tgoop.com/Islam_and_Science/6293
Last Update:
>>>>>>🎖🎖#የጀመአ_ሶላት🎖🎖<<<<<
✍ አሚር ሰይድ
💚ሀቡቡና ሰይዱና ሙሀመድ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-አንድ ሰዉ አዘዉትሮ ወደ መስጊድ ሲመላለስ ካያችሁት ኢማን(እምነት)አለዉ ብላችሁ መስክሩለት ብለዋል፡፡
🟢 ሺፋ ቢንት አብዱላህ (ረ.ዐ) እንዲህ ብላለች፡-
“አንድ ዕለት ኡመር ኢብን ኸጧብ (ረዐ) ሊጠይቁን ወደኛ መጡ። ሁለት የቤተሰባችን አባላት ተኝተው ሲመለከቱ እንዲህ በማለት ጠየቁ
"እነዚህ ሰዎች ምን ችግር ኖሮባቸው ነው በፈጅር ሶላት ላይ ከእኔ ጋር በጀማአ ያልሰገዱት?"
....እኔም የምእመናን አዛዥ ሆይ! ወቅቱ ረመዳን ነበርና እነርሱ የተራዊህን ሶላት በጀመዓ ሲሰግዱ ካነጉ በኋላ የፈጅርን ሶላትም አንድ ላይ ሰግደው ነው ወደ መኝታቸው የሄዱት” አልኳቸው፡
ኡመር ግን እንዲህ በማለት ተናገሩ፡-
እስከ ንጋት ድረስ ከመስገድ ይልቅ መስጂድ መጥተዉ ሱብሂን ሶላት ከእኔ ጋር መስገዳቸው ይበልጥ ያስደስተኛል...ብለዋል፡፡
🟡 ኡሙ ደርዳእ (ረ.ዐ) እንደሚከተለው ብላለች፦
“አቡ ደርዳእ (ረ.ዐ) ወደ እኔ ሲመጣ ተናድዶ ነበር፡፡ እኔም ምንድን ነው እንዲህ ያናደደህ ? በማለት ስጠይቀው የሚከተለውን መልስ ሰጠኝ
እኔ የነብዩ ሙሀመድ ﷺ ኡማ (ሕዝብ) የማውቀው ሶላትን በጀማአ በመስገዱ ነው፡፡ ከመካከላቸው አንዱ ጀማዓ ያመለጠው እንደሆነ የሚቀጥለው የሶላት ወቅት እስኪመጣ ድረስ በተከታታይ ሲሰግድ ይቆያል፡፡ የኢሻን ሶላት በጀማዓ ካልሰገደ ራሱን በይበልጥ ይቀጣል። እስኪነጋ ድረስ ምንም ሳያቋርጥ ሲሰግድ ያድራል፡፡ (ኢብን ሐጀር)
አቡደርዳዕ ያናደደዉ ከጀመአ ሶላት ሰዉ ስለቀነሰ ነበር፡፡
🔴 የሀቢቡና ሰይዱና ሙሀመድ ﷺ 💚የተባረኩ ባልደረባዎች አንዱ የነበረው ሐሪስ ቢን ሀሰን (ረ.ዐ) ጋብቻ መሠረተ፡፡ በዚያ ጊዜ አንድ ያገባ ሰው ለብዙ ቀናት ከቤቱ አይወጣም ነበር፡፡ ስለሆነም በተለይ በሱብሂ ሶላት ወቅት ወደ መስጊድ አይሄድም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ሐሪስ (ረ.ዐ) በጫጉላው ሌሊት የፈጅርን ሶላት ሊሰግድ ወደ መስጊድ ሄደ፡፡ ሰዎችም እንዲህ በማለት ጠየቁት፡-
“ባለፈው ምሽት ማግባትህን እናውቃለን፡፡ ታዲያ ቤትህን ለቅቀህ ልትመጣ የቻልከው እንዴት ነው?" እርሱም የሚከተለውን መልስ ሰጣቸው፡-
“በአላህ እምላለሁ! የሱብሂን ሶላት በጀመዓ እንዳልሰግድ የምታግደኝ ሴት ምን የተረገመች ብትሆን ነው''አላቸው (ሀይሰሚ ዘግበዉታል)
🟣 መሐመድ ቢን ሰማድ አላህን በጣም የሚገዛ ሰው ነበር፡፡ በተለይም ደግሞ የጀመዓ ሶላትን በተመለከተ እጅግ በጣም ጠንቃቃ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ እንዲህ ይላል፡-
“ሶላቴን ሁልጊዜም የምሰግደው በጀማዓ ነው፡፡ ለአርባ ዓመታት ያክል የመጀመሪያው የሶላት ተክቢር (ተክቢረተል ኢሕራም) አምልጦኝ አያውቅም፡፡
ግን አንድ ጊዜ ብቻ እናቴን ሳስቀብር የመጀመሪያው ረከዓ አምልጦኛል፡፡ ያችን ያመለጠችኝን ረከዓ ለመተካትና የሙሉ ጀመዓ ሶላትን ምንዳ ለማግኘት አስቤ ያንን ሶላት ሀያ አምስት ጊዜ ያክል ሰገድኩት፡፡ በዚያው ሌሊት በሕልሜ እንዲህ ተባልኩ፡-
“ሙሐመድ ሆይ! ሶላትህን ለሀያ አምስት ጊዜ ያክል ሰገድክ፡፡ ይሁን እንጂ መላእክቶች በጀመዓ ሶላት ጊዜ አሚን' የሚሉትን በምን ታካክሰዋለህ?'' የሚል ህልም አየሁ ብሏል፡፡
🔵 አምር ቢን አብደላህ ሊሞት እያጣጣረ ነበር። ሩሁ ልትወጣ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ ማለቱን ያስተዋሉት ዙሪያውን ያሉት ዘመዶቹ ማልቀስ ጀመሩ። በዚህ መካከል የመግሪብ ሶላት መድረሱን የሚያበስረው አዛን ሲሰማ አምር በዙሪያው ያሉትን ሰዎች እንዲህ አላቸው፡-
......አንሱኝና ልሂድ!"
......ለምንድን ነው የምትነሳው? የት ለመሄድ ነው?'' አሉት፡፡
......“ወደ መስጊድ” አላቸው፡፡
...........እነርሱም በአግራሞት እያስተዋሉት
በዚህ ሁኔታ ላይ እያለህ?'' አሉት፡፡
......አምር ታላቅ ፅናት በሚታይበት መንፈስ እንዲህ አለ፡-
“ሱብሃነሏህ! ለሶላት ጥሪ ሲደረግ እየሰማችሁ አይደለምን? ከዚያ በኋላ መቅረት ይቻላልን? አንሱኝና ልሂድ እባካችሁ"አላቸዉ
በዚህ ዓይነት ሁኔታ ወደ መስጊድ ተወስዶ አንድ ረከዓ ሶላት ከሰገደ በኋላ በሱጁድ ላይ እያለ ነፍሱ ወጣች፡፡
⚡️⚡️⚡️ #ምን_ያማረ_መጨረሻ ነው፡፡ ሀቢቡና ሰይዱና ሙሀመድ ﷺ "እንዳኗኗራችሁ ትሞታላችሁ" ያሉትን ሐዲስ በትክክል ተግባራዊ ያደረገ ክስተት ነበር ይህ የአምር አሟሟት፡፡ በኃያሉ አላህ እዝነት በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለጀመዓ ሶላት ታላቅ ትኩረት ይሰጥ የነበረው ይህ ሰው በሚወደው ሶላት ላይ እያለ ነፍሱ ወጥታለች፡፡
#እኛም የጀመአ ሶላት ያግራልን ...ጀመአ ሶላት እንሂድ እንስገድ የሚል ጓደኛ ወፍቀን ያረብ
join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6293