tgoop.com/Islam_and_Science/6317
Last Update:
«በሽተኛ ሆኖ ከአልጋ ላይ የዋለው የተከበረው ነብይ የአዩብ (ዐ.ሰ) ሚስት ነኝ፡፡ ከእሱ ውጭ ለሌላ ሰው ቀልቤ ተዘንብሎ እያውቅም.. ዘወር በልልኝ ብላዉ እየተጣደፈች ሔደች፡፡
ተመልሳ ስትመጣ የሆነውን ሁሉ ለሰይዱና አዩብ (ዐ.ሰ) ተረከችላቸው፡፡ ሰይዱና አዩብ (ዐ.ሰ) ቅናት ተሰማቸው:: ጨነቃቸው:: የሰሙት ነገር ሠላማቸውን አደፈረሰባቸው፡፡በዛቻ መልክ እንዲህ አሏት፡-
“ረሒማ! እሱን ራቂ አላልኩሽም??አላስጠነቀቅኩሽም ነበር?›› ተሽሏቸው ሲነሱ እንደሚቀጧት በመሐላ አረጋግጠው ነገሯት፡፡ መሻሉ ቀርቶ ቀን በገፋ ቁጥር በሽታው እየጠናባቸው ሔደ፡፡ መዳፎቻቸውን ዘርግተው ወደ ላይ ከፍ አደረጉ፡፡ ወደ ጌታቸው ተጠጉ፡፡ አላህን ፈውስ ጠየቁ፡-
{ ۞ وَأَیُّوبَ إِذۡ نَادَىٰ رَبَّهُۥۤ أَنِّی مَسَّنِیَ ٱلضُّرُّ وَأَنتَ أَرۡحَمُ ٱلرَّ ٰحِمِینَ }
አዩብንም ጌታውን «እኔ መከራ አገኘኝ አንተም ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነህ» ሲል በተጣራ ጊዜ አስታውስ፡፡(አል-አንቢያእ 83)
🎖🎖🎖 ከጎናቸው ሆነው ሲያፅናኗቸው ከነበሩ ወንድሞቻቸው መካከል እንዱ፡-«አንተ የአላህ ነቢይ፡፡ ቤተሰብዎንና ገንዘብዎን በመንጠቅ፤ እንዲሁም ከዛሬ አስራ ስምንት ዓመት በፊት ጀምሮ ጤናዎትን በመውሰድ አላህ ፈትኖዎታል፡፡ አሁንስ በቃዎት ብሎ ከችግርዎ አይገላግልዎትም? ወይስ ማንም ያላወቀው የፈፀሙት ኃጥያት አለ?፡ ብሎ ጠየቃቸው፡፡
.....የሰይዱና አዩብ (ዐ.ሰ) እንዲህ አሏቸዉ:- ወደ አላህ ተጠግቶ ችግርን ማዋየት አቤቱታ አይደለም፡፡ በእሱ ብቻ የመመካት ውጤት ነው፡፡ ሰይዱና ያዕቁብ (ዐ.ሰ)፣ ዩሱፍ (ዐ.ሰ) በጠፉባቸው ጊዜ ጥልቅ በሆነ የህመም እና የመጎዳት ስሜት ተመሳሳይ አቋም ነበር ያሳዩት፡፡ ቁጭት በሞላው አባባል እንዲህ ነበር ያሉት፡-
{ قَالَ إِنَّمَاۤ أَشۡكُوا۟ بَثِّی وَحُزۡنِیۤ إِلَى ٱللَّهِ وَأَعۡلَمُ مِنَ ٱللَّهِ مَا لَا تَعۡلَمُونَ }
ጭንቀቴንና ሐዘኔንና የማሰሙተው ወደ አላህ ብቻ ነው፡፡ ከአላህም በኩል የማታውቁትን ነገር ዐውቃለሁ» አላቸው፡፡(ዩሱፍ 86)
✏️✏️ ከዕለታት አንድ ቀን ረሒማ ምግብ ፍለጋ በወጣችበት አጋጣሚ ጂብሪል ወደ አዩብ (ዐ.ሰ) መጣና እንዲህ በማለት አናገራቸው:-
‹‹አንተ አዩብ! በችግር ተፈትነህ ትዕግስት አድርገሀልና አሁን ጤናህም ሆነ ሌሎች ፀጋዎች በሙሉ ይመለሱልሃል!» ቀጥሎም እንዲህ በማለት አዘዛቸዉ
{ ٱرۡكُضۡ بِرِجۡلِكَۖ هَـٰذَا مُغۡتَسَلُۢ بَارِدࣱ وَشَرَابࣱ }
በእግርህ ምድርን ምታ፡፡ ይህ ቀዝቃዛ መታጠቢያ መጠጥም ነው» ተባለ፡፡(ሷድ 42)
......አዩብ (ዐ.ሰ) የአላህን ትዕዛዝ ተከትለው መሬቱን በእግራቸው መቱ፡፡ ወዲያው ከመሬት ውሀ ፈለቀ፡፡ በምንጯ ውሃ ታጠቡ፡፡ የውጭም የውስጥም በሽታቸው ሁሉ ለቀቃቸው::
በሌላ ዘገባ ደግሞ አዩብ (ዐ.ሰ) መሬቱን በእግራቸዉ ሲመቱት ሁለት ምንጮች መፍለቃቸዉ ተላልፏል አንዱ ሙቅ ሌላኛው ቀዝቃዛ ውሀ ነበር የፈለቀው:: በሙቁ ውሀ ታጥበው ቀዝቃዛውን ውሀ ጠጡት፡፡ ወዲያው ተፈወሱ፡፡
እዚህ ላይ ተዓምሩ ይፈፀም ዘንድ ‹በእግርህ ምታ›› ብሎ አላህ (ሱ.ወ) አዩብን (ዐ.ሰ) ማዘዙ፤ ሥራ እና ጥረት መጠየቁ፣ ትልቅ ትኩረት ያሻዋል፡፡ መልዕክቱ ግልፅ ነው:፡ አንድን ነገር ለማግኘት የእንቅስቃሴው የመጀመሪያ እርምጃ የሚጠበቀው ከእኛ ነው ማለት ነው፡፡ ሳይሠሩና ጥረት ሳያደርጉ እጅና እግርን አጣጥፎ ተቀምጦ ዱዓ ማድረግ ብቻ በቂ አይደለም፡፡ ዱዓ ተቀባይነት እንዲያገኝ ሁሉንም መሥፈርቶች ማሟላት ብቻ ሳይሆን ሥራ መቅደም አለበት፡፡
አዩብ (ዐ.ሰ) በነቢያዊ አደብ ወደ ሐቅ ዞሩ፡፡ ዱዓቸውም ምላሽ አገኘ፡፡ የፈውስ፣ የእዝነት እና የርህራሄ በሮች ፊት ለፊት ተከፈቱላቸው፡፡
በዚህ መሐል ረሒማ ከከተማ ተመለሰች፡፡ ሰይዱና አዩብን አላወቀቻቸውም፡፡ አንድ ጊዜ ወደ ቀኝ፣ እንደገና ወደ ግራ አቅጣጫ ተመልሳለች:: በቃ ጠፍተዋል ብላ አሰበች፡፡ ማልቀስ😢😢 ጀመረች፡፡
“አንቺ ሴት ማንን ፈልገሽ ነው በማለት ሰይዱና አዩብ (ዐ.ሰ) ጠየቋት::
እንድ በሽተኛ ሰው እዚህ ነበር፡፡ የሕይወቴ አጋር ነበር፡፡ ምንም ቢቸግረንና ብንንገላታም እሱን በማገልገሌ ደስተኛ ነበርኩ፡፡ እሱን በመንከባከቤ እረካ ነበር፡፡ አሁን ያን ለቀልቤ የእርጋታ ምንጭ የነበረ ሀብቴን አጣሁት,,አለቻቸዉ
«ሰውየው ምን ዓይነት ነበር, ደግመው ጠየቋት፡፡
‹በጣም ታጋሽ ሰው ነበር፡፡ በጤና እያለ ካንተ ጋር የሚመሳሰል ቁመና ነበረው, ብላ መለሰችላቸው፡፡
‹የእኔ ውድ ረሒማ!❤️ ያ የምትፈልጊው ሰው እኔ ነኝ፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ጤናዬን መለሰልኝ፡፡- አሏት፡፡ በደስታ ተያይዘው አለቀሱ፡፡ ለምስጋናም ወደ አላህ ዞሩ፡፡
✏️✏️✏️ አዩብ (ዐ.ሰ) ወደ ቀድሞው አቅማቸውና ወጣትነታቸው ተመለሱ፡፡ በፊት ከነበራቸው ሀብትና
ልጆች የበለጠ አላህ (ሱ.ወ) ሰጣቸው፡፡ ተበታትኖ ከነበረው የቤተሰብ አባል ጋር ሁሉ ዳግም ለመገናኘት በቁ፡፡ ድካ ለሌለው ደግነት ግልፅ ምስክር ሆኑ፡፡
አዩብ ከበሽታው በተፈወሱባት፣ ሙሉ ጤና ባገኙባት የመጀመሪያዋ ሌሊት ሱህር ላይ ጮኹ፡፡ ለምን? ተበለው ሲጠየቁ እንዲህ አሉ፡-
-ሁልጊዜ ሌሊት በሱህር ወቅት በሽተኛችን እንዴት ነህ?›› የሚል ድምፅ እሰማ ነበር፡፡ ዛሬ ሱህር ደረሰ፡፡ ነገር ግን ያ ድምፅ:- ሙሉ ጤና የተላበስከው ባሪያችን እንዴት ነህ ሊለኝ አልመጣም፡፡ ለዚህ ነበር አ….ህ! ብዬ የጮህኩት!»አሉ የአላህ እዝነት በእርሶ ላይ ይሁን
👌 ላላገባችሁ እንደ አዩብ ሚስት ረሂማ በችግርም በደስታም በዘንም ጊዜ ከጎን ሁና አብሽር የምትለዉን ይስጣችሁ፡፡ እኛ ላገባነዉም ሚስቶቻችንን ቀልባቸዉን መልሶ የረሂማን እዝነት ደግነት ፍቅር በልባቸዉ ያትምላቸዉ...ይሄ ዱአ ይሻላል ሁለተኛ ይስጠን ☺️ከማለት
ለምን ኑሮ ተወዷል ማስተዳደር ከብዷልና
ግን የአሁን ሴቶች ረሒማን ግማሽ መሆኑ የሚችሉ ስንቶች ናቸዉ??በሸቀጥ በብር በሀብት ተገዝተዉ
ያ ሀብት ሲያልቅ ለመፍታት የተዘጋጁ...ሀብታም አግብተዉ ሲሞት ገንዘቡን ለመዉረስ የተዘጋጁ ያለባት ምድር ነች፡፡
ዉበታቸዉን ዲናቸዉን ከሀብታም ብር ለማግኘት የተሳሳተ ጎጆ ለመግባት የተሰለፉበት ዘመን ላይ ነን....
ልብስ እና ቤት የሸፈነዉ ብዙ ነዉ....ወንድ ሆይ ረሒማ መሆን የምትችል ሚስት ምረጥ በሆላ የእሳት እረመጥ እንዳትሆንብህ......
#share #share #share
4 another channal👇
www.tgoop.com/Islam_and_Science
💐<<<<<<>>>>>>⭐️<<<<<<>>>>>>💐
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6317