tgoop.com/Islam_and_Science/6181
Last Update:
ነገር ግን ይሄን ባለማወቅ በብልግናው ረገድ ይኸው እንከብል የተለመደ ሱስ ሆኗል፡፡ ዝሙት እራሱን የቻለ አደገኛ ሱስ ነው፡፡ የእንከብሉ ሱስ ሲታከልበት ደግሞ በሱስ ላይ ሌላ ደባል ሱስ ስለሚሆን አደጋውን አያድርስ ያስብላል፡፡ ታዲያ በፖስትፒል ሱስ የተደፋፈረውና ይበልጥ ለማተረማመስ የልብ ልብ የተሰማው ወጣት ዓላማው ዝሙትን እንተው፤ ከዝሙት እንራቅ የሚለው ሳይሆን ዝሙትን ልማዳችን አድርገን እንውሰድ የሚል ይመስላል፡፡ ለዚህም ማረጋገጫ የፖስትፒል ሱሰኞች መሆናቸው ነው::
📚 ዘመናዊዎቹ የሸገር ወጣቶች በልቅ ወሲብ አየተጫጫሱ ነው፡፡ በአዲስ አበባ በተደረገ ጥናት ወሲብ ፈፅመው ከሚያውቁ 24 ሴቶች ውስጥ ቢያንስ ለአንድ እና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ሁሉም ልቅ ወሲብን ፈፅመዋል። ከእነዚህ ውስጥ
✈ተመርምረን የጋብቻ ጥርጊያ መንገድ እያሰናዳን ስለሆነ የሚል ምክንያት ሶስቱ ያቀረቡ ሲሆን፣
✈ አራቱ በባዶ ወሲብ ከመፈፀማቸው በፊት የኤች.አይ.ቪ የደም ምርመራ ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡
✈17ቱ ግን ቅድመ የደም ምርመራ ሳያከናውኑ አንዴ እና ከዚያ በላይ ለሚሆን ጊዜ በልቅ ወሲብ ተደስተዋል፡፡ ሁሉንም የሚያመሳስላቸው ወሲብ ከፈፀሙ በኋላ ሁሌ ፖስትፒል መጠቀማቸዉን ተናግረዋል፡፡
╔═════════════════╗
🔰 #የሴቶች_ዉርጃ_መበራከት 🔰
╚═════════════════╝
እኤእ የ2014 የውርጃ ዳታ እንደሚያሳየው
☞በመላው ሀገሪቷ 73,167 ውርጃዎች ተካሄደዋል፡፡
☞በአዲስ አበባ ውስጥ ደግሞ 135,999 ውርጃዎች ተፈፅመዋል፡፡ ይህም በቀን በአማካይ 373 ውርጃዎች ይካሄዳሉ ማለት ነው፡፡
✔ አሁን የሚወጡ መረጃዎች ደግሞ በአዲስ አበባ ውስጥ የውርጃ መጠኑ በእጥፍ መጨመሩን ያሳያሉ፡፡
✔ በአፍሪካ ደግሞ በዓመት 8 ሚሊዮን ውርጃ ይፈጸማል፡፡ ከዚህም ውስጥ የኢትዮጵያ ብቻውን አስር ከመቶውን ይዟል፡፡
⚡️⚡️በሙስሊሙ ማህበረሰብ ውስጥ በሁለት ጥንዶች መካከል ከጋብቻ በፊት ብዙውን ጊዜ ያልተፈለገ እርግዝና ሲከሰት እንስማለን፡፡ ታዲያ ይህ ችግር እጅጉን የሰፈና የበዛ በመሆኑ በተለይ በአፍሪካ ቲቪ የፋታዋ ፕሮግራም ላይ በብዛት የሚጠየቀው ይህንኑ ነጥብ አስመልከቶ ነው፡፡ በተጨማሪም በአዲስ አበባ በርካታ ኢማሞች በተደጋጋሚ እየተደወለላቸው ከጋብቻ ውጭ ላረገዙ ሴት ልጆቻቸው ኒካህ እንዲያስሩላቸው በወላጆች ይጠየቃሉ፡፡
╔══════════════════════╗
🔰 #ዓረብ_አገር_ያሉ_ኢትዮጵያዉያን
#ሙስሊሞች_የሚስተዋሉ_ችግር
╚══════════════════════╝
ዓረብ አገር ያሉ ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች ዘንድ ከጋብቻ ዉጭ እያረገዙ ኒካህ ይታሰርንል በማለት በብዛት ሥር ሰድዶ ይገኛል፡፡ ደግሞ ከቁጥጥር ከአቅም በላይ ሥር ሰድዶ የሚገኘው ችግር ማግባትና መፍታት ሱስ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡ አረብ ሀገር አንድ ወንድ ምናልባትም በዓመት ውስጥ በአማካይ ሁለት ጊዜ ይፈታል፤ ሁለት ጊዜ ቀያይሮ ያገባል፡፡ ይህም እንደ ልማድ ተወራርሶ በርካቶች ይህንኑ የሙጥኝ ብለውታል፡፡ እነርሱ ዘንድ መፍታትና ማግባት ውሃ የመጠጣትን ያህል ቀላል ሆኖ ይታያል፡፡
╔══════════════════════╗
🔰 #በአረብ_ሀገር_የኢትዮጲያ_ሴቶች
#በዝሙት_መሰማራት
╚══════════════════════╝
ሌላው ዓረብ ሀገር የተለመደው ችግር የሴቶች ልቅነትና በተለያዩ የዝሙት ሥራ ላይ መሰማራት ነው፡፡ በርካታ ሰዎች እማኝነታቸውን በመናገር እንደገለፁት በተለይ ዱባይ ያሉ ኢትዮጵያዉን ሒጃቢ ሴቶች ሳይቀሩ በየሀገሩ ካሉ ዜጎች ጋር ይማግጣሉ፡፡ ብሎም በርካታ ቋንቋዎችን በአጭር ጊዜ በመማር በርካታ ወንዶችን ማጥመድ እንደቻሉ ይነገራል፡፡ እነዚህ ሴቶች ወንድን የጫማን ያህል በመቀያየር የሚታወቁ ናቸው፡፡ የተለያዩ ቋንቋዎችንም በመናገር ተከነውበታል፡፡
ስራቸው ዚና ብቻ ሁኖ ሀብት የሚያጠራቅሙ በዙ ኢትዮጲያን ዱባይና ሳዑዲአረቢያ እንደሚገኙ ብዙ ሰዎች ምስክረት ሰጥተዋል፡፡ከዚህ ስራ አላህ ተዉበት ወፍቋቸዉ የተገላገሉ ሴቶች በዱባይና በሳዑዲ አረቢያ በጣጣም ልቅነት እንዳለ ይመሰክራሉ፡፡
╔══════════════════════╗
🔰#አባታቸዉ_በዉል_የማይታወቅ_ልጆች_መበራከት
╚══════════════════════╝
የዝሙት ትልቁ መዘዝ ለዝሙት ልጆች መበራከትና ከዚህም የተነሳ በማህበረሰቡ ውስጥ የተለያዩ ወንጀሎች መበራከትና መስፋፋት ነው፡፡
ዝሙት እና አባታቸው በውል የማይታወቁ ልጆች የታጨቁባት ዘመናዊዋ ዓለማችን ምን ደረሰቸ???
ጥናቶች እንደሚያመለከቱት
☞ 40% አሜሪካዉያንና
☞ 50% እንግሊዛዉያን አባቶቻቸውን በውሉ አያውቁም፡፡ (ዓለምን የሚመሩት እነዚሁ መሆናቸውን ልብ ይበሉ፡፡)
☞እንደዚሁም 65% ስዊዘርላንዳዉያን አባቶቻቸውን አያውቁም::
☞ በ እንግሊዝ 2/3ኛው ሕፃናት የሚያድጉት በነጠላ ወላጆች አማካኝነት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እነዚህ ሁሉ ከጋብቻ አልጋ ዉጭ የተወለዱ ናቸው፡፡ የዓለም አባቶቻቸውን በወጉ በማያወቁ ሕዝቦች መመራትም ዝሙት በዓለም አቀፍ ደረጃ ምን ያህል ስር እንደሰደደ ይጠቁማል። ሌላው ጥናት እንዳመለከተው አሁንም 40% እሜሪካዉያን ልጆች የሚወለዱት ከነጠላ ወላጆች (በትዳር ካልተጣመሩ) ነው::
እንግሊዞች ከመቶ ርዕሰ መምህር አንድ አባት ይሻላል የሚል አባባል ቢኖራቸዉም ግን 2/3ህፃናት የሚያድጉት ያለ አባቶቻቸዉ እንክብካቤ ከእናቶቻቸው ጋር ብቻ ነው:
✏️✏️«እንደ ግለሰቦች ሁሉ ሀገር እና ማህበረሰብም ይታመማሉ፡፡ በቶሎ ሕክምና ካለገኙም እንደ ግለሰቦች ሁሉ ሀገርና ማህበረሰብም ይሞታሉ፡፡ (ዶ/ር ዴሚ አሚሮስት)
✏️✏️አንድ ሀገር ታሟል፤ ከባድ ማህበራዊ ውድቀትም ከፊቱ ተደቅኗል.. የሚባለው የማህበረሰቡ አስኳል የሆነው ወጣቱ በተሳሳተ አስተሳሰብ ሲሞላና በተሳሳተ የሕይወት ጎዳና ላይ ሲጓዝ ነው፡፡.. (ዶ/ር ዴሚ አሚሮስት)
#በቀጣይ_ክፍል ስለቦይ ፍሬንድ ገርል ፍርድ የዝሙት መግቢያ መንገድና ...በፊት የቦይፍሬንድ አመጣጥ ከምዕራባዉያን እንዴት ወደኛ ጓዳ እንደገባ እንዳስሳለን
#ምዕራፍ ➒
ይቀጥላል........
አስተያየት ካለ በዚህ ማቀበል ይቻላል
T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6181