tgoop.com/Islam_and_Science/6135
Last Update:
✏️✏️ ሴት ልጅ በተለይ አሁን ቴከኖሎጂው በብዛት ለመጥፎ ነገር ማስፋፈያነት በሚውልበት አግባብ ውስጥ በለየለት እኩይ ወንድ እጅ ከገባች እርሱም ዚናውን እየፈጸመባት በተጓደኝነትም ያንን ትዕይንት ቀርፆት ያስቀምጠዋል፡፡ ወንዱ ይህንን ካደረገ ደግሞ ከዚህ በኋላ የርሷ ነገር በርሱ እጅ ውስጥ ገባ ማለት ነው፡፡ እንደፈለገ ይጫወትባታል፡፡ ያስፈራራታል፤ ያስለቅሳታል፡፡ ከዚህም የተነሳ ሴቷ ለብላክሜይሊንግ (ማስፈራሪያ) ትጋለጣለች፡፡ ይህም ነገር በተውበት ወደ አላህ (ሱ.ወ) እንዳትለመስ ሁሉ ደንቃራ ይሆንባታል፡፡ በዚያ ቪዲዮ ሳቢያም ሴቷ ወደ ጌታዋ ሁሉ መሸሽ የማትችልበት ሁኔታ ያጋጥማታል፡፡
⚡️⚡️ ዝሙተኛ ሴት ለአስከፊው የሴተኛ አዳሪነትና ለወሲብ ንግድ የመጋለጥ ዕድሏ ሰፊ ነው፡፡ በተለይ ጉንተላ የሚበዛባት ከሆነ በቀላሉ ወደዚህ ሥራ ልትገባ ትችላለች፡፡ የሴተኛ አዳሪነት ሥራ ጭንቅላት፣ ተያዥ፣ የሕከምና ማስረጃ፣ የሥራ ፈቃድና የመነሻ ካፒታል ስለማይጠይቅም የዝሙት ሱስ ያለባቸውን ሴቶች የመሳብ ችሎታው ከፍ ያለ ነው፡፡
በአጠቃላይ ሴት ልጅ በዝሙተኛ ወንድ እጅ ገባች ማለት የትዳር አጋሯ ባልሆነ፣ በማይወዳት፣ በማያፈቅራት፣ በማይጠነቀቅላትና በማያዝንላት ሰው እጅ ገባች ማለት ነው፡፡ ይህ የወሲብ መንገደኛም ለራሱ ስሜት እንጂ ለርሷ ደህንነት አንዳችም ነገር አይጨነቅላትም፡፡ ለሚመጣው መዘዝም ኃላፊነቱን አይወስድም፡፡ ጉዳት ሲደርስባትም አብሮነቱን አያሳያትም፡፡ ከዚህም የተነሳ በወሲብ መንገደኛ እጅ የገባች ሴት ለአውሬያዊ አያያዝ ትዳረጋለች፡፡ ይህም ሴቶችን በሁሉም መልኩ ይጎዳቸዋል፡: ዚና ሴቶችን የወሲብ ሕይወታቸውን ብቻ ሳይሆን ሁለንተናዊ ማንነታቸውን ጭምር ያራክሳል፡፡ ከብራቸውን ዝቅ ያደርጋል፡፡በገላቸዉ እንጂ በጭንቅላታቸው እንዳያስቡ ያደርጋቸዋል፡፡ እራሳቸውን እንዲያሻቅጡና አስከፊውን የሴተኛ አዳሪነት ሕይወትን እንዲቀላቀሉ ምከንያት ይሆናቸዋል፡፡ ይህም በመሆኑ ሴቶች በዚና ሳቢያ ከወንዶች በላይ ተጠቂዎችና ተጎጂዎች ሆነው ይገኛሉ፡፡ ለዚህም ሲባል ነው ቁርኣን በዚና ጉዳይ ሴቶችን ያስቀደማቸው፡፡
⚠️⚠️በዚና መስመር ላይ ያለን፡በመንደር ደር ላይ ያለን ከአላህ ጋር እየተጣላን እርዚቃችንን ደስታችንን ከማሸሽ ከዚህ ከዚና አስከፊ በሽታ ሞት ሳይቀድመን ቶብተን እንጠብቀዉ
መታወቅ ያለበት የሴቶች አለባበስ ለራሱ የዚና መንደርደሪያ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል፡፡
👌የዚና ጉዳይ ሲነሳ ተፈራርቶ አይሆንም ለሌሎች ሼር ያርጉ አይታወቅም አንድ ሰዉ ወደ ቀልቡ ተመልሶ ከዚና ቢቶብት ሼር ባደረግንበት ከአጅሩ ተጠቃሚ ሆን ማለት ነዉ
ስለዚና ያተኮሩ ርዕሶች ኢንሻ አላህ ይዘጋጃሉ
join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6135