tgoop.com/Islam_and_Science/6150
Create:
Last Update:
Last Update:
#ምድራዊውና_ዘልዓለማዊው_ዓለም
ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ “በርግጥ አላህ ሲሳያችሁን በመካከላችሁ እንዳከፋፈለ ሁሉ ሥነ-ምግባራችሁንም በመካከላችሁ ከፋፍሏል፡፡ አላህ ለሚወደው ሰውም ሆነ ለማይወደው ሁሉ ሁበት ይሰጣል፡፡ ሃይማኖትን ኢስላምን ለሚወደው ሰው ካልሆነ በስተቀር አይሰጥም፡፡
አላህ ሃይማኖት የሰጠው ሰው በርግጥ አላህ ወድዶታል፡፡
ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታ እምላለሁ! የአንድ የአላህ ባሪያ ልብና ምላስ ኢስላምን በወጉ እስካልተቀበሉ ድረስ ኢስላምን አይቀበልም፡፡ ጐረቤቱንም ከችግሮቹ ካልጠበቀ አያምንም፡፡" ሰዎችም "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ችግሮቹ ምንድን ናቸው?" ሲሉ ጠየቋቸው፡፡ እሳቸውም “ተንኮሉና በደሉ ናቸው፡፡ አንድ ሰው ገንዘብ አያግኝ፡ በእሱም ይባረክለት ዘንድ ያገኝ ዘንድ ከእሱ አይመፅውት፡፡ ከበስተጀርባውም አይተወውም፡፡ ይህ በራሱ ወደ እሳት የሚከተው ካልሆነ በስተቀር፡፡ አላህ መጥፎ ነገርን በመጥፎ አያጠፋም፡፡ ነገር ግን መጥፎ ነገርን በመልካም ነገር ያጠፋል።"
✍አሚር ሰይድ
join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL

Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6150