tgoop.com/Islam_and_Science/6338
Last Update:
⚡️⚡️ነብዩሏህ ዙልቀርነይን (ዐ.ሰ) ከመሞታቸው በፊት ኑዛዜ ትተው ነበር...
ኑዛዜያቸዉም
ስሞት እጠቡኝ፣ ከፍኑኝ፣ አካሌን ሬሳ ሳጥን ውስጥ አኑሩት፡፡ ነገር ግን እጆቼን ወደ ውጭ ማድረግ እንዳትረሱ፡፡ አገልጋዮቼ ሁሉ ከኋላዬ ይከተሉ፡፡ ንብረቶቼን በበቅሎ ጫኑ፡፡ ምንም እንኳ በብዙ ዓለማዊ ፀጋዎች ተከብቤ ብኖርም፣ ምንም ያህል ትልቅ ኃይል የነበረኝ ሰው ብሆንም ያ ሁሉ አልፎ ወደማይቀረው ዓለም ወደ አኼራ ባዶ እጄን እየሄድኩ መሆኔን ሰው ሁሉ እንዲያይ እፈልጋለሁ፡፡
እጠቀምባቸው የነበሩ ነገሮች ሁሉ አብረውኝ ወደ አኼራ እንዳልተጓዙ ሕዝቤ ይመልከት፡፡ አታላይና ዋሾ በሆነችው ዱንያ እንዳይታለሉ ያደርጋቸዋል፡፡”ብለዉ ስለነበር ከሞቱ ቡሀላ ንዛዜያቸዉ እንዳሉት ሆኖላቸዋል፡፡
አላህ በቁርአን እንደዚህ ማለቱን አስታውስ፡-
ከህዝቡም ሁሉ የተወሰነ ጊዜ አላቸዉ፡፡ጊዚያቸዉም በመጣ ወቅት አንዲትን ሰአት አይቆዩም ከጊዚያቱ አይቀድሙም(አል አዕራፍ 34)
✏️✏️ #ነብዩሏህ_ዙልቀርነይን ለህዝቦቻቸዉ ሲያስተምሩ
እንዲህ ብለዋል
☞ #ቁጣህን_ተቆጣጠር፤ ሸይጧን ከየትኛውም ጊዜ የበለጠ ሰውየውን ለከፉ ድርጊት የሚያነሳሳው በተቆጣበት ወቅት ነው፡፡
☞ #እትቸኩል፣ ከቸኮልከ ማግኘት የሚገባህን ሳታገኝ ትቀራለህ፡፡
☞ላንተ ቅርብም ይሁን እሩቅ ለሰዎች ሁሉ የተመቸህ ሁን፡፡ ከማን አለብኝነት፤ ከክህደት እና ከበደል ተጠንቀቅ!”
ብለዋል፡፡
=======\\=====\\=====\\=====\\\===
✏️✏️ ኸድር #ነብዩላህ_ሙሳ(ዐ.ሰ.) ጋር ተገናኝተው ሲለያዩ ሙሳ ኸድርን ምክር እንዲለግሷቸው ሲጠይቋቸው
ኸድር እንዲህ በማለት መከሯቸው
☞ ሰውን ጠቃሚእንጂ ጎጂ መሆንየለብህም፡፡
☞ ፈገግተኛ እንጂ ቁጡ መሆን የለብህም
☞ ክርክር አታብዛ በሆነው ባልሆነው አትከራከር
☞ ያለምንምጉዳይጉዞ (ዙረት) አታብዛ፣
☞ በሚያስገርምሁኔታ እንጂ በማይረባ ነገር ሳቅ አታብዛ፡፡
ብለዋቸዋል
© አሚር ሰይድ
◈━━━━━━━━◈━━━━━━━━ ◈
4 another channal👇
www.tgoop.com/Islam_and_Science
💐<<<<<<>>>>>>⭐️<<<<<<>>>>>>💐
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6338