KETBEB_MENDER Telegram 3473
​​​​​♥️♡:。.。 እዮሪካ 。.。:♡♥️

ክፍል ፲፪

ደራሲ - አብላካት


አጎንብሼ እያለቀስኩኝ ሳለሁ ድንገት የክፍሌ በር ተንኳኳ የአማን ነበረ..

"ግባ" አልኩት እምባዬን እየጠራረኩኝ
"አስቀየሙሽ አይደል ?"
"ኧረ በፍፁም እኔ እህትህን ደሞ ማነው ደፍሮ እሚናገራት" አልኩት ፈገግ እያልኩኝ
"አትስሚያቸው እሺ እነሱ እኮ ያንቺን ጥሩነት ስለማያውቁ ነው እንጂ ምን አይነት ሰው እንደሆንሽ ሲገባቸው እራሳቸው መተው ይቅርታ ይጠይቁሻል ደሞ መልካምነት እኮ ብዙ ዋጋ ያስከፍላል አንቺ ማለት ልክ እንደ ወርቅ ነሽ ወርቅ በእሳት እንደሚፈተነው አንቺንም ፈጣሪ በነሱ ሊፈትንሽ ነው ስለዚህ ጠንካራ ሆነሽ ፈተናሽን በጥሩ ውጤት አጠናቂ።" አለኝ እውነት ለመናገር አነጋገሩ በጣም ነው ያስገረመኝ አስራ አምስት አመት እንኳን ካልሞላው ልጅ እንዲህ አይነት ንግግር መስማት ትንሽ ያስደነግጣል ሆኖም ግን ንግግሩ ፈገግም አስብሎኛል አስገርሞኛልም። ይህ ህፃን ልጅ ይሄንን ያህል አርቆ ማሰብ ከተቻለው እኛ ተማርን አደግን የምንለው ምን ሆነን ነው የዚህን ያህል አዕምሮአችን የቀጨጨው ? አመስግኜው የስራ ሰዓት ስለደረሰ ትላንት ለእነ ወይዘሮ አለምነሽ እሰጣለው ያልኩት ትዝ ሲለኝ ከሳጥኔ ውስጥ የባንክ ቡኬንና ያስቀመጥኩትን አንድ ሺህ ብር ይዤ ወጣሁኝ ፤ የታክሲ ግርግሩ ለጉድ ነው እንደምንም ተጋፍቼ ገባሁኝ። ወደራሴ ስመለስ የማይለፍ አለመደወልና ወደ ሰፈር አለመምጣቱ ትዝ አለኝ ማታ ቻው ሳልለው እንቅልፍ ስለወሰደኝ ተቀይሞኝ ይሆን እንዴ ግራ ገባኝ "ወራጅ የለም ?" ሲል ከገባሁበት ሀሳብ ብንን አልኩኝ ለካ መውረጃዬ ጋር ደርሼ ነበረ ፈጠን ብዬ ከታክሲው ወረድኩኝና ወደ ህንፃው ገባሁኝ ሀሳቤ ግን አሁንም እሱ ጋር ነበረ ወደ ኢንተርኔት ቤቱ ስጠጋ ፊት ለፊት መቶ አንድ ሰው ድቅን አለ ሀሳብ ውስጥ ስለነበርኩኝ ይቅርታ ብዬው ሱቁን መክፈት ጀመርኩኝ....
"ላግዝሽ ?" ይማውቀው ድምፅ ነበር ፊቴን ዘወር ሳደርግ ማይለፍ ነበር ሮጥ ብዬ ሄጄ ተጠመጠምኩበት አቀፈኝ የሆነ የማላውቀው ስሜት ተሰማኝ ሰውነቴን ሁሉ ነዘረኝ ጠረኑ የማላውቀው አለም ውስጥ ይዞኝ ነጎደ እፎይታ ተሰማኝ ወዲያው ግን "ምን እየሆንሽ ነው ቃል" የሚል ድምፅ ከራሴ ውስጥ ተሰማኝ እና ሸሸሁት

"ምነው ?" አለኝ
"እይ ምንም ሱቁን ልክፈት" ብዬው ፊቴን አዞርኩኝ እጄ ይንቀጠቀጥ ጀመረ
"ቆይ እኔ ላግዝሽ" ብሎ ከፋፈተልኝ እና ወደ ውስጥ ገባን
"ቴክስቱን ቅርብ ሰዓት ነው ያየሁት ይቅርታ ያልመጣሁት ደግሞ አስቸኳይ ስራ መቶ እኔ መፈረም ያለብኝ ነገር ስለነበረ ነው ለሱም ይቅርታ " አለኝ
"ችግር የለውም ዋናው ደህና መሆንህ ነው"
"በቃ ትንሽ ስራ አለኝ ሰላም ልበልሽ ብዬ ነው በኋላ እመጣለው"
"እሺ መልካም ስራ" አልኩት እና ሄደ። ድንጋጤው አለቀቀኝም ነበር ወንድን ልጅ እንደዚህ አቅፌም ነክቼም አላውቅም ምን ያስብ ይሆን መቼስ አይንቀኝም አይደል ደሞስ አቀፍኩት እንጂ ምን አደረኩኝ እያልኩ ከራሴ ጋር ሙግት ገጠምኩኝ። ግን አልክድም ደስ ብሎኛል እንኳንም አቀፍኩት ሳይታወቀኝ እየሳኩኝ ነበረ "ብቻ እሚያስገለፍጥ ምን ነገር ተገኘ ?" የቤቱ ባለቤት ነበር
"ኧረ ምንም ይቅርታ እንዴት ነህ ?"
"በሰላም ከሆነ እሺ ደህና ነኝ ስራ እንዴት እንደሆነ ልጠይቅሽ ብዬ ነው"
"ስራ በጣም አሪፍ እየሄደ ነው"
"ጥሩ በቃ እላይኛው ፎቅ እማገኘው ሰው አለ መልካም ስራ ይሁንልሽ"
"አመሰግናለሁ።"

ምክንያቱን ባላውቀውም ዛሬ ድክምክም ብሎኛል ቀኑም የተሸከምኩት ያህል ነው የከበደኝ።ያሉትን ከስተመሮች አስተናግጄ ስጨርስ ሱቁን ዘጋግቼ ወረድኩኝ። ከህንፃው ወጥቼ ትንሽ እንደተራመድኩኝ ማይለፍን መኪና ማቆሚያው ጋር አየሁትና ወደ እሱ ሄድኩኝ
"እዚህ ደግሞ ምን ትሰሪያለሽ ?" አለኝ መስኮቱን ዝቅ እያደረገ
"ብር ላወጣ ፈልጌ ባንክ ቤት እየፈለኩኝ። አንተስ ስራ የለህም እንዴ"
"እኔ እንኳን ሰው አጊንቼ እየተመለስኩኝ ነበር ሳይሽ ነው የቆምኩት። በቃ ግቢና ልሸኝሽ" አለኝ .....ደክሞኝ ስለነበር አልተግደረደርኩም
"እሺ" ብዬው ወደ ውስጥ ገባሁኝ እና መንገድ ጀመርን...ባንክ ቤት ስንደርስ ወርጄ ለወይዘሮ አለምነሽ እሰጣለው ያልኩትን ብር አወጣሁኝ ። ስመለስ ...
"አሁንስ ወዴት ነሽ ?" አለኝ
"ከተመቸህ ሰፈር አድርሰኝ ካልሆነም ታክሲ እይዛለው"
"አይ ችግር የለውም ግቢ" አለኝ።
"ምነው ዛሬ በጊዜ ?"
"አይ ለሰው እማደርሰው እቃ ስላለ ነው"
"እና ወደ ስራ ካልተመለስሽ እቃውን አድርሰሽ ስትመለሺ ላግኝሽ ?"
"እሺ ስራህን ስትጨርስ ደውልልኝ እስከዛው እቤት ገብቼ እረፍት አደርጋለው"
"እሺ እደውላለው። ይኽው ሰፈርሽም ደርሰሻል"
"አመሰግናለው በጣም ቻው" ብዬው ወደ ወይዘሮ አለምነሽ ቤት ሄድኩኝ። በሩን የከፈቱልኝ እሳቸው ነበሩ...
"ሰላም ዋሉ እማማ ?"
"የኔ ልጅ መጣሽ እንዴ ? ፈጣሪ ይመስገን ቸር ውያለው ውደ ውስጥ ግቢ" አሉኝና በሩን ዘግተው ወድ ቤት ገባን አቶ መኩሪያም ሶፋቸው ላይ ቁጭ ብለው መፅሀፍ እያነበቡ ነበር
"ሰላም ዋሉ ጋሽ መኩሪያ ?"
"ቸሩ መድሀኔአለም ይመስገን። አረፍ በይ"
የያዝኩትን አምስት ሺህ ብር አውጥቼ ለወይዘሮ አለምነሽ ሰጠኋቸው።
"የምን ብር ነው ቃልዬ ?"
"እማማ፣ጋሼ ምንቴ ነው ዛሬ ጠዋት የላከላችሁ"
"የኔው ልጅ ምንተስሞት ነው ?" አሉኝ አቶ መኩሪያ ቀጠል አድርገው
"አዎ ጋሼ ምንቴ ነው።"
"እንደው አይኑን እያየው ባመሰግነው ምን ነበር" አሉ ወይዘሮ አለምነሽ
"ችግር የለውም አሁን እደውልለታለው ብዬ ስልኬን በማውጣት ደወልኩለት ትላንት ያየሁት ምንቴና ዛሬ እያየሁት ያለሁት ተለያዩብኝ ያንን አሸባሪ ያስመሰለውን ፂሙን ያጎፈረውን ፂሙን እርግፍ አድርጎ ተቆርጦት ነበር። ከሀገሩ ሲወጣ የነበረው መልኩ በጥቂቱም ቢሆን ተመልሶ ሳየው ሳይታወቀኝ እምባዬ ወረደ። እሱም እናትና አባቱን ሲያይ እምባው ለጉድ ይወርድ ጀመረ እነሱም እሱን እያዩ ስቅስቅ ብለው አለቀሱ። ይሄ ሞልቶ እማይሞላ ህይወት የስንቱን ቤት አጨለመ የስንቱን ልጅነት እና ወጣትነት ነጠቀ። የስደትን አስከፊነት በምን ቋንቋ በየትኛው ሰው ቢነገረን ይሆን ገብቶን በሀገራችን ሰርቶ መለወጥን ልማድ እምናደርገው ትንሽ ሲከፋን ጎድሎ ስናየው በአይናችን ውል በአእምሯችን ሽው እሚለው ስደት እሚሉት ሰይጣናዊ ሀሳብ ነው። ብቻ እሱ ፈጣሪ በቃ ይበለን። አውርተውት ሲጨርሱ ለላከላቸው ገንዘብ አመስግነው ተሰናብተውት ስልኩ ተዘጋ እኔንም እማይጠገብ ምርቃታቸውን አሽረውኝ ወደ ቤቴ ሄድኩኝ። እቤት ስገባ ማንም አልነበረም ወደ ክፍሌ ገብቼ ጋደም አልኩና ለምንቴ ደወልኩለት እስካሁን እያለቀሰ ነበር....
"ቃልዬ ምን ብዬ ላመስግንሽ በምንድነው ውለታሽን እምከፍለው ?"
"እኔ እና አንተ እኮ ጓደኛሞች አብሮ አደጎች ነን የምን ምስጋና ነው ዋናው አንተም እነሱም መደሰታችሁ ነው ?"
"ፈጣሪ ያክብርልኝ። ግን እንዴት ነሽ ?"
"አሜን። ደህና ነኝ እኔ አንተ ግን እምሮብሀል ትላንት እኮ በልጅነታችን እነ እማማ እንደ ማስፈራሪያ ይጠቀሙት የነበረውን ግዙፍ ሰውዬ መስለህ ነበር" ብዬ ትንሽም ቢሆን ላስቀው ሞከርኩኝ
"ክትክት ብሎ እየሳቀ አሁን አገኘሽኝ" አለኝ እና ብዙ ነገር አውርተን ስልኩ ተዘጋ።


መኖር ትርጉም እሚኖረው ከራስ አልፎ ሌላው ላይ ደስታን መፍጠር ሲቻለው ነው። ሞልቶኝ ሳይሆን ጎድሎኝ እነሱን ከጭንቀት ስለገላገልኩኝ እፎይታ ተሰምቶኛል።



ይቀጥላል........


ቀጣዩ ክፍል እንዲለቀቅ እያነበባችሁ አስተያየታችሁን አድርሱኝ


ለአስተያየት @Yetomah_Bot



tgoop.com/Ketbeb_mender/3473
Create:
Last Update:

​​​​​♥️♡:。.。 እዮሪካ 。.。:♡♥️

ክፍል ፲፪

ደራሲ - አብላካት


አጎንብሼ እያለቀስኩኝ ሳለሁ ድንገት የክፍሌ በር ተንኳኳ የአማን ነበረ..

"ግባ" አልኩት እምባዬን እየጠራረኩኝ
"አስቀየሙሽ አይደል ?"
"ኧረ በፍፁም እኔ እህትህን ደሞ ማነው ደፍሮ እሚናገራት" አልኩት ፈገግ እያልኩኝ
"አትስሚያቸው እሺ እነሱ እኮ ያንቺን ጥሩነት ስለማያውቁ ነው እንጂ ምን አይነት ሰው እንደሆንሽ ሲገባቸው እራሳቸው መተው ይቅርታ ይጠይቁሻል ደሞ መልካምነት እኮ ብዙ ዋጋ ያስከፍላል አንቺ ማለት ልክ እንደ ወርቅ ነሽ ወርቅ በእሳት እንደሚፈተነው አንቺንም ፈጣሪ በነሱ ሊፈትንሽ ነው ስለዚህ ጠንካራ ሆነሽ ፈተናሽን በጥሩ ውጤት አጠናቂ።" አለኝ እውነት ለመናገር አነጋገሩ በጣም ነው ያስገረመኝ አስራ አምስት አመት እንኳን ካልሞላው ልጅ እንዲህ አይነት ንግግር መስማት ትንሽ ያስደነግጣል ሆኖም ግን ንግግሩ ፈገግም አስብሎኛል አስገርሞኛልም። ይህ ህፃን ልጅ ይሄንን ያህል አርቆ ማሰብ ከተቻለው እኛ ተማርን አደግን የምንለው ምን ሆነን ነው የዚህን ያህል አዕምሮአችን የቀጨጨው ? አመስግኜው የስራ ሰዓት ስለደረሰ ትላንት ለእነ ወይዘሮ አለምነሽ እሰጣለው ያልኩት ትዝ ሲለኝ ከሳጥኔ ውስጥ የባንክ ቡኬንና ያስቀመጥኩትን አንድ ሺህ ብር ይዤ ወጣሁኝ ፤ የታክሲ ግርግሩ ለጉድ ነው እንደምንም ተጋፍቼ ገባሁኝ። ወደራሴ ስመለስ የማይለፍ አለመደወልና ወደ ሰፈር አለመምጣቱ ትዝ አለኝ ማታ ቻው ሳልለው እንቅልፍ ስለወሰደኝ ተቀይሞኝ ይሆን እንዴ ግራ ገባኝ "ወራጅ የለም ?" ሲል ከገባሁበት ሀሳብ ብንን አልኩኝ ለካ መውረጃዬ ጋር ደርሼ ነበረ ፈጠን ብዬ ከታክሲው ወረድኩኝና ወደ ህንፃው ገባሁኝ ሀሳቤ ግን አሁንም እሱ ጋር ነበረ ወደ ኢንተርኔት ቤቱ ስጠጋ ፊት ለፊት መቶ አንድ ሰው ድቅን አለ ሀሳብ ውስጥ ስለነበርኩኝ ይቅርታ ብዬው ሱቁን መክፈት ጀመርኩኝ....
"ላግዝሽ ?" ይማውቀው ድምፅ ነበር ፊቴን ዘወር ሳደርግ ማይለፍ ነበር ሮጥ ብዬ ሄጄ ተጠመጠምኩበት አቀፈኝ የሆነ የማላውቀው ስሜት ተሰማኝ ሰውነቴን ሁሉ ነዘረኝ ጠረኑ የማላውቀው አለም ውስጥ ይዞኝ ነጎደ እፎይታ ተሰማኝ ወዲያው ግን "ምን እየሆንሽ ነው ቃል" የሚል ድምፅ ከራሴ ውስጥ ተሰማኝ እና ሸሸሁት

"ምነው ?" አለኝ
"እይ ምንም ሱቁን ልክፈት" ብዬው ፊቴን አዞርኩኝ እጄ ይንቀጠቀጥ ጀመረ
"ቆይ እኔ ላግዝሽ" ብሎ ከፋፈተልኝ እና ወደ ውስጥ ገባን
"ቴክስቱን ቅርብ ሰዓት ነው ያየሁት ይቅርታ ያልመጣሁት ደግሞ አስቸኳይ ስራ መቶ እኔ መፈረም ያለብኝ ነገር ስለነበረ ነው ለሱም ይቅርታ " አለኝ
"ችግር የለውም ዋናው ደህና መሆንህ ነው"
"በቃ ትንሽ ስራ አለኝ ሰላም ልበልሽ ብዬ ነው በኋላ እመጣለው"
"እሺ መልካም ስራ" አልኩት እና ሄደ። ድንጋጤው አለቀቀኝም ነበር ወንድን ልጅ እንደዚህ አቅፌም ነክቼም አላውቅም ምን ያስብ ይሆን መቼስ አይንቀኝም አይደል ደሞስ አቀፍኩት እንጂ ምን አደረኩኝ እያልኩ ከራሴ ጋር ሙግት ገጠምኩኝ። ግን አልክድም ደስ ብሎኛል እንኳንም አቀፍኩት ሳይታወቀኝ እየሳኩኝ ነበረ "ብቻ እሚያስገለፍጥ ምን ነገር ተገኘ ?" የቤቱ ባለቤት ነበር
"ኧረ ምንም ይቅርታ እንዴት ነህ ?"
"በሰላም ከሆነ እሺ ደህና ነኝ ስራ እንዴት እንደሆነ ልጠይቅሽ ብዬ ነው"
"ስራ በጣም አሪፍ እየሄደ ነው"
"ጥሩ በቃ እላይኛው ፎቅ እማገኘው ሰው አለ መልካም ስራ ይሁንልሽ"
"አመሰግናለሁ።"

ምክንያቱን ባላውቀውም ዛሬ ድክምክም ብሎኛል ቀኑም የተሸከምኩት ያህል ነው የከበደኝ።ያሉትን ከስተመሮች አስተናግጄ ስጨርስ ሱቁን ዘጋግቼ ወረድኩኝ። ከህንፃው ወጥቼ ትንሽ እንደተራመድኩኝ ማይለፍን መኪና ማቆሚያው ጋር አየሁትና ወደ እሱ ሄድኩኝ
"እዚህ ደግሞ ምን ትሰሪያለሽ ?" አለኝ መስኮቱን ዝቅ እያደረገ
"ብር ላወጣ ፈልጌ ባንክ ቤት እየፈለኩኝ። አንተስ ስራ የለህም እንዴ"
"እኔ እንኳን ሰው አጊንቼ እየተመለስኩኝ ነበር ሳይሽ ነው የቆምኩት። በቃ ግቢና ልሸኝሽ" አለኝ .....ደክሞኝ ስለነበር አልተግደረደርኩም
"እሺ" ብዬው ወደ ውስጥ ገባሁኝ እና መንገድ ጀመርን...ባንክ ቤት ስንደርስ ወርጄ ለወይዘሮ አለምነሽ እሰጣለው ያልኩትን ብር አወጣሁኝ ። ስመለስ ...
"አሁንስ ወዴት ነሽ ?" አለኝ
"ከተመቸህ ሰፈር አድርሰኝ ካልሆነም ታክሲ እይዛለው"
"አይ ችግር የለውም ግቢ" አለኝ።
"ምነው ዛሬ በጊዜ ?"
"አይ ለሰው እማደርሰው እቃ ስላለ ነው"
"እና ወደ ስራ ካልተመለስሽ እቃውን አድርሰሽ ስትመለሺ ላግኝሽ ?"
"እሺ ስራህን ስትጨርስ ደውልልኝ እስከዛው እቤት ገብቼ እረፍት አደርጋለው"
"እሺ እደውላለው። ይኽው ሰፈርሽም ደርሰሻል"
"አመሰግናለው በጣም ቻው" ብዬው ወደ ወይዘሮ አለምነሽ ቤት ሄድኩኝ። በሩን የከፈቱልኝ እሳቸው ነበሩ...
"ሰላም ዋሉ እማማ ?"
"የኔ ልጅ መጣሽ እንዴ ? ፈጣሪ ይመስገን ቸር ውያለው ውደ ውስጥ ግቢ" አሉኝና በሩን ዘግተው ወድ ቤት ገባን አቶ መኩሪያም ሶፋቸው ላይ ቁጭ ብለው መፅሀፍ እያነበቡ ነበር
"ሰላም ዋሉ ጋሽ መኩሪያ ?"
"ቸሩ መድሀኔአለም ይመስገን። አረፍ በይ"
የያዝኩትን አምስት ሺህ ብር አውጥቼ ለወይዘሮ አለምነሽ ሰጠኋቸው።
"የምን ብር ነው ቃልዬ ?"
"እማማ፣ጋሼ ምንቴ ነው ዛሬ ጠዋት የላከላችሁ"
"የኔው ልጅ ምንተስሞት ነው ?" አሉኝ አቶ መኩሪያ ቀጠል አድርገው
"አዎ ጋሼ ምንቴ ነው።"
"እንደው አይኑን እያየው ባመሰግነው ምን ነበር" አሉ ወይዘሮ አለምነሽ
"ችግር የለውም አሁን እደውልለታለው ብዬ ስልኬን በማውጣት ደወልኩለት ትላንት ያየሁት ምንቴና ዛሬ እያየሁት ያለሁት ተለያዩብኝ ያንን አሸባሪ ያስመሰለውን ፂሙን ያጎፈረውን ፂሙን እርግፍ አድርጎ ተቆርጦት ነበር። ከሀገሩ ሲወጣ የነበረው መልኩ በጥቂቱም ቢሆን ተመልሶ ሳየው ሳይታወቀኝ እምባዬ ወረደ። እሱም እናትና አባቱን ሲያይ እምባው ለጉድ ይወርድ ጀመረ እነሱም እሱን እያዩ ስቅስቅ ብለው አለቀሱ። ይሄ ሞልቶ እማይሞላ ህይወት የስንቱን ቤት አጨለመ የስንቱን ልጅነት እና ወጣትነት ነጠቀ። የስደትን አስከፊነት በምን ቋንቋ በየትኛው ሰው ቢነገረን ይሆን ገብቶን በሀገራችን ሰርቶ መለወጥን ልማድ እምናደርገው ትንሽ ሲከፋን ጎድሎ ስናየው በአይናችን ውል በአእምሯችን ሽው እሚለው ስደት እሚሉት ሰይጣናዊ ሀሳብ ነው። ብቻ እሱ ፈጣሪ በቃ ይበለን። አውርተውት ሲጨርሱ ለላከላቸው ገንዘብ አመስግነው ተሰናብተውት ስልኩ ተዘጋ እኔንም እማይጠገብ ምርቃታቸውን አሽረውኝ ወደ ቤቴ ሄድኩኝ። እቤት ስገባ ማንም አልነበረም ወደ ክፍሌ ገብቼ ጋደም አልኩና ለምንቴ ደወልኩለት እስካሁን እያለቀሰ ነበር....
"ቃልዬ ምን ብዬ ላመስግንሽ በምንድነው ውለታሽን እምከፍለው ?"
"እኔ እና አንተ እኮ ጓደኛሞች አብሮ አደጎች ነን የምን ምስጋና ነው ዋናው አንተም እነሱም መደሰታችሁ ነው ?"
"ፈጣሪ ያክብርልኝ። ግን እንዴት ነሽ ?"
"አሜን። ደህና ነኝ እኔ አንተ ግን እምሮብሀል ትላንት እኮ በልጅነታችን እነ እማማ እንደ ማስፈራሪያ ይጠቀሙት የነበረውን ግዙፍ ሰውዬ መስለህ ነበር" ብዬ ትንሽም ቢሆን ላስቀው ሞከርኩኝ
"ክትክት ብሎ እየሳቀ አሁን አገኘሽኝ" አለኝ እና ብዙ ነገር አውርተን ስልኩ ተዘጋ።


መኖር ትርጉም እሚኖረው ከራስ አልፎ ሌላው ላይ ደስታን መፍጠር ሲቻለው ነው። ሞልቶኝ ሳይሆን ጎድሎኝ እነሱን ከጭንቀት ስለገላገልኩኝ እፎይታ ተሰምቶኛል።



ይቀጥላል........


ቀጣዩ ክፍል እንዲለቀቅ እያነበባችሁ አስተያየታችሁን አድርሱኝ


ለአስተያየት @Yetomah_Bot

BY የብዕር ጠብታ✍📒📖




Share with your friend now:
tgoop.com/Ketbeb_mender/3473

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

So far, more than a dozen different members have contributed to the group, posting voice notes of themselves screaming, yelling, groaning, and wailing in various pitches and rhythms. Add the logo from your device. Adjust the visible area of your image. Congratulations! Now your Telegram channel has a face Click “Save”.! Clear How to Create a Private or Public Channel on Telegram? It’s yet another bloodbath on Satoshi Street. As of press time, Bitcoin (BTC) and the broader cryptocurrency market have corrected another 10 percent amid a massive sell-off. Ethereum (EHT) is down a staggering 15 percent moving close to $1,000, down more than 42 percent on the weekly chart.
from us


Telegram የብዕር ጠብታ✍📒📖
FROM American