tgoop.com/Islam_and_Science/6217
Last Update:
⚡️ #ከአንበሳ_ጋር_የተናነቀው_ሙጃሂድ
✍አሚር ሰይድ
ሙስሊሞች እና የፐርሽያን ወታደሮች የሠይፍ ትንቅንቅ ቢያደርጉ ሁለቱም በተንጣለለ ሜዳ ላይ ተሰልፈዋል። ከሁለቱም በኩል የሚታየው ትዕይጓት ያስፈራ።
ግጥሚያው ከመጀመሩ በፊት ሁለቱም ቡድኖች ተርታቸውን ይዘው ለጥቂት ደቂቃዎች ከፎከሩ በኋላ ያለምንም ማስጠንቀቅያ ፐርሺያኖቹ የጦር አንበሳቸውን ወደ ሙስለሙ ቀጠና ሰደዱ።
ድልብ አንበሳውም የፐርሺያኖቹን ሠልፍ ሰንጥቆ እየጋለበ ወደሙጃሂዶቹ ሠልፍ መገስገስ ጀመረ። ይህን የተመለከተው ጀግና የሙስለሙን ሠልፍ ሰንጥቆ በመውጣት አንበሳውን ሊጋፈጥ ወደሱ አቀና። ይህ ሲሆን የሁለቱም ሠራዊቶች ትዕይንቱን በዝምታ እየተከታተሉ ነበር። ይህ ጀግና አካሄዱ አንበሳው ሊጋፈጠው ሳይሆን አሱን አጓበሳውን የሚጋፈጥ ነበር የሚመስለው።
አንበሳውም አየጋለበ ሙጃሂዱም እየሮጠ እኩል ሜዳ ላይ ተፋጠጡ። ብልህ ጀግና ነበርና በአንበሳው ጀርባ ላይ በመውጣት ከላዩ ቁጭ ብሎ በሠይፋ ይቆራርጠው ጀመር። በመጨረሻም አንበሳውን ገድሎ ወደ አጋሮቹ ተመለሰ።
ይህን የተመለከቱ የፐርሺያ ሠራዊቶች አንበሳ ከማይፈሩ ህዝቦች ጋር መጋፈጥ ቢከብዳቸውም ሰልፉን ትተው ከመሸሽ መጋፈጥን መርጠው በሙጃሂዶች የሠይፍ እራት ሆነው አደሩ። ሙስሊሞች ድልን ተጎናፀፉ። በጊዜው የጦር አዛዥ የነበረው ጦርነቱ ከተረጋጋ በኋላ አንበሳውን ወደ ገደለው ጀግና በመሄድ ግንባሩን ሳመው።
ያ ጀግናም ከፈረሱ ወርዶ ዝቅ በማለት የጦር አዛዡን በመሳም፦ " ያንተ ዓይነቱ የኔን ግንባር ሊስም አይገባም” ብሎ ኢስላማዊ መተናነስን በታሪክ መዝገብ ላይ አሰፈረልን። ይህ ጀግና ስሙ #ሐሺም_ኢብኑ_ኡትባ ይባል ነበር።
"አናንተ መኖርን አንደምትወዱት መሞትን የሚወዱ ህዝቦችን ይዤላችሁ መጣሁ" በማለት የተናገረው ኻሊድ አብኑል ወሊድ ያለ ምክንያት አልነበረም!
ምንጭ☞ታሪኮችን ተርክላቸዉ መፅሀፍ
ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6217