tgoop.com/Islam_and_Science/6130
Last Update:
#የሱን_እሬሳ_ምድር_አትቀበለዉም
ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺከኢስላም ያፈነገጠውን ሰው ሬሳ ምድር እንደማትቀበል መናገራቸው
የነብዩﷺ ተአምር ጭምር ነዉ፡፡
ኢማም አህመድ እንደዘገቡት አነስ ኢብኑ ማሊክ የሚከተለውን አስተላልፈዋል
የበኒ ነጃር ጎሣ አባል የሆነ አንድ ሰው ከመካከላችን ነበር። አል. በቀራህንና አል ዒምራንን ምዕራፎችን አጠና (ቀራ)፡፡ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ፀሐፊ ነበር። ከሙስሊሞች ሸሽቶ ሄደና ከክርስቲያኖች ጋር ተቀላቀለ"
ክርስቲያኖቹም የሙሐመድ ራዕይ ፀሐፊ ነበር» በማለት የክብር ቦታ ሰጡት፡ብዙም ሳይቆይ ሞተ። ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት። ምድር ግን አልተቀበለችውም ተፋችው። እንደገና ቀበሩት አሁንም ተፋችው። ከዚያ በኋላ ግን ሳይበብሩ ተውት።
ይህ የሆነበትን ምክንያት ዐብባስ ሲናገሩ፡ ይህ ሰው በቀራንና አል ዒምራንን ያጠና (የቀራ) በመሆኑ እኛም ለርሱ ልዩ ክብር ነበረን። የአላሀ መልዕክተኛ ﷺ «መሐሪና አዛኝ» የሚል ቃል እንዲፅፍ ሲያዙት «መሐሪና ጥበበኛ» እያለ ይፅፋል። ወዋቂና ጥበበኛ» ብሎ እንዲጽፍ ሲያዙት፡ «ሰሚና ተመልካች» ብዬ ልፃፍ ይላቸዋል...
«ይህ ሰው ከኢስላም አፈነገጠና ከጣዖታውያን ወገነ። «ስለ ሙሐመድ ልንገራችሁ። ራዕይ ፀሐፊው ነበርኩ። የፈለግኩትን ነበር የምጽፈው» በማለት የነቢዩን ስም ማጥፋት! የሐሰት ጥላሸት መቀባት ጀመረ።
ይህ ሰዉ ሲሞት ነብዩ ﷺ ምድር አትቀበለዉም በማለት ተናገሩ።
አነስ እንዳሉት አቡ ጦልሐ ሰውየው ወደሞተበት ሀገር መሄዱን ነግሮኛል። ሜዳ ላይ ተጥሎም አገኘው። «የዚህ ሰዉ ነገር ምንድን ነው?» ሲል ጠየቀ። «ደጋግመን ብንቀብረውም ምድር ልትቀበለው አልፈቀደችም። መልሳ እየተፋች አስቸገረችን» አሉት
♦ቡኻሪ አነስን በመጥቀስ እንደዘገቡት፡ ሰውየው ክርስቲያን ነበር ሰለመ። በቀራንና አል ዒምራንም አጠና። የነቢዩ ፀሐፊም ሆነ። ተመልሶም ወደ ክርስትና ገባ። ሙሐመድ እኔ የፃፍኩለትን ብቻ እንጅ ሌላ ነገር አያውቅም» ይል ነበር። አላህ ይህን ሰው ገደለው፡፡ ቀበሩት። ምድርም ተፍታው አደረች።
«ይህ የሙሐመድና የባልንጀሮቹ ድርጊት ነው። ከነርሱ ስለሽሽ ከመቃብሩ አውጥተውት ነው» አሉ፡፡ ይበልጥ ጥልቅ ጉድጓድ ቆፍረውም ቀበሩት። ምድር በድጋሜ ተፍታው አደረች። «ይሀ የሙሐመድ እና የባልንጀሮቹ ድርጊት ነው። ከነርሱ ስለሽሽ ሬሳውን አውጥተው ጣሉት» አሉ። ይበልጥ ጥልቅ የሆነ ጉድጓድ ቆፈሩና ቀበሩት። ምድር ለሶስተኛ ጊዜ ተፋችው" በዚህ ጊዜ የሰው ድርጊት እንዳልሆነ አወቁና ሬሳውን ወረወሩት፡፡
ሱበሀነሏህ!!!
https://www.tgoop.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6130