KETBEB_MENDER Telegram 3482
​​​​​​​​​​​♥️♡:。.。 እዮሪካ 。.。:♡♥️

ክፍል ፲፮

ደራሲ - አብላካት



ለሶስት ሳምንት ያህል ወደ ጊቢ አልሄድንም ነበር ለሁላችንም ትልቅ የልብ ስብራት ሆኖ ለረጅም ጊዜ ቆይቷል ዛሬን እንደዛው ነው አልዳነም ባሰብናት ቁጥር ያመናል። ለሳቢ ደግሞ ከሞትም በላይ ሞት ነው እናቷን ያጣች ያህል ነው ለሷ ቁስሉ ። ሁሌም ታስታውሳታለች በሳቅ እና በውሸት ፈግግታ እንደረሳቻት ታስመስላለች እንጂ ለደቂቃ እንኳን ከሀሳቧ ርቃ አታውቅም።

ፍቅርን እምፈራው ለዚህ ነው ማጣትን እሚያህል ትልቅ ህመም ይኖራል ብዬ አላስብም አድቅሮ ያንን ሰው ህይወቴ ነው ብለው እየኖሩ ከዛ ሰው በድንገት መለየት እና ያንን ሰው እረስቶ መኖር በጣም ይከብዳል። በሩታዬ ባልፈርድም ግን እራስ ማጥፋት መፍትሄ ነው ብዬ አላስብም። ህይወት እኮ ይቀጥላል እሷን ባትመለስም እኛ ግን እየኖርን ነው ምክንያቱም ህይወት ይቀጥላል የሞተ ግን ይጎዳል ጊዜ ቢፈጅ ነው እንጂ እማያገግም ሀዘን የለም ማን ከሞተው ጋር ተቀብሮ ያውቃል ። ብዙ ተስፋ እሚያስቆርጡ መፈጠራችንን እንድንጠላው እሚያደርጉ ብዙ ለጭንቀት እና እራሳችንን እንድናጠፋ እሚገፋፉ አላፍ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ ሀዘን እና ጭንቀት እድሜ አይገድበውም ብዙ ሰው በዚ እድሜያችሁ የምን ሀዘን ነው ምኑን አውቃችሁት ነው ይላሉ ግን ሀዘን ሁሉም ጋር አለ ትንሹም ትልቁም ቢሆን የራሱ የሆነ እሚያስታምመው በሽታ አለው። ግን ቢሆንም ሞቼ ከራሴ ውጪ እምጎዳው ማንም የለም። ብኖር ግን ምናልባትም ለመኖር ሁለተኛ ዕድል ላገኝ እችላለው አጋጣሚ አቀጣሪ ነው ዛሬ የጨለመው ምናልባትም ሊነጋ የተሻለ ሊመጣ ነው ብሎ ማሰቡ አይከፋም። ሁላችንም ይከፋናል እናዝናለን እንታመማለን እንጨነቃለን ተስፋ እንቆርጣለን ግን እኮ ይሄ ሁሉም ያለው እኛ ስለኖርን ነው ግን ብንሞትስ ይፕምስጥ መጫወቻ መሆን ነው ትርፉ በተጎዳን ሰዓት ይህንን ሁሉ ማሰቡ ቀላል አይሆንም ኧረ ጭራሹኑ ትዝ አይለንም ግን ቀድሞ እራስን በዚህ መልኩ ማሳመን በተጎዳን ሰዓት አላስፈላጊ እርምጃን ከመውሰድ ይቆጥበናል። ሩታን ካጣናት በኋላ የድሮዋም ሳቢ አብራ ተቀበረች። አፈቀርኩሽ የሚሏትን ወንዶች ሁሉ አጋጣሚውን እየጠበቀች መጉዳቷት ለእህቷ የተበቀለችላት ይህል እንዲሰማት ያደርጋታል። ከመቃብር ስፍራው እንደምንም አፅናንቼ ይዧት ከወጣን በኋላ ወደ እኛ ቤት እንሂድ አልኳት እና እሺ ብላኝ ያመጣሁላትን ጃኬት ደርባ መንግፕድ ጀመርን በመሀል እሚበላ ነገር ገስተን እንግባ እማማ ከዚህ ሰዓት በኋላ እራት ለመስራት ከሚጨነቁ ብላኝ ሰፈር ወዳለ አንድ ሆቴል ገብተን ለራት እሚሆን ነገር ቴካዌ አስደርገን ወደ ቤት ገባን እማዬ ሳቢን ስታያት በጣም ነበር ደስ ያለት ወደ እኔ ክፍል ከገባን በኋላ እማዬም አብራን መታ አልጋው ላይ ቁጭ ስትል ሳቢ እግሯ ላይ ድፍት ብላ አለቀሰች እማዬም በእናት አንጀቷ ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች ፀጉሯን ደባበሰቻት ከዛም ቀስ እያለች እሷም ተረጋግታ ሳቢንም ለማረጋጋት ሞከረች እና የድሮውን እያስታወሰችን መጫወት ጀመርን ሳቢዬም ጭንቀቷ ቀለል ሲላት ያመጣነውን እራት አቅርበን በላን እና ፊልም እያየን በዛው እንቅልፍ ወሰደን ጠዋት ላይ የአማን መቶ እኔን ብቻ ቀሰቀሰኝ ስራ መሄድ ስለነበረብኝ ። እኔም ቁርሴን በላልቼ ወደ ስራ ወጣሁኝ ያው ሳሪ እምትሄድባት ስለሌላት ትንሽ ትረፍ ብለን ዝም አልናት። እንደተለመደው ማይለፍ መታጠፊያው ጋር ጠበቀኝ እና ወደ ስራ አብረን ሄድን እንደተለመደው ዛሬም በጣም አምሮበታል እሱም መዋቡን አያቆም እኔም ማድነቄን አልተው። ስራ ቦታ ካደረሰኝ በኋላ የሆነ ፌስታል ሰቶኝ ወጣ ከሄደ በኋላ ፌስታሉን ፈትቼ ሳየው ውስጡ እሚያምር ቀይ ቀሚስ ከጥቁር ሂል ጫማ ጋር እና አብሮ ትንሽዬ ወረቀት ነበር ቀሚሱ ቀልብ ይሰርቃል ጫማውም እንደዛው ተቻኩዬ ወረቁቱ ላይ የተፃፈውን ማንበብ ጀመርኩ...
" የጫማ ቁጥርሽን ባላውቀውም ግን ይሆንሻል ብዬ በገመትኩት ቁጥር ገዝቻለው ቀሚሱ ግን እንደሚሆንሽ አልጠራጠርም። ማታ እራት ከእኔ ጋር ነሽ አስራ ሁለት ሰዓት ላይ መውጫው ጋር ጠብቂኝ" ይላል ወረቀቱ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ግን ውስጤን ደስ አለኝ ስራ ቦታ መሆኔን ዘንግቼው ተነስቼ እየዘለልኩኝ ስጮህ ነበር። በኋላ ዙሪያዬን ስመለከት ለካ መስሪያ ቤት ነኝ ሰዎቹ በግርምት ያዩኛል እንደማፈር ብዬ ወንበሬ ላይ ተቀመጥኩኝ ደስታዬ ወደር አጣ ፊቴ ሁሉ በፈገግታ ተሞላ ግን ለምን ይሄን ያህል ደስታ ተሰማኝ ? ብቻ ምንም ይሁን ምን ሰዓቱ እስኪደርስና እስካገኘው ቸኩያለው።

ወደ ረፋድ አምስት ሰዓት ላይ ለሳቢ ደወልኩላት
"ሳቢዬ"
"ወዬ ቃልዬ ጠዋት ትተሽኝ ወጣሻ"
"ትንሽ እረፊ ብዬ እኮ ነው። በደንብ ተኛሽ ?"
"ቀላል አረፍኩኝ ገና አሁን መነሳቴ እኮ ነው እሱንም እቴቴ ቀስቅሳኝ" እማዬን እቴቴ ብለው ነው ሁሉም ጓደኞቼ እሚጠሯት...
"እና ቁርስሽን ገና አልበላሽማ ?"
"ይኸው እያቀረበች ነው አብረን ልንበላ"
"በቃ ብዪና ትንሽ ተንቀሳቀሽበት"
"ግድ ይላል። ቁርሴን ልብላበት በኋላ እደውላለው"
"ሆዳም ብዪ በቃ ቻው" ብያት ስልኩ ተዘጋ። ትንሽም ቢሆን ስለተረጋጋች ደስ ብሎኛል። የተለያየ ሰው እየመጣ እያስተናገድኩኝ ምሳ ሰዓት ሲደርስ እዛው ህንፃው ላይ ያለው ካፌ ውስጥ ትንሽ ነገር ቀማምሼ ወደ ስራ ተመለስኩኝ። ትዝ ሲለኝ ግን ፀጉሬን ሹሩባ እንደተሰራሁኝ ነበር መቼስ ይሄን የመሰለ የራት ልብስ ለብሼ በሹሩባ አልሄድም የግድ መሰራት አለብኝ ብዬ ከሱቅ ቦርሳዬንና ልብስ እና ጫማ የያዘውን ፌስታል ይዤ ሱቁን ዘጋግቼ ወደ ታች ወረድኩኝ። በፊት እዚሁ ሜክሲኮ አካባቢ ሩታ እያለች ሶስታችን ሄደን የምንሰራበት ፀጉር ቤት ትዝ አለኝ እና ወደዛ ሄድኩኝም ስገባ ቤቱ ውስጡ ተቀይሯል ከበፊቱ በተሻለ መልኩ ሰርተውታል ፤ እኛ በምንመጣበት ጊዜ የነበሩት ሰዎችም ተቀይረዋል። ግን አሪፍ ቤት ነው አዘውትረን ከሰፈር ድረስ ስንት ፀጉር ቤት ትተን ነበር እዚህ መተን የምንሰራውም ከ ሶስት አመት በኋላ እግሬ ረገጠ። ወረፋ ስለነበረ የፀጉር ወረፋዬ እስኪደርስ የእጅና የእግር ጥፍሮቼን ተሰራሁኝ። ከሁለት ሰዓት ቆይታ በኋላ ፀጉሬን እና ጥፍሮቼን ተሰርቼ እዛው እነሱ ልብሳቸውን እሚቀይሩበት ክፍል ውስጥ ገብቼ በስጦታ መልክ የተበረከተልኝን የራት ልብስ ለብሼ ጫማዬን ተጫምቼ ወጣሁኝ። ሲያዩኝ እዛው ያሉ ሰዎች በጣም እንዳማረብኝ እየነገሩኝ መልካም ምሽት ተመኙልኝ። ደስ አለኝ ማይለፍ እጠብቅሻለው ያለኝ ታክሲ መያዣው ጋር ስለነበር እዛ ድረስ እንዲህ ለብሼ መሄዱ ነፃነት ስላል ሰጠኝ ከፀጉር ቤቱ አጠገብ ካለው ካፌ ተቀመጥኩና ያለሁበትን ቴክስት አደረኩለት። ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ አንድ ትልቅ መኪና ከካፌው ፊት ለፊት መቶ ቆመ እየጠበኩኝ የነበረው መኪና የማለፍን ስለነበር የመኪናው ትልቀት እንጂ ከሚኪናው የወረደውን ሰው አላስተዋልኩም። ወዲያው ስልኬ ላይ መልዕክት ተላከልኝ ማይለፍ ነበር ሳነበው ግን ግራ ተጋባሁኝ እሱን ስለነበር የጠበኩት በጥቂጡም እንደ መፍራት አደረገኝ....."ፊት ለፊትሽ የቆመው መኪና ውስጥ ጊቢ ልጁ እኔ ጋር ይዞሽ ይመጣል" ይል ነበር መልዕክቱ። ቀና ስል ከመኪናው አጠገብ ጥቁር በጥቁር የለበስ ልጅ ቆሟል። በእጁ ወደ መኪናው እንድገባ በምልክት አሳየኝ...


ይቀጥላል....

ቀጣዩ ክፍል እንዲለቀቅ እያነበባችሁ አስተያየታችሁን አድርሱኝ

ለአስተያየት- @Yetomah_Bot



✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯
@Ketbeb_Mender
@Ketbeb_Mender
✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯



tgoop.com/Ketbeb_mender/3482
Create:
Last Update:

​​​​​​​​​​​♥️♡:。.。 እዮሪካ 。.。:♡♥️

ክፍል ፲፮

ደራሲ - አብላካት



ለሶስት ሳምንት ያህል ወደ ጊቢ አልሄድንም ነበር ለሁላችንም ትልቅ የልብ ስብራት ሆኖ ለረጅም ጊዜ ቆይቷል ዛሬን እንደዛው ነው አልዳነም ባሰብናት ቁጥር ያመናል። ለሳቢ ደግሞ ከሞትም በላይ ሞት ነው እናቷን ያጣች ያህል ነው ለሷ ቁስሉ ። ሁሌም ታስታውሳታለች በሳቅ እና በውሸት ፈግግታ እንደረሳቻት ታስመስላለች እንጂ ለደቂቃ እንኳን ከሀሳቧ ርቃ አታውቅም።

ፍቅርን እምፈራው ለዚህ ነው ማጣትን እሚያህል ትልቅ ህመም ይኖራል ብዬ አላስብም አድቅሮ ያንን ሰው ህይወቴ ነው ብለው እየኖሩ ከዛ ሰው በድንገት መለየት እና ያንን ሰው እረስቶ መኖር በጣም ይከብዳል። በሩታዬ ባልፈርድም ግን እራስ ማጥፋት መፍትሄ ነው ብዬ አላስብም። ህይወት እኮ ይቀጥላል እሷን ባትመለስም እኛ ግን እየኖርን ነው ምክንያቱም ህይወት ይቀጥላል የሞተ ግን ይጎዳል ጊዜ ቢፈጅ ነው እንጂ እማያገግም ሀዘን የለም ማን ከሞተው ጋር ተቀብሮ ያውቃል ። ብዙ ተስፋ እሚያስቆርጡ መፈጠራችንን እንድንጠላው እሚያደርጉ ብዙ ለጭንቀት እና እራሳችንን እንድናጠፋ እሚገፋፉ አላፍ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ ሀዘን እና ጭንቀት እድሜ አይገድበውም ብዙ ሰው በዚ እድሜያችሁ የምን ሀዘን ነው ምኑን አውቃችሁት ነው ይላሉ ግን ሀዘን ሁሉም ጋር አለ ትንሹም ትልቁም ቢሆን የራሱ የሆነ እሚያስታምመው በሽታ አለው። ግን ቢሆንም ሞቼ ከራሴ ውጪ እምጎዳው ማንም የለም። ብኖር ግን ምናልባትም ለመኖር ሁለተኛ ዕድል ላገኝ እችላለው አጋጣሚ አቀጣሪ ነው ዛሬ የጨለመው ምናልባትም ሊነጋ የተሻለ ሊመጣ ነው ብሎ ማሰቡ አይከፋም። ሁላችንም ይከፋናል እናዝናለን እንታመማለን እንጨነቃለን ተስፋ እንቆርጣለን ግን እኮ ይሄ ሁሉም ያለው እኛ ስለኖርን ነው ግን ብንሞትስ ይፕምስጥ መጫወቻ መሆን ነው ትርፉ በተጎዳን ሰዓት ይህንን ሁሉ ማሰቡ ቀላል አይሆንም ኧረ ጭራሹኑ ትዝ አይለንም ግን ቀድሞ እራስን በዚህ መልኩ ማሳመን በተጎዳን ሰዓት አላስፈላጊ እርምጃን ከመውሰድ ይቆጥበናል። ሩታን ካጣናት በኋላ የድሮዋም ሳቢ አብራ ተቀበረች። አፈቀርኩሽ የሚሏትን ወንዶች ሁሉ አጋጣሚውን እየጠበቀች መጉዳቷት ለእህቷ የተበቀለችላት ይህል እንዲሰማት ያደርጋታል። ከመቃብር ስፍራው እንደምንም አፅናንቼ ይዧት ከወጣን በኋላ ወደ እኛ ቤት እንሂድ አልኳት እና እሺ ብላኝ ያመጣሁላትን ጃኬት ደርባ መንግፕድ ጀመርን በመሀል እሚበላ ነገር ገስተን እንግባ እማማ ከዚህ ሰዓት በኋላ እራት ለመስራት ከሚጨነቁ ብላኝ ሰፈር ወዳለ አንድ ሆቴል ገብተን ለራት እሚሆን ነገር ቴካዌ አስደርገን ወደ ቤት ገባን እማዬ ሳቢን ስታያት በጣም ነበር ደስ ያለት ወደ እኔ ክፍል ከገባን በኋላ እማዬም አብራን መታ አልጋው ላይ ቁጭ ስትል ሳቢ እግሯ ላይ ድፍት ብላ አለቀሰች እማዬም በእናት አንጀቷ ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች ፀጉሯን ደባበሰቻት ከዛም ቀስ እያለች እሷም ተረጋግታ ሳቢንም ለማረጋጋት ሞከረች እና የድሮውን እያስታወሰችን መጫወት ጀመርን ሳቢዬም ጭንቀቷ ቀለል ሲላት ያመጣነውን እራት አቅርበን በላን እና ፊልም እያየን በዛው እንቅልፍ ወሰደን ጠዋት ላይ የአማን መቶ እኔን ብቻ ቀሰቀሰኝ ስራ መሄድ ስለነበረብኝ ። እኔም ቁርሴን በላልቼ ወደ ስራ ወጣሁኝ ያው ሳሪ እምትሄድባት ስለሌላት ትንሽ ትረፍ ብለን ዝም አልናት። እንደተለመደው ማይለፍ መታጠፊያው ጋር ጠበቀኝ እና ወደ ስራ አብረን ሄድን እንደተለመደው ዛሬም በጣም አምሮበታል እሱም መዋቡን አያቆም እኔም ማድነቄን አልተው። ስራ ቦታ ካደረሰኝ በኋላ የሆነ ፌስታል ሰቶኝ ወጣ ከሄደ በኋላ ፌስታሉን ፈትቼ ሳየው ውስጡ እሚያምር ቀይ ቀሚስ ከጥቁር ሂል ጫማ ጋር እና አብሮ ትንሽዬ ወረቀት ነበር ቀሚሱ ቀልብ ይሰርቃል ጫማውም እንደዛው ተቻኩዬ ወረቁቱ ላይ የተፃፈውን ማንበብ ጀመርኩ...
" የጫማ ቁጥርሽን ባላውቀውም ግን ይሆንሻል ብዬ በገመትኩት ቁጥር ገዝቻለው ቀሚሱ ግን እንደሚሆንሽ አልጠራጠርም። ማታ እራት ከእኔ ጋር ነሽ አስራ ሁለት ሰዓት ላይ መውጫው ጋር ጠብቂኝ" ይላል ወረቀቱ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ግን ውስጤን ደስ አለኝ ስራ ቦታ መሆኔን ዘንግቼው ተነስቼ እየዘለልኩኝ ስጮህ ነበር። በኋላ ዙሪያዬን ስመለከት ለካ መስሪያ ቤት ነኝ ሰዎቹ በግርምት ያዩኛል እንደማፈር ብዬ ወንበሬ ላይ ተቀመጥኩኝ ደስታዬ ወደር አጣ ፊቴ ሁሉ በፈገግታ ተሞላ ግን ለምን ይሄን ያህል ደስታ ተሰማኝ ? ብቻ ምንም ይሁን ምን ሰዓቱ እስኪደርስና እስካገኘው ቸኩያለው።

ወደ ረፋድ አምስት ሰዓት ላይ ለሳቢ ደወልኩላት
"ሳቢዬ"
"ወዬ ቃልዬ ጠዋት ትተሽኝ ወጣሻ"
"ትንሽ እረፊ ብዬ እኮ ነው። በደንብ ተኛሽ ?"
"ቀላል አረፍኩኝ ገና አሁን መነሳቴ እኮ ነው እሱንም እቴቴ ቀስቅሳኝ" እማዬን እቴቴ ብለው ነው ሁሉም ጓደኞቼ እሚጠሯት...
"እና ቁርስሽን ገና አልበላሽማ ?"
"ይኸው እያቀረበች ነው አብረን ልንበላ"
"በቃ ብዪና ትንሽ ተንቀሳቀሽበት"
"ግድ ይላል። ቁርሴን ልብላበት በኋላ እደውላለው"
"ሆዳም ብዪ በቃ ቻው" ብያት ስልኩ ተዘጋ። ትንሽም ቢሆን ስለተረጋጋች ደስ ብሎኛል። የተለያየ ሰው እየመጣ እያስተናገድኩኝ ምሳ ሰዓት ሲደርስ እዛው ህንፃው ላይ ያለው ካፌ ውስጥ ትንሽ ነገር ቀማምሼ ወደ ስራ ተመለስኩኝ። ትዝ ሲለኝ ግን ፀጉሬን ሹሩባ እንደተሰራሁኝ ነበር መቼስ ይሄን የመሰለ የራት ልብስ ለብሼ በሹሩባ አልሄድም የግድ መሰራት አለብኝ ብዬ ከሱቅ ቦርሳዬንና ልብስ እና ጫማ የያዘውን ፌስታል ይዤ ሱቁን ዘጋግቼ ወደ ታች ወረድኩኝ። በፊት እዚሁ ሜክሲኮ አካባቢ ሩታ እያለች ሶስታችን ሄደን የምንሰራበት ፀጉር ቤት ትዝ አለኝ እና ወደዛ ሄድኩኝም ስገባ ቤቱ ውስጡ ተቀይሯል ከበፊቱ በተሻለ መልኩ ሰርተውታል ፤ እኛ በምንመጣበት ጊዜ የነበሩት ሰዎችም ተቀይረዋል። ግን አሪፍ ቤት ነው አዘውትረን ከሰፈር ድረስ ስንት ፀጉር ቤት ትተን ነበር እዚህ መተን የምንሰራውም ከ ሶስት አመት በኋላ እግሬ ረገጠ። ወረፋ ስለነበረ የፀጉር ወረፋዬ እስኪደርስ የእጅና የእግር ጥፍሮቼን ተሰራሁኝ። ከሁለት ሰዓት ቆይታ በኋላ ፀጉሬን እና ጥፍሮቼን ተሰርቼ እዛው እነሱ ልብሳቸውን እሚቀይሩበት ክፍል ውስጥ ገብቼ በስጦታ መልክ የተበረከተልኝን የራት ልብስ ለብሼ ጫማዬን ተጫምቼ ወጣሁኝ። ሲያዩኝ እዛው ያሉ ሰዎች በጣም እንዳማረብኝ እየነገሩኝ መልካም ምሽት ተመኙልኝ። ደስ አለኝ ማይለፍ እጠብቅሻለው ያለኝ ታክሲ መያዣው ጋር ስለነበር እዛ ድረስ እንዲህ ለብሼ መሄዱ ነፃነት ስላል ሰጠኝ ከፀጉር ቤቱ አጠገብ ካለው ካፌ ተቀመጥኩና ያለሁበትን ቴክስት አደረኩለት። ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ አንድ ትልቅ መኪና ከካፌው ፊት ለፊት መቶ ቆመ እየጠበኩኝ የነበረው መኪና የማለፍን ስለነበር የመኪናው ትልቀት እንጂ ከሚኪናው የወረደውን ሰው አላስተዋልኩም። ወዲያው ስልኬ ላይ መልዕክት ተላከልኝ ማይለፍ ነበር ሳነበው ግን ግራ ተጋባሁኝ እሱን ስለነበር የጠበኩት በጥቂጡም እንደ መፍራት አደረገኝ....."ፊት ለፊትሽ የቆመው መኪና ውስጥ ጊቢ ልጁ እኔ ጋር ይዞሽ ይመጣል" ይል ነበር መልዕክቱ። ቀና ስል ከመኪናው አጠገብ ጥቁር በጥቁር የለበስ ልጅ ቆሟል። በእጁ ወደ መኪናው እንድገባ በምልክት አሳየኝ...


ይቀጥላል....

ቀጣዩ ክፍል እንዲለቀቅ እያነበባችሁ አስተያየታችሁን አድርሱኝ

ለአስተያየት- @Yetomah_Bot



✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯
@Ketbeb_Mender
@Ketbeb_Mender
✯┄┅┅✿❀♥️❀✿┅┅┄✯

BY የብዕር ጠብታ✍📒📖


Share with your friend now:
tgoop.com/Ketbeb_mender/3482

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Read now Private channels are only accessible to subscribers and don’t appear in public searches. To join a private channel, you need to receive a link from the owner (administrator). A private channel is an excellent solution for companies and teams. You can also use this type of channel to write down personal notes, reflections, etc. By the way, you can make your private channel public at any moment. Deputy District Judge Peter Hui sentenced computer technician Ng Man-ho on Thursday, a month after the 27-year-old, who ran a Telegram group called SUCK Channel, was found guilty of seven charges of conspiring to incite others to commit illegal acts during the 2019 extradition bill protests and subsequent months. Hashtags “[The defendant] could not shift his criminal liability,” Hui said.
from us


Telegram የብዕር ጠብታ✍📒📖
FROM American