Telegram Web
....እኔም አልሀምዱሊላህ ደህና ነኝ አልኩት
.......እሱም ቀለበቴን እያየ ነዋል ልታገቢ ነዉ እንዴ ??? አለኝ
....እኔም...አዎ ኢንሻ አላህ በቅርብ ቀን አስቢያለሁ አልኩት
ሚፍታህም :- ሽማግሌ ተልኳል ወይስ አልተላከም??? አለኝ
....እኔም ገና አልተላከም በቅርብ ቀን ይልካል አልኩት
....... ነዋል ወላሂ ብየ ነዉ የምነግርሽ በጣም ነዉ የምወድሽ ..አንቺ የሌላ ስትሆኝ ማየት አልችልም... ወላሂ ሁሌም ህልሜ አንቺ ጋር ተጋብቶ መኖር ነዉ፡፡

አንድ ነገር እንድታቂልኝ እፈልጋለሁ ... አንቺ የሌላ ሰዉ ሁነሽ ..ትዳር ከሌላ ሰዉ ጋር ብትመሰርች ፀቤ ከአንቺ ወይም ከአገባሽ ሰዉ አይደለም..ፀቤ ከፈጣሪ ከአላህ ጋር ነዉ..... ለምን ብትይ ሀጅ ባደረኩበት ጊዜ አላህን ከሁሉም ሀጃየ አስበልጬ ስጠይቀዉ ስለምነዉ የነበረዉ....አንቺ የኔ እኔድትሆኝ ነበር... አላህን ስለምነዉ የነበረዉ ከአንቺ ልጅ መዉለድ እስከ እለተ ሞቴ አንቺ ጋር አብሮ መኖር ነዉ አለኝ
....ይሄን ሲለኝ አብረዉ ጓደኞቹ ነበሩ... ይሄን እየተናገረ ሚፍታህ እምባ ነዉ የቀረዉ፡፡
ቁርጤን ንገሪኝ ቁርጤን ንገሪኝ ..የሌላ ስትሆኝ ማየት አልፈልግም የኔ ብቻ ሁኜ እባክሽ እያለ ይለምነኛል
........እኔም በጣም ተወዛገብኩ ግራ ገባኝ...ሚፍታህ ዉሳኔየን በስልክ ደዉየ አሳዉቅሀለሁ አልኩት

ከሱቁ ወጥቼ ወደ ቤቴ እየተመለስኩ ነዉ... ልቤ ተሸበረ ...ዉሳኔ መወሰን አልቻልኩም ...የማልክደዉ እዉነት ቢኖረዉ ሚፍታህ በጣም እወደዉ ነበር ለመጋባት ድረስ ደርሰን ቤተሰብ ለቤተሰብ ተጠይቆ እሺ ተብሎ ጨርሰን እንደነበር በአለፈዉ ታሪክ ላይ ታስታዉሳላችሁ...ሚፍታህ አንቺን ማግባት ነዉ የምፈልገዉ ሲለኝ የማላቀዉ ስሜት ከየት መጣ የማልለዉ ወረረኝ ...እሱ ጋር ያሳለፍኳቸዉ የፍቅር ገጠመኞች ጊዚያቶች ፊቴ ላይ እንደመስተዋት መልሶ ያሳየኛል

  ከዛ እንደዚህ እየተጨናነኩ የምወስነዉ ግራ ገብቶኝ ሁለት ልብ ሁኜ ለካሊድ ደወልኩለት፡፡
  ሰላምታ ከተለዋወጥን ----- ካሊድ እኔን ብታጣኝ የሌላ ብሆን ምን ይፈጠራል ብለህ ታስባለህ ? እኔን አጥተህ ብትኖር ምን ይሰማሀል ??? ብየ ጠየኩት
......ካሊዶ ለካ እንደሌሎቹ ወንዶች አይደለም የመለሰልኝ መልስ አስገራሚ ነበር እንደዚህ አለኝ ... #አንቺን_ማጣት_ምን_እንደሆነ_ነዋል_የኔ_ባትሆን_የሚለዉን_በጭራሽ_ማሰብም_መገመትም_አልፈልግም ፡፡ አንቺ የሌላ ስትሆኝ እንዲህ እሆናለሁ ብየ ምሳሌ እንኳ መስጠት አልፈልግም ... ነዋል እኔን ለመቀለድ ብለሽ እንኳን እንደዚህ አይነት ጥያቄ ዳግመኛ እንዳትጠይቂኝ...አለኝ

ወላሂ ጥፋቱ የኔ ነዉ.... ሶስት አመት በትዕግስት ጠብቆ ከነማንነቴ ተቀብሎኝ...ገና ሚፍታህ አንቺን ነዉ ማግባት የምፈልገዉ ሲለኝ ልቤ ወላዉሎ ካሊድን ይሄን ጥያቄ መጠየቄ ከደወልኩ ቡሀላ ብቻየን አፈርኩኝ..

ዉየ ሳላድር ወዳዉኑ ለሚፍታህ Text ላኩለት ...እንደዚህ አልኩት>>>>> ሚፍታህ ከአሁን ቡሀላ ወደ ሆላ መመለስ አንችልም ትናንት ከትናንትናዉ ጋር አብሮ አልፏል ..በርግጥ የማልዋሸህ በፊት እወድህ ነበር ያደግሞ በጊዜዉ አልፏል ...፡፡ አሁን ላይ መጉዳት የማልፈልገዉ የምወደዉ የሚወደኝ እሱን አጥቼ እሱም እኔን አጥቶ መኖር የማይችል እኔም እሱን አጥቼ መኖር አልችል ሁኜ ልቤ ዉስጥ ያስቀመኩት እሱም ያስቀመጠኝ ሰዉ አለ ብየ ላኩለት......
 

  ሚፍታህ ጋር በዚሁ message አንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተለያየን...አንድ የወንድ ልጅ ድክመት አለች እየወደዱ ማግባት እየፈለጉ የተሻለ አገኛለሁ ብሎ ከኔ ዉጭ አታገባም ትጠብቀኛለች ብለዉ እያሰቡ ነገር ግን እሷን የሚወዳት አግኝታ ልታገባ ስትል ትጠብቀኛለች ብሎ ያሰበዉ እንደ አዲስ ከእንቅልፉ ሲባንን ይስተዋላል፡፡ ታዳ ሚፍታህም አገባሻለሁ ብሎ ሽማግሌ ልኮ አጭቶኝ ጥፋቴን ሳላቀዉ አመታት ያህል ረስቶኝ ነገር ግን ላገባ ነዉ ስለዉ እንደገና በቅናት ተንገብግቦ አንቺን ነዉ የማገባዉ ማለቱ አግባብ አይደለም..ሴትነት የእናት ነት የእህትነት ደረጃ እንጂ የምርጫ የቅርጫ ለትዳር መወዳደሪያ አይደለችምና፡፡



ካሊድ ከ 15 ቀን ቡሀላ ቅዳሜ ሽማግሌ እልካለሁ አለኝ
....እኔም መርሀባ ብየ ተስማማሁኝ፡፡


እነዚህ አስራምስት ቀናት ለሁለታችንም እርቃልብናለች ቀን በቀን በተደዋወልን ቁጥር ይሄ ቀን ቀረን እያልን ሲቀርብ ሲቀርብ ..ሶስትም አልፎ ሁለት ቀናት ቀረን ፡ ነገ ቅዳሜ ሁኖ ዛሬ ጁምአ ላይ ደርሰናል  
......ከዛም ጁምአ ቀን የኔ ፈተና መቼም አይለቅ ...ያልተሳበ ይሆናል ብየ ያልገመትኩት በራልኝ ስል የጨለመብኝ የሒወት አዙሪት በባሰ መልኩ አይኑን አፍጥጦ መጣብኝ...እኔ ስፈጠር እንዳትደሰቺ የተባልኩ ይመስል....ያላሰብኩት ነገር ተፈጠረ የሸይጧን መሰናክል ሁሌም ቢሆን አይጠፋም.....



#ክፍል 2⃣6⃣

ይ...............ቀ.............
..........ጥ...........ላ...............ል

Join👇👇👇
💐_⭐️💐⭐️___💐
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ሀያ ስድስት 2⃣6⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ

ከዛም ጁምአ ቀን ያልተሳበ ይሆናል ብየ በራልኝ ስል የጨለመብኝ የሒወት አዙሪት በባሰ መልኩ አይኑን አፍጥጦ መጣብኝ...እኔ ስፈጠር እንዳትደሰቺ የተባልኩ ይመስል...ያላሰብኩት ነገር ተፈጠረ የሸይጧን መሰናክል ሁሌም ቢሆን አይጠፋም ፡፡
 
     ቅዳሜ ካሊድ ሽማግሌ ሊልክ ጁምአ እናቴ ከአባቴ ጋር ተጣልታ ዘመዶቿ ጋር ሄደች ፡፡ በእኛ ሰፈር የሚገኙ ሽማግሌ ተሰብስበዉ ሁለቱም እንዲታረቁ ቢለመኑ ..አንታረቅም የኛ መጨረሻዉ ፍች ብቻ ነዉ መፍትሄዉ ብለዉ በጭራሽ ሊስማማሙ አልቻሉም፡፡
...እኔም ለካሊድ ደዉየ ቤተሰቦቼ እንደተጣሉ እና ሽማግሌዎቹን እንዳይልክ ነገርኩት

ጊዜያቶች እየነገዱ ነዉ....አባቴ ሌላ ሴት ለማግባት እየፈለገ ነዉ...እናቴም ፍርድ ቤት ከሳ ንበረቱን ተካፍላ ከቤት ይዉጣልኝ እያለች ነዉ፡፡ ነገሩ በጣም ሲጠና ...አባቴ ለልጆቼ ብየ እታረቃለሁ ቢልም ..እናቴ ግን በጭራሽ አልታረቅም ብላ አሻፈረኝ አለች.... የሰፈር ታዋቂ ሸሆች... የመስጊድ ኢማማችን ሳይቀር ቢለምኗት እምቢ አለች፡፡


እኔ እና ካሊድ ለመጋባት 100% ጨርሰናል ሁለታችንም ለትዳር ልባችን ቢንጠለጠልም ግን እናት እና አባቴ ተለያይተዉ በሚኖሩበት ቤት በተበታተነ ቤተሰብ ለማን ሽምግልና ይላካል??? ዱአ ከማድረግ ዉጭ ምንም አማራጭ የለም...

   ደግሞ አዲስ ነገር የማይፈጠር የለም ...ሚፍታህ ደወለልኝ እና ...ነዋል አንቺን ማግባት ነዉ የምፈልገዉ ነዋል ከልቤ ነዉ እወድሻለሁ ሽማግሌ ልልክ ነዉ አለኝ
......እኔም ሚፍታህ አሁን መቼም ቢሆን የአንተ መሆን አልችልም ለሁሉም ጊዜ አለዉ አንተም በጊዜህ እኔን ትተህኛል...አሁን እኔም ልቤ የሌላ ነዉ ...ተስፋ ቁረጥ እንደፈለክ የምከፍተዉ የምዘጋዉ የቤትህ በር አይደለሁም አልኩት ቆጣ ብየ
 

አይጠቅምም ብለዉ የጣሉት እቃ ሌላ ሰዉ አንስቶ ሲጠቀምበት ምነዉ ባልጣልኩት ብለዉ ይቆጩ የለ... ..ሚፍታህ እኔን ትቶኝ ላገባ ፕሮሰስ ላይ መሆኔን ሲያቅ ..እንደገና ካላገባሁ ሙቼ እገኛለሁ..ሽማግሌ ልልክ ነዉ እያለ አሁንም ተስፋ ያልቆረኩ ይመስለዋል..ሴት ልጅ ስወድ ወደደች ነዉ ከጠላች ደግሞ በእሷ መስፈርት ሁሉንም አሟልተህ ብትገኝ ከጠላችህ መቼም በልቧ መግባት እንደማችል እንደነ ሚፍታህ ያሉ ወንዶች ዘንግተዉታል... መቼም ካሊድን በማንም የማልቀይረዉ እዉነተኛ የትዳር አጋሬ ነዉ፡፡

✿✿✿ ምርጥ ጓደኛየ መፍቱሀም ተመርቃ የግል ሆስፒታል ዉስጥ ገብታ እየሰራች ነዉ..

✿✿✿ብሩክታይትም ቢላል የሚባል የወንዶች የጀመአ አባል ብሩክታይት ዲነል ኢስላምን አስተምራለሁ ቁርአን አቀራታለሁ ብሎ መፍቱሀን እና እኔን አማከረን ...እኛም ብሩክታይትን አማከርናት ... ቢላልን ታቀዋለች በትዳር ጥያቄዉ ተስማማች .. ስሟንም በራሷ ፍቃድ ብሩክ ታይት ሳይሆን ራዉዳ ነኝ ብላ ከቢላል ጋር እህል እና ዉሀቸዉ ገጥሞ በትዳር አለም አብረዉ መኖር ጀምረዋል፡፡

✿✿✿ ካስታወሳችሁ በአለፉት ክፍል ናርዶስ(በአጎቷ እና በአባቷ ጓደኛ በልጅነቷ የተደፈረችዉ) በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህግ ተምራ ተመርቃለች

✿✿✿ የሱፍ (ለሚፍታህ ነዋልን ዳረኝ ብሎ ስልኩን የሰጠዉ) እሱ ደግሞ ሚፍታህ ጋር አንዴ ተጣልተዉ...ነገሩ ከብዶ ፓሊስ ጣቢያ ድረስ ሂደዉ ነበር በሽምግልና ታረቁ ቢባል የሱፍ በጭራሽ አልታረቅም እበቀለዋለሁ እንዳለ ቂም እንደያዘ .. በመጨረሻም የሱፍም ቤተሰቦች እነሱዉ አምጥተዉ እሱም ጎጆ ቀልሶ እየኖረ ነዉ፡፡

✿✿ ሚፍታህም በንዴት ይሁን አስቦበት አላቅም እኔ ላገባ ነዉ ከአሁን ቡሀላ አንተ እና እኔ አንድ ላይ መሆን አንችልም ካልኩት ቡሀላ ...ብዙም ሳይቆይ አንድ ወር ባልመላ ቀናት ዉስጥ እኔን አናዳታለሁ ብሎ አስቦ ይሁን ..ትዳሩን አምኖበት ይሆን...ነዋልን ልቀደማት ብል አስቦም ይሆን አላቅም እሱም የትዳር ጎጆዉን ቀልሷል

✿✿✿ ካሊድም የቤት እቃ እያማሏ ነዉ ፡፡ እኔም ነገሮች እስከሚስተካከሉ ብየ ጅማ የሚገኝ የመንግስት ሆስፒታል በተመረኩበት ፊልድ ማገልገል ጀመርኩኝ...አልሀምዱሊላህ አባቴ ያሰበዉ ደረጃ ደረስኩኝ ..

ሆስፒታል መቼም የብዙ ሰዉ ብሶት መቀበያ አይደል....እንደ እኔ በልጅነታቸዉ የተደፈሩ ሴቶች በጣም ብዙ ገጥመዉኛል ..ልጆችን በማፅናናት ከጎናቸዉ በመሆን እነሱን ማገዝ የአእምሮ ጭንቀት እንዳይዛቸዉ የስነልቦና አገልግሎት መስጠት የዘወትር ስራየ ነዉ. .በተጨማሪም በፍቅር ለተጎዱ ሴቶች ...እንደ እኔ በቤተሰብ ፍቅር ዉጭ ለአደጉ ልጆች..በተለያዩ ጉዳዮች ዲፕሬሽን(በአእምሮው ጭንቀት) የተጎዱ የዱንያ የአኼራ እህቶቼን ከጎናቸዉ በመሆን እነሱን መንከባከብ በሀሳባቸዉ ተረድቼ መፍትሄ ስሰጥ ለኔ የዉስጥ ደስታ ሰላም ይሰጠኛል፡፡ የሰዉ ልጅ ደስታዉ ብቻዉን መቀየሩ ደስታን ማግኘቱ ሳይሆን በእሱ የተነሳ ስንት ሰዉ መቀየሩ መደሰቱ ታላቅ ደስታ ነዉ..

የሚገርማችሁ እዛዉ ጤና ጣቢያ በሴት ልጆች ላይ የሚደርሰዉ በደል ሳይ የኔ ምን አለበት አልሀምዱሊላህ ያልኩባቸዉ ብዙ ቀናቶች አሉ..
እኔ ከገጠመኝ በታላቅ ወንድሞቻቸዉ የተደፈሩ ልጆች ገጥሞኛል..በተዘዋዋሪ ጭካኔ የበዛበት ዘመን መሆኑ ያሳዝናል ብዙ ህፃናት በአባቶቻቸዉ ተደፍረዉ የሚመጡ ብዙ ልጆች ገጥመዉኛል፡፡እኔ አንድ ሴት ነኝ ከጎኔ ማን አለ?? ሁሉም ከጎኔ ባይሆኔም ግን እንደ እኔ ተብድለዉ በሆዳቸዉ አፍነዉ የሚኖሩ ቤት ይቁጠረዉ,..... መቼ ድረስ ነዉ የሴት ልጅ እምባ መዉረድ የሚያቆመዉ ??? ሁሌም በልቤ ቁጭት አለ ታዳ ምን ያደርጋል አንድ ሰዉ አስቦ አንድ በሬ ስቦ አይሆንም...እኔ የራሴን ታሪክ በፁሁፍ ዘረገፍኩት እንጂ ብዙ ሴቶች አሁን ድረስ ዛሬ ከነገ ይሻላል ቢሉም ግን የብስ እየጨለመ የሚሰቃዩ ለቁጥር አይገባም. ... እንደ እኔ እንቅልፍ አጥተዉ የሚኖሩ ሴቶች አይናገሩ ሰሚ የለ ....ለማን ይነገር?? በእንባ ጎርፍ ለፈጣሪ አቤት ከማለት በቀር ፡፡ ስለሆነም ወንዶች እባካችሁ ለሴት ልጆች እዘኑ ይሄ ሁሉ ለቅሶየ ስቃየ በኔ በራሴ የመጣ አይደለም በጨካኝ ስሜቱን መቆጣጠር በአቃተዉ ወንድ የተፈጠረብኝ በልጅነት መደፈር ነዉ ፈጣሪ ሁላችንንም ልቦና ይስጠን

ቢያንስ ከ5 ወራት ቡሀላ በስንት ሽምግልና አልሀምዱሊላህ እናት እና አባቴ ተስማምተዉ መልሰዉ አብረዉ መኖር ጀመሩ ..

እናት እና አባቴ ታርቀዉ ብዙም ቀን ሳይቆዩ በቤተሰብ የትዳር ጥያቄ መጣ ...
ማታ ላይ ሳሎን ቁጭ ብለን አባቴም፡- ነዋል ይሄ መታለፍ መመለስ የሌለበት ትዳር ነዉ..እኛ እንተማመንበታለን ጥሩ ሰዉ አላህን ፈሪ ነዉ ፡፡ነዋል እኔ አባትሽ ለምወድሽ ልጄ መጥፎ ምርጫ እንደማልመርጥ ታቂያለሽ .. አሁን የመጣዉን ትዳር እንድታገቢ ምርጫየ ነዉ እሺ በይኝ አለኝ
....... አባቴ አንተ የተናገርከዉ ልክ ነህ ...ነገር ግን እኔ ትልቅ ልጅ ነኝ የሚጠቅመኝን የሚጎዳኝን ለይቻለሁ ..እኔን በደስታ ሊያኖረኝ የሚችል የኔ የራሴ የምለዉ አንድ ሰዉ አለኝ አልኩት
.....አባቴም ማን ነዉ ልጁ እኔ አቀዋለሁ??አለኝ
....እኔም አዎ ታቀዋለህ ካሊድ ነዉ ብየ ... እሱን እንዲያቁት በምልክት ሰፈሩን ቤተሰቡን ስነግራቸዉ እናቴም አባቴም አወቁት👇👇👇
......እናቴም፡- በጭራሽ ካሊድ ጋር እንድትጋቡ አልፈቅድልሽም ... ለምን ብትይ ሹፌር አይታመንም ሴቶችን ሲያጀዝቡ አይደል እንዴ የሚዉሉት ??..እኔ በካሊድ አልስማማም አይኔ እያየ ለካሊድ አልድርሽም አለችኝ
...እናቴ ጋር በዚሁ ምሽት ዉርክብ ብጥብጥ ተፈጠረ በጭራሽ መግባባት አልቻልንም ... አባቴም በኔ ምርጫ ጣልቃ ላለመግባት ፈልጎ...ነዋል ትዳር ቀልድ አይደለም ተረጋግተሽ እሰቢበት አለኝ..እናቴ ደግሞ ሹፌር መቼም ቢሆን አታገቢም እያለች እየደነፋች ነዉ፡፡

ለነገሩ በእናቴም አልፈርድም አሁን ዘመን ላይ ያሉ ሹፌሮች አላማቸዉን የረሱ ከትርፉ ላይፉ እያሉ ራሳቸዉን እና ሞኝ ተላላ ሴቶችን የሚታልሉ ብዙ ፡ናቸዉ ...ደግሞ በተዘዋዋሪ ሹፌሮችን የሚያስቸግሩ ሴቶችንም እያስተዋልን ነዉ...

ጃፓን መኪናዉን ስትሰራዉ መሪዉ ላይ ሹፌር ሹፌር የሚያስብል የቀበረችበት ያለ ነዉ የሚመስለዉ...ግን ከሁሉ የሚያናደኝ በነዚህ ጋጠወጥ ሹፌሮች እንደ ካሊድ ያሉ ምርጥ ለሴት ልጆች የሚያስቡ ሹፌሮች አብረዉ መወቀሳቸዉ እና መሰደባቸዉ አሳዛኝ ነዉ

★★★ አንዲት አበባል አለች ጭልፊት የወደቀ ስጋን እንጂ በቁሙ ያልተገፈፈ በግን እንደማይነካ የታወቀ ነዉ፡፡
እህቴ ሆይ ሒወትሽ እንደ በግ ነጋዴ በግ ተራ እንደወሰደዉ በግ እጣ ፈንታ አትወስኝ...አንድ በግ ሊሸጥ ሲል በጣም ብዙ ገዥ አገላብጦ ሽንጡን እየያየዘ ስጋ አለዉ የለዉም እያለ ያየዋል..ከተቻለ ዛሬ አለዛም ነገ ቀይም ከነገ ወዳ ሲገላበጥ ቢቆይም ይሸጣል.. አንቺም እንደዚህ እንደሚሸጥ በግ አላማቸዉን ከዘነጉ ተኩላ ወንዶች እያገላበጡ እየታየሽ አለፈች ወደቀች እየተባልሽ በየመንገዱ ስትሄጅ ግምገማ አትቀረቢ...መስሪያ ቤት ግምገማዉ በወር ወይ በአመት ነዉ...አንቺ ግን ኮስሞቲክስ እየተጠቀምሽ ቀን በቀን የወንዶች መሳለቂያ አትሁኝ...ሒወትሽ ሊሸጥ ገበያ የሄደ በግ አይነት እንዲሆን በራስሽ ጊዜ አትፍቀጅ...
ብዙዎች ሴቶች በመጥፎ ጓደኛ ግፊት እንየሚበላሹ የማይካድ ሀቅ ነዉ
ግን እህቴ ሴት ልጅ ብዙ ነገሮችን ተቋቁማ ወደ ትዳር አለም ትገባለች ያንን እንዴት ነዉ ፈተናዉን ማለፍ ያለብሽ?? ..ሴቶች ተማሪዎች አብረሽ መደበኛ ትምህርት ስትማሪ ሁሉንም ትምህርት ሂሳብ እንግሊዝ አማረኛ civics ወ.ዘ.ተ ዉጤትሽ ጥሩ ሊሆን ይችላል ግን ከትምህርት ዉጤትሽ በላይ የአንቺ የሂወት ዉጤትሽ ጓደኞችሽ ሲሆኑ  የጓደኞችሽ ግፊት አንቺን ወደ ማፈልጊዉ ወደ ማታቂዉ አለም ትገቢያለሽ ...ስምንት ማትሪክ ስትፈተኝ ጥሩ ዉጤት አመጣሽ ወደ ዘጠኝ አለፍሽ ከዛስ አስርም አለ ማትሪክን ስትወስጅ ከዘጠኝ እና ከአስረኛ ክፍል ከበፊቱ ምን ለዉጥ አለኝ?? ቂርአት ላይ ጥሩ ነኝ ወይስ መጥፎ የሴት ጓደኞች አሉኝ ወይስ በሀራም ከወንድ ጋር ሀራም የሆነ የማይጨረስ ፍቅር ጀምሪያለሁ ወይ?? ወ.ዘ.ተ የሚለዉን አንቺ እራስሽ ለራስሽ ጥያቄዉን አቅርበሽ መመለስ አለብሽ
ከዛስ ማትሪክ ተፈተንኩ ትምህርቴን ካለፍኩኝ 11 ክፍል ስገባ አላማየ ምን መሆን አለበት ከ10 ብወድቅስ ? ብለሽ እሰቢ

እህቶቼ አራት አመት ፈተናዉን ማለፍ መታገስ ከቻላችሁ የወደፊት የእናንተ ከአላህ ጋር የአርባ አመት ፕላናችሁ መስተካከል ይችላል ፡፡ ግን አራት አመት ላይ ግን የምትሸወዱ ከሆነ በሀራም ከአጂ ነቢ ጋር ግንኙነት ከጀመራችሁ ለአንድቀን ለዛዉም 20 ደቂቃ ለማይሞላ ስሜት የ40 አመታት ፕላናችሁን ታበላሻላችሁ ማለት ነዉ፡፡ እነዚህ አራት አመታት እነማን ናቸዉ ካልን ከዘጠነኛ ክፍል እስከ 12 ክፍል ያሉትን አመታት ፋየር ኤጅ ሁሉም አለሁ አለሁ ከሰዉ በላይ ነኝ የሚባልበት እድሜ ነዉ ስለሆነም እነዚህ የትምህርት አመታት የወደፊት ሂወታችሁ ወሳኝ ናቸዉ፡፡ University በምገቡበት ጊዜ እናንተ የአራት አመቱ ምርት ዉጤት ናችሁ አራት አመቱን በመጃጃል ያሳለፍሽ ከሆነ university ከቤተሰብ ቁጥጥር ዉጭ ነሽ ለቤተሰብም ለሀገርም ለአንቺም አጠቅሚ ትበላሻለሽ ..


...በዚህ ሁኔታ እኔ ካሊድን አገባለሁ እናቴም በጭራሽ አታገቢም እያለች ቀን በቀን ስንጨቃጨቅ የአላህ ነገር ይሄ covid 19 መጥቶ ከችክችክ ከንዝንዝ አረፍኩኝ...የሰዉ ወሬ ስለዚሁ በሽታ ሲሆን እናቴም ጋር ስለትዳሩ ሁኔታ ማዉራት አቆምን

..የእኔ እናት አላማዋ እኔን ከሀብታም ጋር በትልቅ ድግስ በሰፊ ሰርግ እኔን ለመዳር ነበር ....የነብዩ ሰ.ዐ.ወ የሰርግ ስነ-ስርአት እና ሱና ነገሮች ለመተግበር የመጣ ይመስላል ኮረና ደሀም ሀብታምም ሰርጉ ልዩነት የለዉም ሁሉም በኒካህ ኢስራፍ ከሆነ ከሰርግ ወጭ ገላግሏል፡፡

ቤተሰቦቼም በአባቴ ጥረት ብዙ ነገሮችን ከጠየቀኝ ቡሀላ አባቴ ተስማምቶ እናቴም ባይዋጥላትም በግድ ካሊድን እንዳገባ ፈቀደችልኝ .. ከካሊድ የ 2012 ረመዷን ሊደርስ የተወሰኑ ቀናት ሲቀረዉ በትንሹ ሰርግ ተደግሶ ...እኔም ጂልባቤን ለብሼ መፍቱሀ እና ሩቅያም ሌሎች የዓሊይ መስጂድ የጀመአ ጓደኞቼም በጅልባባቸዉ አምረዉ ድምቅ ብለዉ ከጎኔ ሁነዋል...አልሀምዲሊላህ እኔም ከምወደዉ ከሚወደኝ ካሊድ ጋር የሰርጌ ቀን ደረሰ...

ካሊድም የተወሰኑ ጓደኞቹን ይዞ መጥቶ ኒካህ ታስሮ ያሁሉ ጉፍ መከራ ለቅሶ አልፎ የሚስትነት ማዕረጉን ይዤ ከእናት አባቶቼ ተለይቼ  ካሊድ ጋር የትዳርን ህይወት አሀዱ ብለን ልንጀምር እሱ ጋር የሰርጌ ምሽት ሄድኩ ፡፡ ሁለታችንንም የናፈቀንን የሀላል ጨዋታ ምሽት ላይ ጀምረናል፡፡ ሰርግ ላይ ሲጨፈር የምሰማት ግጥም ትዝ አለችኝ እስኪ ልበላት
ካሊድ ምሽት 3:45 ታላቅ ፍልሚያ አለዉ
እኛም አላገዝነዉ አላህ ይሁነዉ
የሚሏት ግጥም እዉነትም ከፕሪሚየርሊግ የበለጠ ፍልሚያ ነዉ ...

ከዚህ ፍልሚያ ቡሀላ ያልተጠበቀ ይሆናል ብላችሁ የማጠብቁት ነገር እኔም ማመን ያልቻልኩት ነገር ተፈጠረ ...

#የመጨረሻዉ_ክፍል

ይ.......ቀ.........ጥ............ላ................ል

          `·. www.tgoop.com/Islam_and_Science
www.tgoop.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል#የመጨረሻዉ_ክፍል

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ


ከዚህ ፍልሚያ ቡሀላ ያልተጠበቀ ይሆናል ብላችሁ የማጠብቁት ነገር ተፈጠረ

እኔም ካሊድም ገረመን አላህ ምን ይሳነዋል..
ይገርማል አረ በጣም ይገርማል ገርሞም ይገርማል የሚገርም ነዉ... #ድንግል ነበርኩኝ ፡፡ በአራት አመቴ ተደፍሪያለሁ እያልኩ ሳለቅስ ኑሬ ...በትምህርት ቤት በሰፈር በልጅነትሽ የተደፈርሽዉ እያሉ ሲያስለቅሱኝ ሲያገሉኝ ያለፉት የኖርኩባቸዉ አመት አላህ እኔን እየፈተነኝ እንደሆነ ተረዳሁኝ
...ካሊድም እየተገረመ ነዋል ታስታዉሻለሽ በምታለቅሽበት ጊዜ የአላህ ነገር አይታወቅም ድንግልም ልትሆኝ ትችያለሽ ስልሽ አላምንም ብለሽ ነበር ከአላህ ምንም ተስፋ መቁረጥ አያስፈልግም አለኝ

#የጫጉላየ_ምሽት

ፊቴ አብርቶ ጥርሴ ይስቃል
ከጀርባ ያለዉ ሀዘን ከቶ ማን ያዉቃል
እንዲህ ደምቄ ፈክቼ ላየኝ ሰዉ
በሆዴ ፍም እሳት ያለም አይመስለዉ

ዛሬ ላይ ሁኜ የትናንቱን ግፍ አስታዉሳለሁ
በትዝታ መስኮት እያንዳንዱን ህመም እመለከታለሁ

በጨቅላ እድሜየ ክፉን ከደጉ ባለየሁበት
ጫማ ለመልበስ ግራዉን ከቀኙ ባላወኩበት
ስጋና አጥንቴ ከደሜ ጋራ ሳይዋሀዱ
ሁለቱ እግሮቼ እንኳን እርቀዉ ሳይራመዱ
ሲመሩኝ ምመራ ኩልትፍትፍ የምል
ዉብ ፅጌሬዳ ሲያዩኝ ደስ የምል

እንኳን ጭካኔ ለኔ ሊገባኝ
ለቁንጥጫ እንኳን የማሳሳ ነኝ
ምን ዋጋ አለዉ የሰዉ አዉሬ ጨከነብኝ
ለማይረባ ለደቂቃ ስሜቱ ተጫወተብኝ
ከሰዉ በታች አድርጎ እንዳልነሳ ቀበረኝ
አንገቴን ላይነሳ እንድደፋ አደረገኝ

ያ! ሰው መሳይ ሰው ያልሆነው
ህልሜን በአንድ ቀን አጠልሽቶ በላዉ
ቅስሜን ሰብሮ ልቤን አደማዉ
ያ የሰዉ አዉሬ ደስታየን ነጥቆ ሀዘን አሸከመኝ
ሚስጥሩን ያወቀም ከጎኔ እንዲሸሽ አረገኝ


ሂወትን በጠላሁ ሰው ባጣሁ ሰአት
ሞቴን ስናፍቃት ቀብሬን ስመኛት
ትዝ አለኝ አንድ ቃል የመጠጊያዬ
ለምኑኝ ሰጣለው ያለውን ጌታዬ

ያኔ በጥዋት በማታ በቀን በለሊት
እንባየ ሲፈስ ለብዙ አመታት
አብሽሪ የሚለኝ ሀዘኔን አይቶ
እንባየን አባሽ አንድ ሰዉ ጠፍቶ
ተደፍረሻል ብለዉ ሰዎች ሲሸሹኝ
እጆቼን ዘርግቼ ያረቢ አልኩኝ

እኔም ሁሉንም ትቼ ወደሱ ሸሸሁ
እንደመርየም ንፁህ መሆንን ተመኘሁ
ማንነቴን የሚቀበለኝ ደግ ባሪያህን ስጠኝ ብየ አንገቴን ሱጁድ ላይ ደፋሁ
ሌት ተቀን እየሰገድኩ አምርሬ አነባሁ
ያረብ አልኩት አላህም ዱአየን ሰምቶኝ
ማንነቴን ተቀብሎ የወደድኩት የወደደኝ
ደጉን ባሪያዉን የዱአሽ ዉጤት ብሎ ሰጠኝ
ሀዘንሽ ሀዘኔ ደስታሽም ደስታየ ብሎ ተቀበለኝ

የበደለኛ እንባ መች ይቀራል ፈሶ
ትአምር አየሁ ዱአየ ደርሶ
ልክ እንደመርየም እንደጠየኩት
ቢክራ አደረገኝ በሰርጌ ምሽት
በደቂቃዎች ሁኔታዎችን የሚቀያይር
ለኛም አሳየን የማይታመን ትልቅ ታአምር

ነብዩ ዪኑስን
ከአሳ ነባሪ ፈልቅቆ አወጣዉ

ነብዩ ሙሳን
ከሚያሰምጥ ዉሀ ነፃ አወጣዉ
ነቢዩ እስማኤልን
በአንገታቸዉ ላይ ያንን ቢላዋ አቅም አሳጣዉ

ለነቢ ኢሳ
የሞተዉን ሰዉ ህያዉ እንዲያደርግ ችሎታ ሰጠዉ

ነቢ ኢብራሂምን
ከዛ ከነበልባሉ ከአስፈሪዉ እሳት ነፃ አወጣዉ

የሰዉ ዘርን
ከአፈር ከጭቃ በታላቅ ጥበብ አቡክቶ ሰራዉ

ከመርየም ገላ ክብርዋ ሳይነካ ልጅ ፈጠረው

ታድያ...!

ይሄን ያረገ ታላቁ ያመውላ
ድንግል ማድረግ የነዋልን ገላ
እንዴታ ይሳነው እሱ እኮ ጌታ ነው
ሁሉ ሚታዘዘው ሁን ሲል የሚሆን ነው

ዛሬ ያሁሉ ሀዘንና ስቃይ ተወግዶ
በደስታ ተተካ የሀዘን ተራራዉ ተንዶ
አልሀምዱሊላህ ከማለት ዉጭ ምን ይባላል
በርግጥም ሁኔታዉ አጃኢብ ያስብላል
እልፍ ምስጋና ጥራት ይገባዉ
ለአንዱ ጌታችን ወደር ለሌለዉ

ይሄዉ ከአራት አመቴ ጀምሮ ሳለቅስ የኖርኩትን በአንድ ቀን ወደ ደስታ ቀየረዉ...በጣም ደስተኛ ነኝ ያለፉትን ጊዜያት ሀዘኔ  ከአሁኑ ደስታ ሳወዳድረዉ የሰማይና የምድር ልዩነት አለዉ ሌላ ምን ይባላል አልሀምዱላህ


ልብ በይ እህቴ!!!! በሴቶች ላይ የሚገኘዉ ገቢ በዓመት ከ7ቢሊየን ዶላር እንደደረሰና..ይህም ገቢ ከመሳሪያ ሽያጭና ከአደንዛዥ እፅ ቀጥሎ በሶስተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጥናቶች ይገልፃሉ

እህቴ ሆይ የሴቶች እኩልነት ብለዉ ምዕራባዉያን ለአንቺ የሰጡሽ መብት ምን አንቺን ለማጃጃል እንደሆነ ምን ያህል ታቂያለሽ? ለምሳሌ ስፔን እንዉሰድ የሴቶች መብት ተብሎ መስሪያ ቤት ገብተዉ እየሰሩ ነዉ ..በስፔን በተደረገዉ ጥናት ከአንድ ሚሊየን በላይ ሴቶች በየመስሪያ ቤቱ የመደፈር ሙከራ ተደርጎባቸዋል፡፡ በስፔን ዋና ከተማ ማድሪድ ብቻ በተደረገዉ ጥናት 13100 ሴቶች በአለቃዎቻቸዉና በስራ ባልደቦቻቸዉ የመደፈር ሙከራ ተደርጎባቸዋል..በአጠቃላይ 15% የሚሆኑት የስፔን ሴት ሰራተኞች በጠቅላላ 8ሚሊየን 425 ሺ ሴት ሰራተኞች ለመደፈር አደጋ እንደተጋለጡ ጥናት ያሳያል፡፡ደፈራ የተደረገባቸዉ ሴቶች ስማቸዉን ለመጠበቅ እና ከሀፍረታቸዉ የተነሳ ለሚመለከተዉ አካል ክስ አይመሰርቱም ..ክስ ለመመስረት ሙከራ ያደረጉት 25% ብቻ ናቸዉ..56% ተደብቀዉ ይገኛሉ..8% የሚሆኑት ክስ በመመስረታቸዉ ከአለቆቻቸዉ ከሚሰሩት ድርጅት ከስራ እንዲሰናበቱ ተደርገዋል..45% የሚሆኑት ከስራቸዉ እንዳይባረሩ የመደፈርን ችግር ተቀብለዉ ጊዚያቸዉን ያሳልፋሉ፡፡ በዚህ የተነሳ ሴቶች ለጭንቀት ለመረበሽ ሰላምና እንቅልፍ አልባ ለመሆን አደጋ ስለተጋለጡ የማስታገሻና የማረጋጋት መድሀኒት ለመዉሰድ ተገደዋል፡፡ ሴቶች በእኩልነት ወደ መስሪያ ቤት በመግባት ባስከተለባቸዉ የጭንቀት በሽታ በአሜሪካ 61% በኢማራት 38% የጭንቀት ማስታገሻ መድሀኒት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ እናም እህቶቼ መብቴ ነዉ እያልሽ በዚህ አዘቅት ዉስጥ እንዳትገቢ አንቺም ተጠንቀቂ ሰዉ ሲሸወድ ሲዘነጋ በአንድ ቀን አይለይም በሒደት በጊዜ ብዛት እየተንሸራተተ ነዉ የሚሄደዉ የአቋም መዋዠቅ ሲገጥምሽ ጠርጥሪ

★ የሴት ልጅ ጥቃት መቼ ነዉ የሚያበቃዉ? አንተም እሱም እነሱም እነዛም ዘር ብሔር ሀይማኖት ሳይለያየን ከጎናችን ቁሙሉን ..ሴት እናትህ ነች እህትህ ነች ለቅሷዋ ሊያስለቅስህ ሊያስዝነን ይገባል፡፡ ለሴት ልጅ ክብር የሚጨነቅ ሴትን ልጅ ለስሜት ብቻ ማሰብ ትተን በሆዷ ዉስጥ አፍና የምትዞረዉን የፉም እሳት ለመረዳት ሞክሩ .ሴት ልጅ ሀዘን በዉስጧ እያለ በጥርሷ ደስተኛ ተጨዋች መስላ መኖር የምትችል ፍጥረት ነች .ማንኛዉም ሴት ስለሳቀች ስለተደሰተች ደስተኛ አይደሉም ብዙዎቹ ለሊት ላይ ሲጨነቁ ሲጠበቡ ሲያለቅሱ የሚያድሩ በብዙ የሀሳብ ማዕበል እና ሆዳቸዉ ዉስጥ ተናገረዉ የማይወጣ የሚቀጣጠል ጥፋ ቢሉት የማይጠፋ እንደዉም እየተፏፏመ የሚሄድ የእሳት ማዕበል ተሸክመዉ የሚሄዱ ናቸዉ ..እናም አንተ ወንድ ነህ በእሳት ላይ እሳት ከመጨመር በሆዷ ያለዉን እሳት አንተዉ ተረድተህ በስሜት መነዳቱን ትተህ ሸክማን በሀሳብህ ተቀብለህ እሳቱን በብልሀት አጥፋላት..የዛን ጊዜ አንተ ለሷ የደስታ ምንጭ እና የህሊና እረፍት ታገኛህ
ታሪኬ ከሞላ ጎደል ይሄን ይመስላል፡፡
አሁን ላይ የአንድ ልጅ እናት ነኝ...ወንድ ልጅ አላህ ሰጥቶኛል አድጎ ለዲነል ኢስላም የሚጠቅም ልጅ እንዲሆን ዱአ አድርጉልኝ፡፡👇👇👇
★ዉድ አንባቢዎች ይሄን ታሪክ እንዲቀርብ የፈለኩት ለኔ ባይጠቅመኝም ግን እንደ እኔ ብዙ የተጎዱ ስላሉ ከኔ ትምህርት እንዲወስዱ እና ተስፋ መቁረጥ እንደሌለባቸዉ ለማስታወስ ያህል ነዉ
★ፀሀፊ አሚር ሰይድ ከደሴ ከተማ ከልብ አመሰግናለሁ በየaudio የላኩልህን እና በስልክ ያጫወኩህን ዉሸት ሳትጨምር እንደዚህ በሚያምሩ ቃላት አሳምረህ በማቅረብህ ከልብ አመሰግናሀለሁ፡፡


የኔ የአሚር ሰይድ ለማጠናቀቅ ያህል በዚህ እዉነተኛ ታሪክ የተወሰነ ልበል፡፡
በዚህ በነዋል ታሪክ ለእሷ ጥንቃቄ ሲባል የእሷ ስም የምትኖርበት ከተማ ተቀይሯል...
   ባለታሪኳ ነዋል ታሪኩን የነገረችኝ ለካሊድ መደፈሯን ከነገረችዉ ቡሀላ ሽማግሌ ሊልክ ሲል ነበር....ከዛ ቤተሰቦቿ ሲጣሉ ሚፍታህ መልሼ ልላክ ሲል እንደ አጋጣሚ እኔን ነበር የምታማክረዉ በሚዲያ ያገናኘን ምርጥ እህት ወንድም ሁነን ነበር ጠዋት ማታ ነበር የተፈጠረዉን እየደወለች እየነገረችኝ በመመካከር ነበር ለዚህ ትዳር  እንድትደርስ የሆነችዉ
☞ሚፍታህ መልሶ ልላክ ሲል የነዋል ሁብ የመጀመሪያ ፍቅር ከባድ ነዉና..ሚፍታህን ፊት እንዳትሰጥ ማግባት እንደሌለባት ያሳመንኳት እኔ ነበርኩ....እኔ ከሚፍታህ የካሊድ ደጋፊ ነበርኩ ሚፍታህን እንዳታገባ ካሊድን እንድታገባ ያደረኩት እሷ ጋር ስንመካከር በማሳመን ነበር መቼም ከታሪኩ ትረዳላችሁ፡ መቼም አላህም የፃፈዉ ነዉ ካሊድ ጋር በመሆኗ ምንም ቁጭት እንደሌለዉ  ትረዱኛላችሁ ብየ አስባለሁ...
ሚፍታህን ነዋል እንደምወደዉ ባቅም ግን የሴት ልጅ ፍቅር ለትዳር በቂ አይደለም እሷን ከ3 አመት በላይ የሚወዳት ብታገባ ይሻላል ብየ ነዉ፡፡ ሲጀመር ሚፍታህ ለሰዉ ልዳርሽ ብሎ ጀምሮ ነዉ በሰዉ እርዚቅ ገብቶ ነዋል ጋር የጀመሩት ካሊድ ግን ሁሌም ይወዳታል ነዋል ትገበዋለች ብየ እኔም በተደዋወልን ቁጥር በሚፍታህ ፍቅር ብትቸገርም ካሊድን እንድታገባ ተፅእኖ ፈጥሬበታለሁ፡፡ የነዋል ባህሪ ደስ የሚለዉ ሰዉ ትሰማለች ታገናዝባለች እንደአሁን ሴቶች ችኩል አይደለችም ..በፊት እሷ በዛ ችግሯ እኔን አማካሪዋ በማድረጓ ሁሌም ትዝ ባለኝ ቁጥር ደስተኛ ነኝ፡፡
ሚፍታህ ሌላ ሲያገባ ምንም እንዳይመስልሽ ነበር ብየ ከእሷ አግብቶ በመራቁ ሞራል ስሰጣት የነበረዉ..ሚፍታህም ጓደኛዉ የሱፍም ሲያገቡ አዉቅ ነበር ለምን ከነገረችኝ ቡሀላ ታሪኩ ላይ ያልተፃፈ ብዙ ፈተና ስለነበር..ይሄን ፈተና እኔ ከደሴ ሁኜ አብረን ነበር በመወያየት በመመካከር ለዚህ ደረጃ ነዋል የደረሰችዉ
☞እኔም ጋር ስታወራ ነዋል በኔ አመለካከት ድንግል ነሽ ብየ ነዉ የማስበዉ ብየ እነግራት ነበር...አራት አመትሽ ነዉ ወዳዉ እናትሽ ደርሳበታለች አንቺም በጊዜዉ ታመሽ አልተኛሽም እናም አትጨነቂ አንቺ ድንግል ነሽ አንቺን የሚያስቸግርሽ የሰዉ ወሬ ተደፍረሻል እያለ እንጂ አንቺ ድንግል ነሽ እላት ነበር፡፡
በነገራችን ላይ እሷ ስታገባ covid ባይሆን እንደ እቅዷ ሀይለኛ ሰርግ ብታዘጋጅ ሰርጉ ለመገኘት ቃል ገብቼ ነበር ግን covid ሁኖ ሰርግ ስለተከለከለ የተካበደ ሰርግ አላረገችም እኔም አልሄድኩም...በሰርጉ ማግስት ሰኞ ለት ጠዋት አሚር የሚገርም ነዉ ድንግል ነበርኩ ስትለኝ ወላሂ ያንን message ሳየዉ የደስታ ለቅሶ ነበር ያለቀስኩት...ለምን በስልክ ከ6ወር በላይ ተወያይተናል ሚስጥሯን ስለነገረችኝ የሆነ ሙሲባ ሲመጣባት ደዉላ አማክራኝ ተወያይተን ነበር የምንፈታዉና

#ይሄን_ታሪክ ከፃፍኩት ቡሀላ በተለያዩ ምክንያቶች በጊዜ ማጣት ላለማቅረብ ወስኜ ነበር ነገር ግን 2012 ረመዷን ሶስተኛዉ ቀን ላይ እሁድ ቀን እንደ አጋጣሚ ከምሽቱ ሁለት ሰአት ቡሀላ በሪሞት እየቀያየርኩ prgram ሳይ 2012 ላይ ፋናtv ላይ የሆነ እዉነተኛ ዶክመንተሪ ፊልም አይኔ አረፈ
አንዲት ሴት ልጅ ከልጅነቷ ጀምሮ በአባቷ የወሲብ ጥቃት ይደርስባት ነበር ..አባቷ መጠጥ እየጠጣ ማታ ማታ ሁሌ ያስቸግራታል ..ሳትወድ በግዷ አባቷ ጋር ብዙ ቀን ታድራለች...ከዛም ወደ 18ቹ አመት ሲጠጋት ከአባቷ ታረግዛለች...ግን ለማን ታዉራ ለማን ትናገር
??ሁለት ታላቅ ወንድሞች አሏት ግን የየራሳቸዉ ስራ አላቸዉ እቤት አይኖሩም..አባቴ ይደፍረኛል ብላም ለመናገር ትፈራለች...ከዛም ሲቸግራት ለጓደኛዋ ትነግራታለች ..ጓደኛዋ እና ልጅቷ ሁነዉ ጓደኛ መኖሪያ ቤት ይሄዳሉ ..ጓደኛዋ ለእናቷ ነግራት እንርዳት ስትላት..ከአሁን ቡሀላ እሷ ጋር ጓደኛ እንዳትሆኝ ብላ የጓደኛዋ እናትም ከቤት አስወጣቻት...ከዛም ሲጨንቃት ለአባቷ እህት(አክስቷ)ታማክራታለች ..አክስቷም አመነጫጭቃ ከአሁን ቡሀላ ወንድሜን እንደዚህ ብለሽ ብታነሺ በእኔ እጅ ነዉ የምሞችዉ ብላ ከቤት አባረረቻት....ታዳ ይሄን በደሏን የሚረዳት ስታጣ ጓደኛዋ የምትፅፈዉን ደፍተር ብቻ አደረገች

ይቺ ሚስኪን ልጅ ከአባቷ አርግዛ ሆዷ ገፋ..አባትየዉ በሰፈር ልጄ ዱርየ ሆነች ዲቃላዋን ይዛብኝ መጣች እያለ ወሬዉን አናፈሰዉ...የልጅቱ ሁለቱ ወንድሞችም እርጉዝ በመሆኗ ዱርየ ሆነች ብለዉ ከማን አረገዝሽ ብለዉ እንኳ ሳይጠይቁ አኮረፏት... ይቺ ልጅ ለማን ተናግራ ማን ይረዳት??ሒወቷ ገና በልጅነቷ ተበላሸ ህልሟ በአባቷ ጨለመ...ይሄም ሳያንሰዉ በሰፈር ልጄ ዲቃላ አመጣችብኝ እያለ በዉሸት ወሬዉን ነዛዉ፡፡ ልጅቱ የወሰደችዉ እርምጃ መጠኑ ያልታወቀ ኪኒን ዉጣ እራሷን አጠፋች😔😢ከሞተች ቡሀላ ወንድሞቿ ቢያለቅሱ የጓደኛዋ እናት ብትቆጭ ለልጂቱ የጠቀማት ነገር የለም ..
ፓሊስ የሞተችበትን ሲያጣራ በደብተር ላይ የፃፈችዉን መኝታ ክፍሏ አግኝቶ አባቷን አስሮ .ስንት አመት እንደሆነ እረሳሁት እስር ተፈረደበት፡፡

ቆይ እስኪ እንደዚህ አይነት አባት....በልጅነታቸዉ የተደፈሩ ሴቶች ምክንያት የሆኑ ወንዶች የሞት ፍርድ ካልተፈረደበት የሴት ልጅ አስገድዶ መደፈር ያቆማል ወይ???በጭራሽ ወንድ ልጅ ሴትን ልጅ እየበደለ ታስሮ እስከተፈታ ድረስ በልጅነታቸዉ የሚደፈሩ ሴት ልጆች መቼም መቆም አይችልም

የሞተ ተጎዳ አባትየዉ ከእስር ይፈታል መልሶ መኖር ይጀምራል ...እራሷን ያጠፋችዉ ልጅ ግን ወላሂ አሳዘነችኝ አስለቀሰኝ የነዋል ታሪክ ጋር ሳመዛዝነዉ የዝች ልጅ ታሪክ አሁን ድረስ ከአእምሮየ ሊጠፋ አልቻለም.. ይሄን እዉነተኛ ዶክመንተሪ ፊልም ካየሁ ቡሀላ ነዉ የነዋልን ታሪክ ለማቅረብ ያነሰሳኝ፡፡

#የእኔ_አሚር_ሰይድ ልባዊ ምኞቴ ይሄን ታሪክ ያነበበዉ ሰዉ ...ወንድ ለሴት ወገኖቹ እንዲያስብ ..ሴቶችም የወደፊት ትዉልድ በእነሱ ማህፀን የተቋጠረ ስለሆነ በተርቢያ በዲን አሳድገዉ ለዲነል ኢስላም የሚያስረክቡ እንስቶች ካሉበት ተጨባጭ እራሳቸዉን እንዲፈትሹ ነዉ፡፡

እኔ የምፅፋቸዉን ያነበበ ሰዉ እራሱን ቀይሮ ወደ ፈጣሪዉ እንዲቃረብ እና ወደ ወንጀል መንደርደር የያዙ እንዲያፈገፍጉ እና በወንጀል የተዘፈቁ ጥርት ያለ ተዉበት ቶብተዉ ወደ ፈጣሪያቸዉ ያለዉን መንገዳቸዉን እንዲያስተካክሉ እና ማንኛዉም ሰዉ እራሱ ተቀይሮ ማንኛዉንም ሰዉ የመቀየር ተሰጥኦ ስላለዉ ይሄን ተሰጥኦ በተግባር እንዲያሳይ ብር ያለዉ በብር..ሀሳብ ያለዉ በሀሳቡ..እዉቀት ያለዉ በእዉቀቱ...ዲነል ኢስላምና ኢስላም ወንድም እህቶቹ ጎን እንዲሆን ልባዊ ምኞቴ ነዉ፡፡
#ተ............ #ፈ............ #ፀ...... #መ.....

ታሪኩ በ2013 ተነቦ በድጋሜ አሁን የቀረበ ነዉ
⚠️⚠️ከይቅርታ ጋር ጥሩም መጥፎም ማንኛዉንም አስተያየት አልቀበልም
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ዉድና የተከበራችሁ የቻናል ቤተሰቦች የሆድ ዉስጥ ፉም እሳት ታሪክ ጨርሰናል ፡፡እስኪ ስለታሪኩ ወንድሜችሁ አሚር ሰይድ የመሰለኝን ትንሽ ብቻ ልናገር ለምን አሁን ሰሚ የለም ሁሉም በራሱ አለም ላይ ነዉ ያለዉ

🔵በዚህ ታሪክ ላይ ከሙሉ ፁሁፉ ቢያንስ 20% በራሴ አመለካከት ስላስገባሁ ታሪኩ በመሀል ያሉት የራሴ አመለካከት ስለሆነ ያበቂ ነዉ ግን በተጨማሪ
☞በአሁን ጊዜ በህፃንነታቸዉ ወይም አድገዉ ተገደዉ ሴት ልጅ መደፈር የሴት ልጅ ጥቃት በየሰፈሩ በየመንደሩ የቡና መጠጫ ወሬ ሁኗል..ይሄ ታሪክ በዚህ ሰለባ የሆነች እህታችን እዉነተኛ ታሪኳን አቅርቢያለሁ ግን ማወቅ ያለብን ከዚች ልጅ የባሰ ብዙ የሒወት ተራራን ለመግፋት የተገደዱ እህቶች አሉ ታዳ እነዚህን እህቶቻችንን ማን ነዉ ተርድቶ ከአእምሮ መጨናነቅ ዲፕሬሽን ሊያላቅቃቸዉ የሚችለዉ?? ዘመድ ቤተሰብ ወይስ ጓደኛ??? ወይስ እንደዚሁ ሰዉ ሲያያቸዉ እየሳቁ ብቻቸዉን እንዳለቀሱ እንዲኑሩ የተፈረደባቸዉ እህቶቻችንን ለማን አቤት ብለን ድምፃችንን በሰማን?? ለመንግስት ወይስ ለሀይማኖት አባቶች ወይስ ለፓለቲካ ፓርቲዎች?? ሁሉም ይሄን ግፍ ያወቀዋል ግን ለምን አሁን ድረስ መፍትሄ ለምን ጠፋ?? መቼ ድረስ ነዉ የሴት ልጅ ጥቃት የሚቆመዉ?? ይሄ ጥያቄ የሁሉም ሰዉ ጥያቄ ነዉ መልሱ ግን እስከ አሁን ከሰዎች አንደበት ሲመለስ ሰምቼዉ አላቅም ፈጣሪ የተሻለዉን ያዉቃል ብለን እንለፈዉ ..ግን ለወደፊት ይሄ ነገር መቅረት የሚችለዉ እንዴት ይሆን??እስኪ ሁሉም ብቻዉን ሰአት ሰጥቶ ይሰብበት....

🔴 በታሪኩ ላይ ድንግል አይደለሁም ተደፍሪያለሁ ብላ አስባ ስንት ትዳር ሲመጣ በልጅነቴ ተደፍሪያለሁ ለማለት ስትጠበብ ስትጨነቅ ስንት ስቃይ እንዳሳለፈች አይተናል..ግን ወንድሞቼ ለትዳር ቢክራ መሆን መስፈርት ነዉ ወይ?? በልጅነታቸዉ ሳይወዱ በግዳቸዉ የተደፈሩ..በስራ ብዛት ..በምቾት..በወር አበባ ብዛት አብሮ ድንግልናቸዉ የሚሄድ እህቶች እኮ በጣም ብዙ ናቸዉ..ታዳ ለእነዚህ ንፁህ እህቶቻችን ንፁህ ልባችንን ከፍተን የምንረዳቸዉ መቼ ይሆን ??
በጣም ማሰብ አለብን ይሄ ነገር እኮ እኛ ካልተረዳናቸዉ ለሌላ ሀይማኖት አጋልጠን ሰጠናቸዉ ማለት ነዉ..ለምን ድንግልና ለትዳር መስፈርት ያልሆነ ሀይማኖት ተከታዮች አሉና...


🔴በዚህ ታሪክ ላይ የትምህርት ቤት ላይፍ አይተናል፡፡ የማይካድ ሀቅ ነዉ...አሁን ትምህርት ተዘግቶ ምነዉ ትምህርት በተከፈተ ብለዉ የሚናፍቁ ተማሪዎች ትምህርቱ ናፍቋቸዉ ሳይሆን ላይፉ ናፍቋቸዉ እንደሆነ ጥርጥር የለዉም፡፡ትምህርት ቤቶች ሴትና ወንድ አንድ ላይ እየተማሩ ይሄ ይቀራል ብሎ ማሰብ ቤንዚን ላይ እሳት ጨምሮ አይነድም እንደማለት ይቆጠራል ፡፡ ለምን ነዳጅ ለማስሞላት ገና ማደያ ስንገባ ስጋራ ማጨስ እና ተቀጣጣይ ነገሮች ይዞ መግባት ክልክል ነዉ የሚል በማንኛዉም ማደያ ቦታ ተለጥፏል ፡፡ታዳ ሁሉም ማደያዎች ቅድመ ጥንቃቄ ማስጠንቀቂያዉ ተለጥፏል እኛስ ይሄን የወንድና የሴት አብረዉ እየተማሩ ዱርየ ቢሆኑ ይፈረዳል ወይ??? ግን አንድና አንድ መፍትሄ አለ ይሄም መፍትሄዉ በሁላችንም አእምሮ እና ጥረት የሚስተካከል ነዉ ብየ አስባለሁ .

🔸🔸እስኪ እኔ በራሴ ያጣራሁትን ልንገራችሁ፡፡ ደሴ ከተማ አንድ ጓደኛየ ሳዳትን በደንብ ያቀዋል ከሱ ነዉ ቂርአት የቀራዉ ብሎ አስተዋወቀኝ ከዛም ስለሳዳት ጥርጥር ያለብኝን ነገር ሁሉ ጠየኩት ልጁ ጋር የሚገርማችሁ 99% ተግባባን በጥሩም በመጥፎም ጎኑም ብዙ ነገሮች ተመካከርን ግን ትምህርት ኢህቲላጥ እያላችሁ ለምንድን ነዉ የምከለክሉት?ብየ ጠየኩት..ልጁም ሳዳት አይከለክልም የሚከለክለዉ የደሴዉ ሙስጠፋ ነዉ አለኝ፡፡ እኔም በጣም ቅርብ 6አመት ሙስጠፋ ኪታብ ያቀራዉን ልጅ ጠየኩት
ለምንድን ነዉ ኢህቲላጥ እያላችሁ ትምህርትን የምከለክሉት?? ብየ ጠየኩት
እሱም እንዲህ ብሎ መለሰለኝ ወደ ቁርአን ሀዲስ ስንመልሰዉ መደባለቅ አላህ ከልክሏል ፡፡ እና ነብዩ ሙሀመድ ሰዐወ እና አራቱ ኸሊፋዎች ዘመን ወንድና ሴት ተደባልቆ አልተማረም ..ደግሞ የበላዮች ህግ የሚለዉ ህገመንግስት እያልን ነዉ የምትማረዉ የበላዮች ህግ ግን ቁርአን ነዉ ..ይሄ ትምህርት ዱንያዊ እንጂ አኼራዊ አይደለም ብሎ መለሰልኝ
..እኔም መጀመሪያ እኮ ኢህቲላጥ ሀራም ነዉ ማለት ያለባችሁ ሴትና ወንድ የማይደባለቅበት ከፍታችሁ ነዉ መከልከል የምችሉት ስለዉ
እሱም ዱአ አድርግ በKGጀምረናል ለወደፊት አንደኛም ሁለተኛም ደረጃ እስከ ኮሌጅ ለመክፈት አስበናል:: በተጨማሪ የሙስሊም ሴቶች ሲወልዱ በሙስሊም ሴቶች እንዲወልዱ እስከ ሆስፒታል ድረስ በደሴ አስበናል አለኝ ፡፡ ከዚህ በላይ መጠየቅ አልፈለኩም አላህ ይገዛችሁ በአቅሜ የበኩሌን አደርጋለሁ አላህ ይገዛችሁ ብየ ጥያቄየን ጨረስኩ፡፡
☞አንድ ነገር ማወቅ ያለብን የሁሉንም የኢስላም ኡስታዞች ትምህርት ማዳመጥ ጠቃሚ ነዉ እኔ የሳዳትንም የሙስጠፋንም የነአቡበከር ያሲን ኑሩ ወዘተ በተመቸኝ አጋጣሚ አዳምጣለሁ ከሁሉም ኡስታዞች የሚጠቅመንን መያዝ እንጂ የአንድ ወገን አመለካከት ጨምድዶ መያዝ ሞኝነት እንደሆነ ይሰማኛል፡፡

ለማንኛዉ አሁን ተደነጋግረናል ፈጣሪ ከድንግርግር ይጠብቀን....
አንዱ ባለፈዉ በደርግ ጊዜ የተማረ ወይ በ19 ክፍለ ዘመን የተማረ መሰለኝ እኔ እስከ 12 ተምሬ እስከምጨርስ 1000 ብር አልጨረስኩም ዛሬ ልጅ ትምህርት ቤት ይዞት የሄደዉ ከ3000 ብር በላይ ሁኗል ብሏል፡፡ እዉነት ነዉ ፓርሳ 1500-1000 ደብተር 800 የትምህርት ክፍያዉ እስክርቢቶዉ ሁሉ ሲሰላ ከ3000 ይበልጣል እናም በኑሮ ዉድነት ወጭ ወጥቶ እየተማሩ ወላጅ ቢከታተል ጥሩ ነዉ፡፡



🔴 ማወቅ ያለብን ጓደኛ ወሳኝነት ነዉ በታሪኩ ላይ ስለ ጥሩ ጓደኛ ብዙ ቦታ አስገብቻለሁ...
☞ሚፍታህ ነዋልን የጀመረዉ የሱፍ ዳረኝ ብሎት እንደሆነ አንብበናል.ሁሌም ቢሆን አደራ ለሀላል ከሆነ የምፈልጋት በጓደኛችሁ አደራ እንዳትጀምሩ ለምን የቅርብ ጓደኛህ አይሆን...ሴትና ወንድ ሲያወሩ ምን እንደሚፈጠር አናቅምና👌 እሱ በአፉ በጣም ቀልጣፋ ከሆነ ሴት ልጅ ልቧ ያለዉ ጆሮዋ ላይ ነዉ ይባላል. እናም የሰማችዉን ሁሉ ስለምታምን አስታርቃለሁ ብሎ ገብቶ አፍኜ ብበላ ብሎ ከኳስ መጫወቻ ሜዳ ዉጭ ጠርዞ እንዳያወጣህ😊

እኔ ወላሂ ከዚህ ታሪክ ጋር የተያዘዘ እዉነተኛ ነዉ..
🔸አንድ በጣም የምቀርበዉ ጓደኛየ ሌላ የእሱ አብሮ አደጉ ጓደኛ አለዉ..ጓደኛዉ አንዲትን ልጅ ይወዳታል ለትዳር እያወራት በመሀል በቀላል ነገር አለመግባባት ይፈጠራል..ላስታርቃችሁ ብሎ ተለሳልሶ ገብቶ አጣልቷቸዋል..ከዛም ለራሱ አድርጎ ሊያገባት ጫፍ ደርሶ ደግሞ ተጣልተዋል፡፡ ግን አስታርቀኝ ያለዉ ልጅ ጓደኛዉ ነዉ እየደበረዉ እየገረመዉ ትችታለሁ ለአንተ ትሁን ብሎ አዝኖ መጥፎም ክፉም ሳይናገረዉ ጓደኝነቱን ሰረዘዉ ..እኔም ወላሂ ይሄን በማድረጉ ባልጣላዉም ግን ለወደፊት እንዳላምነዉ አድርጎኛል..ለምን ነገ የሚሆነዉ አይታወቅምና፡፡
☞ እናም የቻናል ቤተሰብ ምርጥ ወንድሞቼ ለትዳር የሰብካትን ከተጠላህ በሁለታችሁ ብቻ ይፈታ..በሀሳብ ማመን በመነጋገር ማመን አለባችሁ ሚስጥር ከሁለታችሁ ከወጣ ሶስተኛዉ ሰዉ ለምን ይደብቀዋል?? ለምን ከእናንተ አልፏላ... በሁለታችሁ ችግራችሁ  ካልተፈታ ገና ዉስጥ ለዉስጥ አልተናበባችሁም ማለት ነዉ፡፡ አላህ ያግባባችሁ 😊 ሌላ ካግባባችሁ በጣም ግራ ነዉ የሚገባችሁ. ችግርን ሁለታችሁ ተነጋግራችሁ መፍታት ካልቻላችሁ ነገ ስትጋቡ ብትጣሉ አስታራቂ ካልተገኘ አራተኛዉ የአለም ጦርነት ፈጠራችሁ ማለት ነዉ😉👇👇👇
እህቴ ሆይ አስተዉይ
☞መጀመሪያ በአንቺ በቤተሰቦችሽ የመጣ ትዳር ፈላጊ ነዉ ተብሎ 75% ይታሰባል
☞ነገር ግን በጓደኛሽ የመጣ ከሆነ ..አላህን የማፈራ የሙስሊምም ሆነ የሌላ ሀይማኖት ተከታይ ብትሆንም አንቺን ከእሱ በምታገኘዉ ጥቅማ ጥቅም  ልትሸጥሽ እንደሆነ 90% ይጠረጠራል፡፡ እናም ይሄ ልጅ ለአንቺ ያለዉ አመለካከት..ስለ አንቺ ጥሩ ነገር ያወራል ካለችሽ እባክሽ ተጠንቀቂያት ሴት ስትፈግ ሴትን በሴት እሾህን በእሾህ ነዉና..የአንቺ ጠቃሚሽም ጎጅሽም ሴት እህቶችሽ እንደሆኑ ሁሌ አትዘንጊ

🎖🎖ዉድና የተከበራችሁ ቤተሰቦች የማጠቃለያ ፁሁፍ በጊዜ ማነስ አስቤበት አላዘጋጀሁም ነገር ግን በታሪኩ ላይ ብዙዉን ጠቅሸዋለሁ...

መልካም ንባብ ተመኘሁ
አስተያየት አልቀበልም ለምን እራሴ ለራሴ መቋቋም የማይቻልበት አቅም ላይ ተሁኖ አስተያየት መቀበሉ ጥቅም የለዉም..ደግሞ በአስተያየት የሰዉ ልጅ መፅሀፍ ነዉ ብዙ የደበቀዉ አለ አንዳንዴ ስለምሰማ ራሴን መሆን እያቀተ የሰዉ ሀሲብ ሲጨመር ከባድ ነዉ የሚሆነዉ ፡፡ እናም በአስተያየት መስጫ bot ትችትም ጥሩ ሀሳብም ለወደፊት የሚስተካከል ብየ የምቀበለዉ የለኝም...መፃፍ አቁሚያለሁ ይሄም የሆድ ዉስጥ ፉም እሳት ለyoutuber እና ለቻናሎች በማሰብ ነዉ የበፊቱ 45 part ስለነበር ሳይዙን ቀንስልን ስላሉኝ ነዉ 2013 የተነበበ ታሪክ አሁን የተደገመዉ፡፡

ብዙ ቀን ለምን ታሪክ አታዘጋጅም ቻናልህ ሰዉ እየቀነሰ ነዉ ምናምን የሚል አስተያየት አያለሁ...እኔ አንድ ሰዉ ቻናል ላይ ቢቀር አይመለከተኝም እኔ እንደሙነሺዶች ዩቲዩብሮች በስሜ ነግጄ ብር ማግኘት አልፈልግም ሁሉም የራሱ አቋም አለዉ....እኔ የራሴ በጣም ቢዚ የሚያደርግ ስራ አለኝ ፁሁፍ በፊትም በትርፍ ሰአቴ ለሊት ነበር የማዘጋጀዉ እንደሙነሺዶች እንደ አንዳንድ ፀሀፊዎች ሚዲያ ለኔ ቀጥታ ስራየ ሳይሆን ትርፍ ሰአቴን ነዉ የተጠቀምኩበት፡፡ እናም ከቻናል መግባት መዉጣት የባለቤቱ ባለእጁ ዉሳኔ እንጂ ገና ቻናል ሰዉ ወጣ ብየ 100% ሁኜ ልንገራችሁ ለወደፊት የሚዘጋጅ ታሪክ የለም፡፡ብዙ እዉነተኛ ታሪክ በእጄ ነበር ግን ጥቅምና ጉዳቱን ሳነፃፅረዉ ለኔ ስላልተዋጠልኝ ላለመዘጋጀት ወስኜ ትቸዋለሁ፡፡ ይሄም የማይቀየር አቋሜ ነዉ፡፡

ብዙ ሀጃ አለኝ የሰዉ ልጅ ዱንያ ነዉ ይከፋል ይደሰታል..,የኔ መከፋቴ ማዘኔ ጨምሯልና ሙስሊም ወንድማችሁ ነኝ ዱአ አርጉልኝ..,,
እንደበፊቱ አሚር ሰይድ መሆን የማይቻልበት ላይ ነኝ ብቻ በዱአ እንደሚስተካከል አምናለሁ..ነብዩ ሰዐወ ኢማን ይጨምራል ይቀንሳል ብለዋል ኢላህ ኢማኔ እንዲጨምር እናንተም በዱአ አትርሱኝ
መአሰላም

ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሁ ወበረካትሁ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሰላም ያለዉ ህይወት ለመኖር አላስፈላጊ ሰዎችን ከህይወትህ ማስወጣት ይኖርብናል

Join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እስከዛሬ ሙነሺዶችን ተጠንቀቁ ስትል ለእነሱ ያለመረጃ ነዉ እነሱን የመዉቀስ ሞራል የለህም እያለች የምትከራከረኝ ልጅ ነበረች ከዛሬ 3 አመት በፊት...እኔም ንዝንዙ ሲሰለቸኝ የዛሬ ሶሰት አመት አካባቢ በሂደት በጊዜ ብዛት የእሱን ጉድ ትሰሚያለሽ እድሜ ይስጥሽ ብየ ክርክሩን አቁመን ነበር...

ይሄዉ ዛሬ ይሄን Video ላከችልኝ በፊት የተከራከርኩህን አዉፍ በለኝ ብላ......

Video ሳየዉ እኔም ገረመኝ😂 አራት አግቡ ምናምን የሚል ነዉ...ብለዉ ብለዉ በምላሳቸዉ
ነቢይ ነቢይ ብለዉ ሲጨርሱ ይሄዉ በኑሮ ዉድነት  አንድ ማግባት አቅቶት እዳዉን አይቶ ይሄዉ በነሺዳ አግቡ እያሉ መጡ ብለዉ ብለዉ በሰላም እየኖረ ያለ ቤተሰብን ሊበጠብጡ ነዉ☺️

በነገራችን ላይ ይሄ ከአንድ በላይ ማግባት የመቃወም የምፍቀድ ሳይሆን የኢስላም ህግ
ሸሪአ አላህ የፃፈዉ አለ ለሁሉም ድንበር ህግ አለዉ በነሺዳ ሶስት አሪት አግቡ ብሎ የሚወጣ አልነበረም..,,

ሴቶች ሆይ ልብ ይስጣችሁ ..አሁን ሙነሺዶች የያዙት አቋም ከባድ ነዉ በዚህ አካሄዳቸዉ ከሄዴ
ከሁለት ወይ ከሶስት አመት ቡሀላ ከባድ የማይፈታ ችግር በዲነል ኢስላም ላይ ሊያመጡ ይችላሉ..
የሙነሺዶች ችግር ስር ሰዷል ብቻ አሁንም እባካችሁ ሴቶች እየተሸወዱ ነውዉዉዉ....,


📚የዛሬ ሁለት ወይ ሶስት አመት በፊት ስለሙነሺዶች ያልኩትን እስኪ ዛሬም ደግሜ ልላክላችሁ ...አሁን ያለዉ ሁኔታ አንፃር አዉነት ነዉ ወይስ አይደለም??

👇👇👇👇
☞ ብዙ ጊዜ ሙነሺዶችን ተጠንቀቁ እያልክ አንዳንድ ሙነሺዶችንም ስም እየጠራህ በVideo እየፓሰትክ ነዉ ይሄ ለሌላ ሀይማኖት ተከታዮች እርስ በራሳችን ስንናቆር ክፍተት አይሆንም ወይ? አንተስ የመዉቀስ ሞራል አለህ ወይ ? የሚል ከበፊት ጀምሮ በተደጋጋሚ ይሰጠኛል አሁንም ታሪኩ ሲያበቃም ብዙ ሰዉ ፅፎት አንብቢያለሁ እስኪ የተወሰነ ልበል

አንተ ለመዉቀስ ሞራል አለህ ወይ ላላችሁኝ ትክክል ናችሁ ወላሂ ሞራሉ ብቃቱ የለኝም ግን የለኝም ብየ እጄን አጣጥፌ አልቀመጥም ብቻ በነዚህ የጊዜ ወጥመዶች የተዘናጋ ካለ እንዳይዘናጋ ማስጠንቀቅ አለብኝ ለምን እኔን በስመ ፀሀፊ አንድ እዉቀት የሌለኝ ሚስጥራቸዉን የሚነግሩት ሲያጡ ከማዘጋጃቸዉ ፁሁፎች ጋር እራሳቸዉን እየፈተሹ ብዙ ሚስጥር በማስረጃ የነገሩኝ እህቶቼ ጋር የብዙ ሙነሺዶች ገበና ለማወቅ ችያለሁ ..እሺ ማወቅ የለብኝም ነበር??? እና የአሁን ሙነሺድች አንድ ሰዉ ሁነዉ ሁለት ቅርፅ ያላቸዉ ናቸዉ ..እናም እኔ እንደማቀዉ በአደባባይ ወላሂ ከተናገርኩት 1% እንኳን የሚሰሩትን ስራ መች ገለፅኩና ..ብቻ ሙነሺዶች እያልኩ እተች ይሆናል፡፡
ወደዳችሁም ጠላችሁም የአሁን ጊዜ ሙነሺዶችና ሚንበር ቲቪ ይዘዉብን የመጡት ጉድ ከአህባሽ ዘመን ካለፈ የባሰ ፈተና እንደሆነ አንዘንጋ፡፡ ለምን አህባሽ ሲመጣ ብዙ ነገሮችን ከዲን የለቀቁ ይፋ አድርጎ ነዉ ሙነሺዶችና ሚንበር ቲቪ ግን በአህባሽ ዘመን የተጃጃለዉን ወጣት ልቦና ስለሚያቁ ወጣቱን ወደማንነቱ ከመመለስ በነሺዳ ስም ወንድ ሴት እየቀላቀሉ ትዉልድን የከሸፈ ቀለሀ እየሆነ ነዉ፡፡ ሙነሺድ ተብየዎች ደግሞ ታዋቂነት በመጠቀም ብዙ ስራ እየተሰራ ነዉ አላማ ኢላማ በሌላቸዉ በሴቶች ላይ

እሺ ሌላ ማረጋገጫ ልስጣችሁ
ዘንድሮ ኢድ ናሁtv ያየ ካለ አንድ ሙነሺድ(ስሙን መጥቀስ አልፈለኩም ያየ ያቀዋል) ቃለመጠይቅ እየተደረገለት..ነሺዳ የጀመርኩት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በArt ነበር የምማረዉ ሙዚቃ ማጥናቱን ትቼ በዛ መንገድ የኒሽዳን ተማርኩ ብሎ አረ ብዙ ሲያወራ ነበር
ከ15 ቀን በፊት ይመስለኛል በbst tv አንዱ ሙነሺድ ቀርቦ(ስሙን አልገልፅም ያየ ያቀዋል) ገና ነሺዳ ስራ በኢትዮ አልተሰራም በሂክማ ነዉ ሰዉ መማር ያለበት እያለ ሲበጠረቅ ነበር
ለወደፊት ምን ሀሳብ አለህ ሲባል..የነሺዳ መለማመጃ ትቤት መክፈት ነዉ ሀሳቤ ብሎ እርፍ ቁርአን ሂፍዝ መድረሳ ቀረ
አንተ በሂወት ዘመንህ የምታደንቀዉ የምትከተለዉ ሰዉ ሲባል ..ማሂር ዘይን ነዉ ያለዉ..ነቢይ እያለ የሚያቋላምጣቸዉ ቁጥር 1 ብሎ መቼ አደነቀ??
እኔ የሰዉ ትችት ነዉ ያጠነከረኝ እንደማሂር ዘይን በሙዚቃ መሳሪያ ስሰራ ሀራም ነዉ እያሉ ሲተቹኝ ለኔ ግን ብርታት ሆነኝ አለ
ከኒሻዳ ዉጭ ምን ስራ አለህ? ተብሎ ሲጠየቅ እኔ ነሺዳ ቋሚ ስራየ አይደለም ዩቲዱብ አለኝ ይከፈለኛል ብሎ እርፍ መገን ጊዜ
እኔ ብዙ የማቃቸዉ ሙነሺዶች አሉ ደሴ እናም የሚሰሩትን በfb በአካል በተመቸኝ አጋጣሚ እከታተላቸዋለሁ፡፡ ብዘ ነዉ ሚስጥሩ ወዳጆቼ
አንድ አብሮ አደግ ጓደኛየ ቁርአን አብረን የቀራነዉ አሁን ሙዚቀኛ ሁኗል..ግን አዲስ አበባ ሲገባ ነሺዳ አወጣለሁ ብሎ ነበር...ለምን ሙዚቃ አወጣህ ስለዉ ምን ልዩነት አለዉ ..እነ.......ሙዚቃ እንዳወጣ ገፋፉኝ አለኝ..ዛሬ ላይ ታዋቂ ወጣት ሙዚቀኛ ሁኗል ስሙ ግን ይቆይ ለምን ብዙ ሰዉ ያቀዋል
ስንት ወጣት ልጆች ቁርአን ሀፊዞች ነሺዳ እናወጣለን ብለዉ አላማቸዉን ስተዉ የቀሩት?ስንት ሰዉ በእነሱ ተሳነፈ ? ስንት ሰዉ ከቁርአን እራቀ?

ብቻ ሁሉም እራሱን ይፈትሽ
ግን አንዷ እህቴ አንዱን ጠይቃዉ የመለሰዉ መልስ ግን መቼም ቢሆን ሊረሳ አይችልም
.እኔ ተቸገርኩ ሙነሺድ ታዋቂ መሆን አስቸጋሪ ነዉ እራሳቸዉ ሴቶች እየደወሉ እያስቸገሩኝ ነዉ ..ምን ይሻለኛል እስከማለት የደረሰም አለ...
ግን ግራ የሚገባኝ መልስ አልባ ጥያቄዉ ጥፋቱ ከእነሱ ነዉ ወይስ አላማ ኢላማ በተቆረሰ ልብ የምትኖረዉ ሴቷ ትሆን? ብቻ አላህ እዉነተኛን የሙስሊሞች መንገድ ለሁላችንም ይምራን

የአሁን የሙነሺዶች አደረጃጀታቸዉን ተንኮላቸዉን ከፊል የአዲስ አበባ ሰዉ እና 80% የደሴ ከተማ ነዋሪ ያቃል ሁሉም ባለበት ከተማ እነሱ ከዞሩ መጠርጠር አይከፋም

📘 አሁን ላይ በተለይ ሴቱ ስንት ኡስታዝ ደአዋ ከማዳመጥ ስንት ታዋቂ ቃርዕ እያለ ቁርአን ከማዳመጥ የተለያዩ አላማ የሌላቸዉን ሙነሺዶች እያዳመጡ ከመስመር እየሳቱ ነዉ...ሌላዉ ይቅር የእነሱ ጠበቃዎች እነሱን ከተናገርክ አይኔን ግንባር ያርገዉ እያሉ ጠበቃ እየቆሙ እያስተዋልን ነዉ፡፡😊ቆይ ግን ሙነሺዶች እነማን ናቸዉ? ነቢይ እያሉ ፓንክ ባላቶሊ ተቆርጦ ፊዳከ ነቢይ ቢል ነብዩን እየወደደ ሳይሆን ሙድ እየያዘ ነዉ ይሄ ደግሞ በአዳማጩም ሙድ እየያዘ ነዉ
ግን ለምን ሴቶች ሙነሺዶችን ይወዳሉ ?? አንዱ አዲስ ነሽዳ የሚያወጣ አንድ ወጠጤ ያለዉን ስሜን ሳልፅፍ ያለዉን ቃል በቃል አንብቡት ማረጋገጥ የፈለገ ከFB በscreen shoot ስላነሳሁት ልኬለት ማረጋገጥ ይችላል

📥📥"""በቅርብ ቀን እንደ ሙነሺድ__ግጥምና ዜማዉ በኔ የተሰራ አንድ የነሺዳ ነጠላ ዜማ ልልቀቅና ሴቱን ሁላ ላሳብደዉ እያሰብኩ ነዉ ፡፡ ሴቶች ለሙነሺድ ያላቸዉን ፍቅር ካየሁ ቡሀላ የተመኘሁት ታላቅ ሙነሺድ መሆን ብቻ ነዉ ፡፡
መልካም እድል በሉኝ"""'
ይላል እና ነገሩ እንዴት ነዉ 🙄ነሺዳ የሚወጣዉ ለሴቶች ለመወደድ ከሆነስ ከዛስ...ከዛስ ከዛስ....ከዛ ቡሀላ ነገሩ ብዙ ነዉ የደረሰባቸዉ ያቃሉ
...የአሁን ሙነሺዶች አቋማቸዉ የዘነጋችን ሴት ማጥመጃ እንጂ የነቢይ ፍቅር ልባቸዉን ነክቷቸዉ አይደለምምምም....የነብዩ ሰዐወ ፍቅር ቢኖርባቸዉ በአደራሽ አጂ ነብይ ሴት ሰብስበዉ መድረክ ላይ ሁነዉ ጨፍረዉ አያስጨፍሩም ነበር.....
በእልክ የሚሄደዉ ሙስሊም በሙነሺዶች አንድ ቀን በየቤቱ ችግር ይዞ ሲመጣ ከረፈደ ስር ከሰደደ ቡሀላ ይረዳል...አረ ሴቶች የሴት ቤተሰቦች እናስተዉል

📘 ነሺዳ እንዲህ ማለት እንዲህ ሽርክ ነዉ ሀራም ነዉ ሲባሉ ሀራም ነዉ ካለማ የብስ እናናደዉ እየተባለ የባሰ ነሺዳ እያወጡ ሙስሊሙን የማይጠቅም የማይጎዳ ማህበረሰብ እያደረጉ ወደ ጀሀነም መንገድ እነሱ ከፊት ሁነዉ ሌላዉ አብሮ እያጨበጨበ እየሄደ ነዉ

📘 ይቅርታ አርጉልኝና እንኳን የአሁን ነሺዳ ተብየ የድሮዉ የየዋሆቹ ለራሱ ረድ ተሰጥቶበታል፡፡ የአሁንማ ለሴት ለመታወቅ ብለዉ አጨመላለቁት...እኔ አሁን ላይ በሙዚቃ መሳሪያ እያቀነባበሩ ሲያወጡ እነዚህ ሰዎች ምነዉ ፔንጤ ፔንጤ አጫወታቸዉ ነዉ ያልኩት ..ለምን ፔንጤዎች ከክርስትና ተገንጥለዉ ነዉ በሙዚቃ መሳሪያ የጀመሩት...አሁን ያሉት ሙነሺዶች እነደዚሁ በሙዚቃ መሳሪያ ጀምረዋል ነገ ደግሞ እንደ......የማይሁንበት ምን ምክንያት ይኖራል ብቻ አላህ ከነዚህ ሰዎች በላእ ይጠብቀን፡፡

👌አንዱ ክርስቲያን ዘመዴ ነዉ የእናንተም እስልምና በሙዚቃ መሳሪያ እንደ ፔንጤ ዘፈን ጀመራችሁ እንዴ ያለኝ..እነሱ በስሜት ሲጓዙ ክርስቲያኖቹ የሙስሊም ፔንጤ ብለዉ ታምፔላ እንደሰጡ መታወቅ አለበት

📘  እግር በእግር የካፊሮችን መንገድ የሚከተለዉ Member tv የነሺዳ ዉድድር አላቸዉ ቀኑን ባላስታዉስም እቤት እንደአጋጣሚ እዛ ላይ ነበር አንዱ የሆነ አልጫ ወንድ መጣና

   አንድ ነዉ አላህ አንድ ነዉ
አንድ ነዉ አንድ ነዉ አላህ አንድ ነዉ
አንድ ነዉ አላህ አንድ ነዉ
አንድ ነዉ አንድ ነዉ አላህ አንድ ነዉ👇👇
እያለ የፈጠረንን ጌታ በነሺዳ መሳለቂያ ማድረጋቸዉ በጣም አሳዛኝ ነዉ ..ይሄን ብዙ የሌላ ሀይማኖት ተከታዮች ይመለከቱታል ግን በጣም የሚያስጠላዉ ሰዉ ትንሽ ስለተዉሂድ ማወቅ ስንጀምር መልሰዉ ወደ ጠማማ መንገድ መዉሰዳቸዉ ዛሬ በስሜታቸዉ ቢጓዝም ነገ ከሞት ቡሀላ ለሁሉም መልስ አለ..ተጠያቂነት አለ

☞ አንዳንድ ሙነሺዶች አንዳንድ የሌላ ሀይማኖት ተከታዮች Comment ላይ በጣም ደስ ይላል ስላሏቸዉ ለመከራከሪያነት ሌላም ሀይማኖት ይከታተለናል ይላሉ እስኪ እሰቡት አሁን ፔንጤዎች በሙዚቃ መሳሪያ ይዘምራሉ ነሽዳዉ በሙዚቃ ከሆነ ፔንጤ ቢያዳምጠዉ ለእሱ ምንም ልዩነት አይኖረዉምና ይከታተሉታል እነሱ comment ላይ ስለሰጡ ትክክለኛ መስመር መሆናቸዉን ሙነሺዶች ማረጋገጥ አይችሉም...

ብቻ የሆድን ቢያወሩት ሆድ ባዶ ይሆናል እስኪ ነገሩ ብዙ ነዉ ግን በዚሁ ይብቃኝ ሰዉ ያዉቃል የቸገረን የሚተገብረዉ ነዉ ፡፡ እናም የወሬ ሳይሆን የተግባር ሰዎች ያድርገን !!!
Forwarded from ISLAM IS UNIVERSITY
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የነቢይ ወዳጆች ተመልከቱ ..በጀመአ ነቢይ ሙሀመድ ሰዐወ ሲያወድሱ🙄

እነዚህ ናቸዉ ኡማዉን በሂክማ እናስተምራለን ብለዉ ራሳቸዉን ያሳመኑት ሙነሺዶች😒
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሸኽ ሙሀመድ ሀሚዲን መስክሩልኝ ብለዋል!
---------------------

በነሺዳ ስም ሙስሊሙን ማህበረሰብ ወደ ዘፈን እየወሰዱ ላሉ ሁሉ...

ዑለማዎቹ ቁርአኑ ሀዲሱ በሚያዘው ለኡማው እውነታውን አስተላልፈዋል።

አድርሰናል መስክሩ ሲሉም አስመስክረዋል።

ስሜት አሸንፎህ በዘመናዊው ነሺዳ የተለከፍክስ አብሽር!! አላህ ተውበቱን ይወፍቅህ እንልሀለን!!!

ከዛ አልፎ ሀላል ነው በሚል ከዑለማዎቹ በልጦ የሚከራከረውና በዲኑ ያለእውቀት የሚፈተፍተው አላህን ይፍራ!!!

#ኡለማዎቹ_መስክሩ_ብለዋል
#እኛም_አድርሳችኋል_ስንል_መስክረናል

ሌሎች ዑለማዎችም እውነታውን በዚህ መልኩ ለዑማው በማድረስ እውነታውን ማስገንዘብና ማህበረሰቡን መታደግ የግድ ሆኗል!!!
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሙነሺዶች ሲያማቸዉ ተመልከቱ..ይሄ ጉንፋን ይዞት ነዉ...ወይ ታይፎይድ ወይ ሆድ ቁርጠት ቢይዘዉ ምን ሊል ነዉ☺️

ኢስላምን በሂክማ የሚያስተምሩን ተመልከቱ.... ጉንፋን ሲይዛችሁ እንደዚህ ብታንጎራጉሩበት ይለቅ ይሆናል😆

ኢስላምን በሂክማ የሚያስተምሩ እነዚህ ናቸዉ??? ሁሉም ለህሊናዉ ይፍረድ...የክርስቲያን ሀይማኖት መዝሙር የሚዘሞሩት እና የኛ ሙነሺድ ተብየዎች እስኪ አወዳድሯቸዉ...የክርሲቲያኖቹ በጭራሽ በሚዲያ ላይ አይቀልዱም ጌታ ብለዉ ለያዙት ለሀይማኖታቸዉ ክብር አላቸዉ፡፡

የኛ ሙነሺዶች ግን በቃ የሚፈልጉት ዝና እና የዘናገች ሴት ልብ ማድከም ነዉ....

ብቻ አሁን ሙነሺዶች የያዙት አቋም ከባድ ነዉ በጊዜ መባነን ያስፈልጋል⚠️
ሁሉም ያዳምጠዉ ሩቃ ነዉ ፡፡ downlod አርጋችሁ ሁሌም ጠዋትና ማታ ብታዳምጡት አሪፍ ነዉ

Watch "الرقية الشرعية رقية خروج المس وابطال السحر اقوي رقية شرعية شاملة للسحر والمس والعين والحسد" on YouTube
https://youtu.be/Bu8D2hhY_gk
2025/07/03 08:52:26
Back to Top
HTML Embed Code: