tgoop.com/Islam_and_Science/6128
Last Update:
#አሳፋሪ_ጥያቄና_አጥጋቢ_መልስ
✍አሚር ሰይድ
ከዕለታት አንድ ቀን ሮማዊው _ ቄሳር _ ለሙዓዊያህ (ረ.ዐ) የሚከተለውን የደብዳቤ መልዕክት ላከለት፡፡ “አቅጣጫ፣ አባት የሌለዉ፣ ወላጅ ስሌለው፥ ቀብሩ ውስጥ ደስተኛ ስለሆነው በማህፀን ውስጥ ስላልተፈጠሩ ሶስት ነገሮች ሙሉ፣ ግማሽና ባዶ ስለሆነ ነገሮች ንገረኝ። የማናቸውንም ነገሮች መፈጠሪያ ዘር የሆነችውንም በብልቃጥ አድርገህ ላክልኝ።''
ሙዓዊያህ (ረ.ዐ) የደብዳቤውን መልዕክት ካነበበ በኋላ መልስ ይሰጡበት ዘንድ መልዕክቱን ለዑብደላህ ኢብነ ዐብባስ (ረ.ዐ) ላከው፡፡
ዐብደላህ ኢብነ- ዕብባስ (ረ.ዐ) የደብዳቤውን መልዕክት አንብበው የሚከተለውን ምላሽ ለሮማዊው ቄሳር ፃፉለት፡፡
☞“አቅጣጫ የሌለው ነገር የተከበረው ከዕባህ ነው፡፡
☞ አባት የሌለው ዒሳ(ዐሰ) (ኢየሱስ)ናቸው፡፡
☞ወላጅ የሌለው አደም (ዐ.ሰ) ናቸው፡፡
☞በቀብሩ ውስጥ ደስተኛ የሆነው ዩኑስ (ዐ.ሰ) ናቸው።
☞ በማህፀን ውስጥ ያልተፈጠሩት ሦስት ነገሮች
➊ የነብዩላህ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) በግ
➋የነብዩላህ ሷሊሕ ሴት ግመልና
➌የነብዩላህ ሙሳ (ዐ.ሰ) ዘንዶ ናቸው።
☞ሙሉ የሆነው ነገር አእምሮ ኖሮት በዚህ አእምሮው የሚጠቀም ሰው ሲሆን፥ ግማሹ ነገር አእምሮ የሌለው ግን አእምሮ ባላቸው ሰዎች የሚሠራ ሰው ነው፡፡
☞ ባዶ ነገር ደግሞ አእምሮ የሌለውና አእምሮ በሌላቸው ሰዎች አእምሮ የሚሠራ ነው፡፡
ከዚያ በአንዲት ብልቃጥ ውስጥ ውሀ ከሞሉ በኋላ “ይህች የማናቸውም ነገሮች መፈጠሪያ ዘር ነች በማለት ከፃፉለት በኋላ መልዕክቱን ወደ ቄሳር ላኩት።
ቄሳሩ ዐብደላህ ኢብኑ ዐብባስ (ረ.ዐ) በሰጡት ምላሽ በጣም ተደነቀ።
join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6128