምን እደለኝነት አለ። ጋሼ ለኔ በዚህን ሰዓት ከፈጣሪ እንደተላኩ መልዕክ ነው የሆኑኝ ፤ በፊት የነበረኝ ትዕግስተኝነት ጠፍቶ ግልፍተኛ እየሆንኩ በመጣሁበት ጊዜ ነው የደረሱልኝ ፤ እውነት ነው ችሎ ማለፍን እና ንቆ መተውን የመሰለ ምን አለ ? እሱም እኮ መልስ ነው።

ምን አልባት እናቴ የመታችኝ ለነሱ ደግፍ ሳይሆን የኔ እንደዚህ መለወጥ አናዷት ይሆን ? ግራ ገባኝ ግን እናቴ ላይ ቂም ከምይዝ ምክንያቷን ብጠይቃት ቀን ከሌት ከመብሰልሰል እተርፍ ይሆናል። አሁን ተረጋግቻለው ደስም ብሎኛል ምክንያቱም ወደ እራሴ መመለስ ባለብኝ ሰዓት እኚህን የመሰሉ መልካም አባት ስለሰጠኝ ደስ ብሎኛል ፤ ብቻ ለሁሉም ነገር ፈጣሪ ይመስገን። ሀሳቤን ሰብስቤ ጋሼን አመስግኜ ወደ እራሴ ተመልሼ ነገሮችን ለማስተካከል እንደምሞክር ቃል ገባሁላቸው።

ትንሽ ቆይቼ ለእራታቸው እሚሆን ምግብ ልሰራላቸው ወደ ውስጥ ገባሁኝ ስገባ የቤቱ ሁኔታ ልክ አልነበረም እናም እቃዎቹን አንድም ሳላስቀር ወደ ውጪ አወጣኋቸው። ያው ጋሼ እንድሰራ ባይፈልጉም እኔ ግን ከእሳቸውም የባስኩ ደረቅ ስለሆንኩኝ እሳቸውም እያገዙኝ ቤቱን አፅድቼ አስተካከልኩኝ እና ውስጥ ገብተን እራት እየሰራሁላቸው ብዙ ተጨዋወትን። በመሀልም ከጋሼ ውጪ የመታወቂያ ስማቸው ማን እንደሆነ ጠየቋቸው....

" ጋሼ ትክክለኛ ስሞት ግን ማነው ? ማለቴ ቢነግሩኝ ችግር ከሌለው" አልኳቸው
" ምን ገዶኝ የኔ ልጅ እንግዲ ልጅ ጌታ መሳይ ጋሼ ይለኛል እኔም በዛው ለመድኩ እንጂ ስሜስ አባ ያዕቆብ እባላለሁ ከሀገሬ ሳለው ቤተክርስቲያን ስለነበርኩ አባ ይሉኛል ከስሜ ጋር በአንድ አባ ያዕቆብ ነው" አሉኝ
"ታዲያ እኮ ይሄ ነው ደስ እሚለው እኔ ጋሼ ስሎት ይጨንቀኛል ከዚህ በኋላ አባ ያዕቆብ ነው እምሎት " አልኳቸው....
"ደስ ነው እሚለኝ ልጄዋ" ብለውኝ ወደ ጨዋታችን ተመለስን። ወደ አስራ አንድ ሰዓት ገደማ ለማይለፍ ደወልኩለት እና መጥቶ ወሰደኝ።



ይቀጥላል....

ቀጣዩ ክፍል እንዲለቀቅ እያነበባችሁ አስተያየታችሁን አድርሱኝ...


ለአስተያየት - @Yetomah_Bot



✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯
@Ketbeb_Mender
@Ketbeb_Mender
✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯

BY የብዕር ጠብታ✍📒📖




Share with your friend now:
tgoop.com/Ketbeb_mender/3514

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

In handing down the sentence yesterday, deputy judge Peter Hui Shiu-keung of the district court said that even if Ng did not post the messages, he cannot shirk responsibility as the owner and administrator of such a big group for allowing these messages that incite illegal behaviors to exist. Invite up to 200 users from your contacts to join your channel Select: Settings – Manage Channel – Administrators – Add administrator. From your list of subscribers, select the correct user. A new window will appear on the screen. Check the rights you’re willing to give to your administrator. Add up to 50 administrators Commenting about the court's concerns about the spread of false information related to the elections, Minister Fachin noted Brazil is "facing circumstances that could put Brazil's democracy at risk." During the meeting, the information technology secretary at the TSE, Julio Valente, put forward a list of requests the court believes will disinformation.
from us


Telegram የብዕር ጠብታ✍📒📖
FROM American