tgoop.com/Islam_and_Science/6321
Last Update:
⛔️ አረብ ሀገር፡ ዩኒቨርስቲ ፡ከክፍለሀገር ወጥቼ የተሻለ ከተማ ላይ ነዉ ያለሁት ማንም አያየኝ ብለሽ(ህ)ወንጀል የምትሰሩ ሆይ!!! ትክክል ናችሁ ወንድም እህት አባት እናት ዘመድ ጎረቤት አያያችሁም ግን አሏህ ያያችሆል...በዚና በሀራም ንግድ ላይ የተሰማራችሁ የክፍለ ሀገር ልጆች፡ የአገረብ አገር የምትኖሩ እና ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ወደ አሏህ ተመለሱ....ሞት አማክሮ አይመጣምና፡፡አረብ አገር ያለሽ እህቴ አንዳንዶች በዚና ህይወት ላይ ሁነዉ ብር የሚሰበስቡ እንዳሉ እየሰማን ነዉ ግን እስከ መቼ አስበሽዋል??
☞ አረብ ሀገር ነን እድሜያችን ሄደ ትዳር እንዳያልፈን እያላችሁ በማህበራዊ ሚዲያ ከምታቁትም ከማታቁትም ወንድ ጋር በሚዲያ እያሳለፋችሁ ወንጀል እየሰራችሁ ነዉ ራሳችሁን ፈትሹ....በተዉበት ዛሬዉኑ ወደ አላህ እንመለስ ፡፡ ነገ የእኛ ቀን አይደለምና ላንደረስበት እንችላለን...ነገ ጀናዛ ልንባል እንችላለን እና
⛔️ የሰዉ ሀቅ ይዘሀል(ይዘሻል) በቃ የእናንተ አይደለም መልስ ለባለሀቁ አስደስቱት አለቀ ጉዳዩ ይህ ነዉ ወደ አላህ መመለስ
⛔️ ሶላት በተለያየ ምክንያት አቁማችሁ ይሆናል፡፡ወይም ጊዜዉን እያሳለፍን ይሆናል...ወንድሜ ሆይ በጫት ወይም በማህበራዊ ሚዲያ ሁነህ ጀመአ እያለፈህ ነዉ አይደል ባይሆን ያለፈህ ትናንት ነዉ..,ተዉበት ማለት ከዛሬ ጀምሬ በጀመአ ልሰግድ ብሎ ነይቶ ወደ መስጊድ መንቀሳቀስ ነዉ
⛔️ መጥፎ ጓደኛ አለችሽ አይደል...አላህ የምትቀሰቀሱት የምትወዱት ጋር ነዉ ብለዉናል፡፡ መጀመሪያ ራስሽ ቶብች ወደ አላህ ተመለሽ ...ወደ አላህ ከተመለሽ ቡሀላ ታገይ እሳ እንድትመለስ ድከሚ ጣሪ አብሮ ጀነት ለመግባት...ታገልሽ ካልተሳካልሽ ለተዉበትሽ አደጋ ከሆነች ነገ የዉመል ቂያማ እናት አባት እህት ወንድም የሚፈራራበት ጊዜ ነዉ ነፍሲ ነፍሲ ስለሆነ እነዚህ ቤተሰቦችሽ ለአኼራ ስለማይጠቅሙሽ ከአቅም በላይ ከሆነ ነፍሲ ነፍሲ ብለሽ ራቂያት...አንተም ቢሆን ራቀዉ፡፡እርቃችሁ አላህ ቀልባቸዉን እንዲያስተካክላቸዉ ዱአ አርጉላቸዉ
⛔️ ቤተሰብ ጋር ሆድና ጀርባ ከሆናችሁ፡፡ ዛሬዉኑ እናቴ አባቴ አዉፍ በለኝ ማለት ነዉ፡፡ ነገሮች የተወሳሰቡት አልሳኩ ያሉን በወላጆችን ቀልብ ሊሆን ስለሚችል፡፡ በድለናቸዉ አዉፍ ሳይሉን ሙተዉ ከሆነ ጀነት እንዲወፍቃቸዉ ዱአ ማድረግ ለእነሱ ነይቶ ሰደቃ መስጠት ዚክር ማድረግ...ይሄ ለራሱ የተዉበት ክፍል ነዉ
✏️✏️ አሏህ እኮ ተዉበት እስከምናደርግ እየጠበቀን ነዉ ...,እሱ እንደወነጀላችሁኝ አቃለሁ ሳትሞቱ ተመለሱ ልማራችሁ እያለን እኛ እንቢ ማለት ከቶ የት ለመድረስ ነዉ??የሰዉ ህይወት ታሪክ ሲነበብ ተወለደ ተብሎ ብዙ ከተነገረ ቡሀላ የታሪኩ ማብቂያ ሞተ ተብሎ ነዉ የሚዘጋዉ ወገን
አሏህ ለእኛ ለባሪያዎቹ እንዲህ ብሎናል፡- እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! ከአሏህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አሏህ ሀጢያቶችን በሙሉ ይምራልና፡፡ " ዙመር 53።
📚📚 ዕውቁ የኢስላም ምሁር ሐሰን አል-በስሪ አንድ ጊዜ ጥያቄ ተጠየቁ፡-
“ሰውየው ወንጀልን ይሰራል ከዚያም ተውበት ያደርጋል፤ ነገር ግን ድጋሜ ይመለሳል፡፡ በዚህ ሁኔታ እስከ መቼ ይቀጥላል?” በማለት ጠየቋቸው፡፡
“እሳቸውም ሸይጧን ከእሱ እስኪሰለች'' ድረስ በማለት መለሱ፡፡
ኢንሻ አላህ ከሚያበላን ከሚያጠጣን ከብዙ ሀዘን ጭንቀት ያወጣን...ዛሬስ ይሄን ፈተና አናልፈዉም ብለን እንድናልፍ ካረገን...ጌታ አሏህ ተስፋ አንቆርጥም የሸይጧንን ወስዋስ እናሰለቸዋወን ኢንሻ አላህ
☑️ እህት ወንድሞቼ ለተዉበት ተዘጋጀን ወይ??እስኪ ራሳችንን እንፈትሽ ዛሬ ብንሞት ነገ ጀናዛ ተብለን ተሰግዶብን ቀብር ብንገባ ዛሬ ያለንበት ህይወት ለቀብር ህይወታችን ዋስትና ጀነት ለመግባት የሚያበቃ ኸይር ስራ አለን ወይ??ነገ ቀብር ነን እንበል በተዉበት ወደ እሱ ተመልሰን ነዉ ወይ የምንገናኘዉ ወይስ እስከ ወንጀላችን??
አሏህ በቁርአኑ እንዳለን ቀብር የገቡት በህይወት ብትመልሰን ኑሮ ኸይር ስራ እንሰራ ነበር እንደሚሉት ባሪያዎች ነን ወይ??
ነብዩ ﷺ አንድ ሰዉ ሲሞት ኸይርም ሸርም የሰራ ይቆጫል ሲሉ...እንዴት ሲሏቸዉ ኸይር የሰራዉም
ምነዉ ጨምሬበት በነበር ሲል...ወንጀል የሰራዉም ምነዉ ቶብቼ ኸይር ሰርቼ በነበር ነዉ ቁጭቱ ብለዉናል፡፡
እና እኛ ነገ ከመቆጨት ነገ ከቀብር ጨለማ ምን አለን??ኸይር ስራ ብቻ ሚዛን የሚደፋበት የሚያዋጣበት አኼራን አንዘንጋ፡፡
የእኛ ዉሳኔ ተዉበታችን አላህ ከተቀበለን ቀልባችን ከጠራ ማሊክ ኢብኑ ዲናር አይነት የአላህን ፍራቻ አላህ ቀልባችን ላይ ሊያትምልን ይችላልና ....አይዞን ወደ ቀኝም ወደ ግራም ወደፊትም ወደሆላ ስንዞር ተዉበት ለማድረግ መሰናክሉ ብዙ ነዉ በአራቱም አቅጣጫ በጣጥሰን ወደ አላህ ተመልሰን የአላህን ፍቅር ዉዴታ እናገኛለን...,አይዞን አይዞን አይዞን
ነገ ጀነች ለመግባት ለተዉበት ዝግጁ ነን❔❔❓
━━━━━━━━◈━━━━━━━━ ◈
4 another channal👇
www.tgoop.com/Islam_and_Science
💐<<<<<<>>>>>>⭐️<<<<<<>>>>>>💐
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6321