ISLAM_AND_SCIENCE Telegram 6248
  #ኢኽላስ_ጋ_የተጣመረ_ርዕስ_የሌለው_ጀግንነት
               አሚር ሰይድ

    ለእስልምና መስፋፋትና ማበብ ሕይወታቸውን የገበሩ አያሌ ሙጃሂዶች በኢስላም ታሪክ ላይ በደማቁ ሰፍረዋል። ስማቸው ተዘክሯል፣ገድላቸው ተወስቷል፣ ጀብዳቸው ተተርኳል። ግን ከነዚህ ሙጃሂዶች ባሻገር የአዕላፍ ሙጃሂዶች ገድል ተቀብሯል። ያለእነሱ ያ! ድል ምኞት ነበር። እነርሱም ሙስሊሞች ዘንድ የሚታወሱበትን ስም አልተውም። ራሳቸውን ደብቀው ለነገው ቤታቸው ሰንቀዋል።

   ታላቁ የጦር መሪ መስለማ አብኑ ዐብዱል መሊክ ወደ አንድ የሮማ ከተማ ዘመተ። ከተማዋ ባላት ጠንካራና ብርቱ ምሽግ ምክንያት ለሙስሊሞች ከባድ ሆነች። እንደከበቡ ብዙ ጊዜያት አለፉ። ሮሞች ከምሽጋቸው በስተጀርባ ሆነው ቀስት በመወርወር በሙስሊሞች ላይ ሌላ ራስ ምታት ሆኑ።

መስለማ ከተማዋን የሚከፍትበትን ዘዴ በማሰላሰል እንቅልፍ ከዓይኑ ጠፋ። ጠብ የሚል ሀሳብ ፍለጋ ብዙ ደከመ። ሙስሊሞችም የከበባው ርዝመት፣ የምሽጉ ብርታትና የከሀዲያኑ ቀስት ሞራላቸውን አያላሸቀው መጣ።

እንዲህ ጭንቀቱ በበረታበት አንድ ለሊት ነበር ፊቱን በጨርቅ የሸፈነ ሙጃሂድ ከሙስሊሞች ጦር በድብቅ ተነስቶ ወደ ምሽጉ ያመራው። ፍፁም ጀግንነት የተላበሰ ብቻውን ወደ ምሽጉ ሄደ። እንደደረሰም የምሽጉን ግንብ መቦርቦር ጀመረ። በስተመጨረሻም ተሳካለትና ክፍተት መፍጠር ቻለ  ይህ ሙጃሂድ ስራውን እንዳጠናቀቀ ለማንም ሳያሳውቅ ወደማረፊያው አመራ።
     በማግስቱ ሮሞች ቀስት ለመወርወር ተዘጋጅተዋል ያ ሙጃሂድ ወደ ቦረቦረው ክፍተት ብቻዉን በመሄድ ወደ ከተማው በስውር ዘለቀ። ቀጥታ ወደ በሩ በመሄድ የበሩን ዘበኞች ብቻውን ተፋልሞ በመዘረር ካስወገደ በኋላ በሩን ከፈተ፡፡

ሙስሊሞች የሚያዩትን ማመን አቃታቸው። ለወራት መግቢያ የሌለው አስኪመስላቸው ያለፋቸው የምሽግ በሩ ተከፈተ። ያ ሙጃሂድ ከውስጥ በኩል ብቅ ብሎ “አሏሁ አክበር" በማለት አድማሱን ሲያቀልጠው ሙስሊሞች የሱን ድምፅ ተከትለው “አሏሁ አክበር" እያሉ አስተጋቡ። ሮሞች በድንጋጤ ተሸበሩ። ሙስሊሞችን የሚፋለሙበት ወኔ ከቶውንም ሸሻቸው። የድል ፀሀይ በሙስሊሞች ላይ ፈነጠቀች።

ከድሉ በኋላ የሙስሊሞች መሪ መስለማ ሙጃሂዶቹን ሰበሰበ። “ምሽጉን ከፍቶ የገባው ማነው? ይውጣና ሽልማቱን እንስጠው" በማለት አሳወጀ።
.....ሁሉም በፀጥታ ያን ጀግና ለማየት በጉጉት ይጠባበቃል።ያ! ሙጃሂድ ግን ሽልማቱን በዱንያ ሳይሆን በአኼራ ነበር ማጣጣም ያለመዉና በመስለማ ጥሪ ምሳሹን ነፈገው።
.....መስለማ ዳግም ተጣራ የሚወጣ ግን ማንም አልነበረም። መስለማ ጥሪውን ደጋገመ። በማግስቱ ተጣራ። አሁንም የወጣ የለም።

"በሽንቁሩ የገባውን ሰው በፈለገበት ሰአት ማረፊያዬ አንዲመጣ በአላህ ስም እጠይቀዋለሁ" አለ አንዲመጣና እንዲያየው ከልቡ እየተመኘ።

ከቀትር በኋላ ሰዎች ሲያርፉ ያ ሙጃሂድ ፊቱን እንደሸፈነ ወደ መስለማ ማረፊያ መጣ።
.... መስለማም “አንተ ነህ? " አለው

“አኔ አውቀዋለሁ ግን አንድታውቀወው ከፈለክ ሶስት መስፈርቶች አሉት" አለ መጃሂዱ። መስለማ "ምንድን ናቸው መስፈርቶቹ ? " ሲል ጠየቀ፡፡

☞ ስሙን ላትጠይቀው
☞ ፊቱን ላይገልጥና
☞ ሽልማት ላትሰጠው" አለ። መስለማ ተስማማ። ሙጀሂዱም “እኔ ነኝ” አለና ሌላ ተጨማሪ ቃል ሳይናገር ወጥቶ ሄደ።

መስለማ አይኑ በእምባ ተሞላ። የዚህ ሙጃሂድ ልዕልና የእንባ ከረጢቱን ለመቆጣጠር አቅም አልሰጠውም።


ያ አላህ! ምን ያማረ ኢኽላስ! ከዚያን ቀን ጀምሮ ታዲያ መስለማ ዱዓ ሲያደርግ “ጌታዬ ሆይ! ከዚያ ሰው ጋር ቀስቅሰኝ" እያለ ነበር።

#ምንጭ ☞ ታሪኮችን ተርክላቸዉ መፅሀፍ


join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group



tgoop.com/Islam_and_Science/6248
Create:
Last Update:

  #ኢኽላስ_ጋ_የተጣመረ_ርዕስ_የሌለው_ጀግንነት
               አሚር ሰይድ

    ለእስልምና መስፋፋትና ማበብ ሕይወታቸውን የገበሩ አያሌ ሙጃሂዶች በኢስላም ታሪክ ላይ በደማቁ ሰፍረዋል። ስማቸው ተዘክሯል፣ገድላቸው ተወስቷል፣ ጀብዳቸው ተተርኳል። ግን ከነዚህ ሙጃሂዶች ባሻገር የአዕላፍ ሙጃሂዶች ገድል ተቀብሯል። ያለእነሱ ያ! ድል ምኞት ነበር። እነርሱም ሙስሊሞች ዘንድ የሚታወሱበትን ስም አልተውም። ራሳቸውን ደብቀው ለነገው ቤታቸው ሰንቀዋል።

   ታላቁ የጦር መሪ መስለማ አብኑ ዐብዱል መሊክ ወደ አንድ የሮማ ከተማ ዘመተ። ከተማዋ ባላት ጠንካራና ብርቱ ምሽግ ምክንያት ለሙስሊሞች ከባድ ሆነች። እንደከበቡ ብዙ ጊዜያት አለፉ። ሮሞች ከምሽጋቸው በስተጀርባ ሆነው ቀስት በመወርወር በሙስሊሞች ላይ ሌላ ራስ ምታት ሆኑ።

መስለማ ከተማዋን የሚከፍትበትን ዘዴ በማሰላሰል እንቅልፍ ከዓይኑ ጠፋ። ጠብ የሚል ሀሳብ ፍለጋ ብዙ ደከመ። ሙስሊሞችም የከበባው ርዝመት፣ የምሽጉ ብርታትና የከሀዲያኑ ቀስት ሞራላቸውን አያላሸቀው መጣ።

እንዲህ ጭንቀቱ በበረታበት አንድ ለሊት ነበር ፊቱን በጨርቅ የሸፈነ ሙጃሂድ ከሙስሊሞች ጦር በድብቅ ተነስቶ ወደ ምሽጉ ያመራው። ፍፁም ጀግንነት የተላበሰ ብቻውን ወደ ምሽጉ ሄደ። እንደደረሰም የምሽጉን ግንብ መቦርቦር ጀመረ። በስተመጨረሻም ተሳካለትና ክፍተት መፍጠር ቻለ  ይህ ሙጃሂድ ስራውን እንዳጠናቀቀ ለማንም ሳያሳውቅ ወደማረፊያው አመራ።
     በማግስቱ ሮሞች ቀስት ለመወርወር ተዘጋጅተዋል ያ ሙጃሂድ ወደ ቦረቦረው ክፍተት ብቻዉን በመሄድ ወደ ከተማው በስውር ዘለቀ። ቀጥታ ወደ በሩ በመሄድ የበሩን ዘበኞች ብቻውን ተፋልሞ በመዘረር ካስወገደ በኋላ በሩን ከፈተ፡፡

ሙስሊሞች የሚያዩትን ማመን አቃታቸው። ለወራት መግቢያ የሌለው አስኪመስላቸው ያለፋቸው የምሽግ በሩ ተከፈተ። ያ ሙጃሂድ ከውስጥ በኩል ብቅ ብሎ “አሏሁ አክበር" በማለት አድማሱን ሲያቀልጠው ሙስሊሞች የሱን ድምፅ ተከትለው “አሏሁ አክበር" እያሉ አስተጋቡ። ሮሞች በድንጋጤ ተሸበሩ። ሙስሊሞችን የሚፋለሙበት ወኔ ከቶውንም ሸሻቸው። የድል ፀሀይ በሙስሊሞች ላይ ፈነጠቀች።

ከድሉ በኋላ የሙስሊሞች መሪ መስለማ ሙጃሂዶቹን ሰበሰበ። “ምሽጉን ከፍቶ የገባው ማነው? ይውጣና ሽልማቱን እንስጠው" በማለት አሳወጀ።
.....ሁሉም በፀጥታ ያን ጀግና ለማየት በጉጉት ይጠባበቃል።ያ! ሙጃሂድ ግን ሽልማቱን በዱንያ ሳይሆን በአኼራ ነበር ማጣጣም ያለመዉና በመስለማ ጥሪ ምሳሹን ነፈገው።
.....መስለማ ዳግም ተጣራ የሚወጣ ግን ማንም አልነበረም። መስለማ ጥሪውን ደጋገመ። በማግስቱ ተጣራ። አሁንም የወጣ የለም።

"በሽንቁሩ የገባውን ሰው በፈለገበት ሰአት ማረፊያዬ አንዲመጣ በአላህ ስም እጠይቀዋለሁ" አለ አንዲመጣና እንዲያየው ከልቡ እየተመኘ።

ከቀትር በኋላ ሰዎች ሲያርፉ ያ ሙጃሂድ ፊቱን እንደሸፈነ ወደ መስለማ ማረፊያ መጣ።
.... መስለማም “አንተ ነህ? " አለው

“አኔ አውቀዋለሁ ግን አንድታውቀወው ከፈለክ ሶስት መስፈርቶች አሉት" አለ መጃሂዱ። መስለማ "ምንድን ናቸው መስፈርቶቹ ? " ሲል ጠየቀ፡፡

☞ ስሙን ላትጠይቀው
☞ ፊቱን ላይገልጥና
☞ ሽልማት ላትሰጠው" አለ። መስለማ ተስማማ። ሙጀሂዱም “እኔ ነኝ” አለና ሌላ ተጨማሪ ቃል ሳይናገር ወጥቶ ሄደ።

መስለማ አይኑ በእምባ ተሞላ። የዚህ ሙጃሂድ ልዕልና የእንባ ከረጢቱን ለመቆጣጠር አቅም አልሰጠውም።


ያ አላህ! ምን ያማረ ኢኽላስ! ከዚያን ቀን ጀምሮ ታዲያ መስለማ ዱዓ ሲያደርግ “ጌታዬ ሆይ! ከዚያ ሰው ጋር ቀስቅሰኝ" እያለ ነበር።

#ምንጭ ☞ ታሪኮችን ተርክላቸዉ መፅሀፍ


join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group

BY ISLAMIC SCHOOL


Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6248

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Over 33,000 people sent out over 1,000 doxxing messages in the group. Although the administrators tried to delete all of the messages, the posting speed was far too much for them to keep up. During the meeting with TSE Minister Edson Fachin, Perekopsky also mentioned the TSE channel on the platform as one of the firm's key success stories. Launched as part of the company's commitments to tackle the spread of fake news in Brazil, the verified channel has attracted more than 184,000 members in less than a month. The visual aspect of channels is very critical. In fact, design is the first thing that a potential subscriber pays attention to, even though unconsciously. How to Create a Private or Public Channel on Telegram? A few years ago, you had to use a special bot to run a poll on Telegram. Now you can easily do that yourself in two clicks. Hit the Menu icon and select “Create Poll.” Write your question and add up to 10 options. Running polls is a powerful strategy for getting feedback from your audience. If you’re considering the possibility of modifying your channel in any way, be sure to ask your subscribers’ opinions first.
from us


Telegram ISLAMIC SCHOOL
FROM American