ISLAM_AND_SCIENCE Telegram 6117
#ምን_የቀረ_ምክር_አለ⁉️
     አሚር ሰይድ

ኻሊድ ኢብኑ ወሊድ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት አንድ የገጠር ሰው ወደ አላህ መልዕክተኛ ﷺ መጣና “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! በምድርም ሆነ በዘልአለማዊው ዓለም (አኺራህ) የሚጠቅመኝ ነገር ልጠይቅህ መጣሁ” አላቸው፡፡ እሳቸውም “ያሻህን ጠይቅ" አሉት፡፡

እሱም
ከሰዎች በላይ አዋቂ ለመሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡ እሳቸውም
>>“አላህን ፍራ ከሰዎች በላይ አዋቂ ትሆናለህ' አሉት፡፡

ከሰዎች የበለጥክ ሀብታም ለመሆን እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>“አላህ የሰጠህን ነገር በፀጋ የምትቀበል ሁን፤ ከሰዎች የበለጥክ ሁብታም ትሆናለህ" አሉት፡፡

“ከሰዎች የበለጠ ፍትሀዊ  ሰው መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ለራስህ የምትወደውን ለሌሎች ሰዎች ውደድ! ከሰዎች የበለጠ ፍትሀዊ ሰው ትሆናለህ' አሉት፡፡

ከሰዎች የበለጥኩ መልካም መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>"ለሰዎች ጠቃሚ ሁን፤ ከሰዎች በበለጠና መልካም ትሆናለህ" አሉት፡፡

ከሰዎች በበለጠ ወደ አላህ የቀረብኩ መሆን እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>“አላህን ማስታወስን አብዛ፣ ከሰዎች በበለጠ ለአላህ የቀረብክ ትሆናለህ" አሉት፡፡

እምነቴ ምሉእ እንዲሆን እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>“ሥነ-ምግባርህን መልካም አድርግ ! እምነትህ ምሉእ ይሆናል" አሉት፡፡

መልካም ከሚፈፅሙት መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>"አላህ የማታየው ብትሆንም እንኳ እሱ ያይሃልና እንደምትመለከተው አድርገህ ተገዛው፧ መልካም ከሚፈጽሙት ሰዎች መሆን ትችላለህ" አሉት፡፡

“አላህን በቅን ከሚታዘዙት መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው::
>>“አላህ ግዴታ ያደረገብህን ተግባራት ፈፅም፣ አላህን በቅን ከሚታዘዙት ትሆናለህ" አለት፡፡

“አላህን ከኃጢአት የጠራሁ ሆኜ ለመገናኘት እፈልጋለሁ አላቸው፡፡
>>“ሚስትህ ጋር ግብረ-ሥጋ ግንኙነት ከፈፀምክ በኋላ ለመንፃት ብለህ ታጠብ፤ ከኃጢአት የፀዳህ ሆነህ አላህን ትገናኘዋለህ" አሉት፡፡

“በትንሳኤ ቀን (የውመል ቂያማህ) ብርሃን ውስጥ ሆኜ ከሞት መቀስቀስ እፈልጋለሁ'' አላቸው፡፡
>>“ራስህን አትበድል፤ ማንንም ሰው አትበድል፡ በትንሳኤ ቀን በብርሃን ውስጥ ሆነህ ትቀሰቀሳለህ" አሉት፡፡

ጌታዬ በትንሳኤ ቀን እንዲያዝንልኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “ለራስህ እዘን፤ ለባሪያዎቹም እዘን፤ በትንሳኤ ቀን ጌታህ ያዝንልሃል" አሉት፡፡

ኃጢአቶቼ እንዲያንስልኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “ምሕረት መጠየቅን አብዛ፤ ኃጢአቶችህ ያንሱልሃል" አሉት፡፡

"ከሰዎች በበለጠ ቸር ለመሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ችግሮችህን ለፍጡራን አቤት አትበል፤ ከሰዎች በበለጠ ቸር ትሆናለህ" አሉት፡፡

"ከሰዎች በበለጠ ብርቱ መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>"በአላህ ላይ ተመካ፤ ከሰዎች በበለጠ ብርቱ ትሆናለህ" አሉት፡፡

“አላህ ሲሳዬን እንዲያሰፋልኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ንፅሕናን አብዛ፤ አላህ ባንተ ላይ ሲሳይህን ያሰፋልሃል'' አሉት፡፡

“አላህንና መልዕክተኛውን ከሚወዱ ሰዎች መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“አላህና መልዕክተኛ የሚወዱትን ውደድ፤ አላህንና መልዕክተኛውን ከሚወዱ ሰዎች ትሆናለህ" አሉት፡፡

“በትንሳኤ ቀን ከአላህ ቅጣት የተጠበቅኩ መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “አላህ ከፈጠራቸው ፍጡራኖች በአንዱም ላይ አትበሳጭ" አሉት፡፡

“ዱዓዬ ተቀባይነት እንዲያገኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ሁሉንም ክልክል የሆኑ ነገሮች ከመመገብ ራቅ፧ ዱዓህ ተቀባይነትን ያገኛል" አሉት፡፡

“ጌታዬ በትንሳኤ ቀን እንዳያጋልጠኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “በትንሳኤ ቀን ጌታህ እንዳያጋልጥህ ከፈለግክ ብልትህን ከዝሙት ጠብቅ” አሉት፡፡

“ጌታዬ በትንሳኤ ቀን ገመናዬን እንዲደብቅልኝ እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>የወንድሞችህን ገመና ደብቅ፡ አላህ ያንተን ገመና በትንሳኤ ቀን ይደብቅልሃል" አሉት፡፡

ከኃጢአቶችና ከስህተት ነፃ የሚያደርግ ነገር ምንድን ነው?” አላቸው፡፡
>>"እንባ፣ ቅን ታዛዥነትና በሽታዎች ናቸው" አሉት፡፡

በአላህ ዘንድ በላጩ ምንዳ የትኛው ነው? አላቸው፡፡
>>“መልካም ሥነ-ምግባር፣ መተናነስና በመከራ ጊዜ ትዕግስት ማድረግ ናቸው˚ አሉት፡፡

በአላህ ዘንድ በጣም ትልቁ ኃጢአት የትኛው ነው?" አላቸው፡፡
>>መጥፎ ሥነ-ምግባርና ስግብግብነት ናቸው አሉት፡፡

በምድራዊውና በዘልዓለማዊጡ ዓለማት የአላህን ቁጣ የሚያበርዱ ነገሮች የትኞቹ ናቸው?" አላቸው::
>> "በድብቅ የምትሰጥ ሰደቃህ (ምፅዋት) እና ዝምድናን መቀጠል ናቸው" አሉት፡፡

በትንሳኤ ቀን የጅሀነምን እሳት የሚያጠፋ ነገር ምንድን ነው?" አላቸው፡፡
>>“በምድራዊው ዓለም ችግርና መከራ ሲያጋጥም ትዕግስት ማድረግ ነው” አሉት፡፡"

ሀምሌ17/11/2016
ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group



tgoop.com/Islam_and_Science/6117
Create:
Last Update:

#ምን_የቀረ_ምክር_አለ⁉️
     አሚር ሰይድ

ኻሊድ ኢብኑ ወሊድ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት አንድ የገጠር ሰው ወደ አላህ መልዕክተኛ ﷺ መጣና “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! በምድርም ሆነ በዘልአለማዊው ዓለም (አኺራህ) የሚጠቅመኝ ነገር ልጠይቅህ መጣሁ” አላቸው፡፡ እሳቸውም “ያሻህን ጠይቅ" አሉት፡፡

እሱም
ከሰዎች በላይ አዋቂ ለመሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡ እሳቸውም
>>“አላህን ፍራ ከሰዎች በላይ አዋቂ ትሆናለህ' አሉት፡፡

ከሰዎች የበለጥክ ሀብታም ለመሆን እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>“አላህ የሰጠህን ነገር በፀጋ የምትቀበል ሁን፤ ከሰዎች የበለጥክ ሁብታም ትሆናለህ" አሉት፡፡

“ከሰዎች የበለጠ ፍትሀዊ  ሰው መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ለራስህ የምትወደውን ለሌሎች ሰዎች ውደድ! ከሰዎች የበለጠ ፍትሀዊ ሰው ትሆናለህ' አሉት፡፡

ከሰዎች የበለጥኩ መልካም መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>"ለሰዎች ጠቃሚ ሁን፤ ከሰዎች በበለጠና መልካም ትሆናለህ" አሉት፡፡

ከሰዎች በበለጠ ወደ አላህ የቀረብኩ መሆን እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>“አላህን ማስታወስን አብዛ፣ ከሰዎች በበለጠ ለአላህ የቀረብክ ትሆናለህ" አሉት፡፡

እምነቴ ምሉእ እንዲሆን እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>“ሥነ-ምግባርህን መልካም አድርግ ! እምነትህ ምሉእ ይሆናል" አሉት፡፡

መልካም ከሚፈፅሙት መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>"አላህ የማታየው ብትሆንም እንኳ እሱ ያይሃልና እንደምትመለከተው አድርገህ ተገዛው፧ መልካም ከሚፈጽሙት ሰዎች መሆን ትችላለህ" አሉት፡፡

“አላህን በቅን ከሚታዘዙት መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው::
>>“አላህ ግዴታ ያደረገብህን ተግባራት ፈፅም፣ አላህን በቅን ከሚታዘዙት ትሆናለህ" አለት፡፡

“አላህን ከኃጢአት የጠራሁ ሆኜ ለመገናኘት እፈልጋለሁ አላቸው፡፡
>>“ሚስትህ ጋር ግብረ-ሥጋ ግንኙነት ከፈፀምክ በኋላ ለመንፃት ብለህ ታጠብ፤ ከኃጢአት የፀዳህ ሆነህ አላህን ትገናኘዋለህ" አሉት፡፡

“በትንሳኤ ቀን (የውመል ቂያማህ) ብርሃን ውስጥ ሆኜ ከሞት መቀስቀስ እፈልጋለሁ'' አላቸው፡፡
>>“ራስህን አትበድል፤ ማንንም ሰው አትበድል፡ በትንሳኤ ቀን በብርሃን ውስጥ ሆነህ ትቀሰቀሳለህ" አሉት፡፡

ጌታዬ በትንሳኤ ቀን እንዲያዝንልኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “ለራስህ እዘን፤ ለባሪያዎቹም እዘን፤ በትንሳኤ ቀን ጌታህ ያዝንልሃል" አሉት፡፡

ኃጢአቶቼ እንዲያንስልኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “ምሕረት መጠየቅን አብዛ፤ ኃጢአቶችህ ያንሱልሃል" አሉት፡፡

"ከሰዎች በበለጠ ቸር ለመሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ችግሮችህን ለፍጡራን አቤት አትበል፤ ከሰዎች በበለጠ ቸር ትሆናለህ" አሉት፡፡

"ከሰዎች በበለጠ ብርቱ መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>"በአላህ ላይ ተመካ፤ ከሰዎች በበለጠ ብርቱ ትሆናለህ" አሉት፡፡

“አላህ ሲሳዬን እንዲያሰፋልኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ንፅሕናን አብዛ፤ አላህ ባንተ ላይ ሲሳይህን ያሰፋልሃል'' አሉት፡፡

“አላህንና መልዕክተኛውን ከሚወዱ ሰዎች መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“አላህና መልዕክተኛ የሚወዱትን ውደድ፤ አላህንና መልዕክተኛውን ከሚወዱ ሰዎች ትሆናለህ" አሉት፡፡

“በትንሳኤ ቀን ከአላህ ቅጣት የተጠበቅኩ መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “አላህ ከፈጠራቸው ፍጡራኖች በአንዱም ላይ አትበሳጭ" አሉት፡፡

“ዱዓዬ ተቀባይነት እንዲያገኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ሁሉንም ክልክል የሆኑ ነገሮች ከመመገብ ራቅ፧ ዱዓህ ተቀባይነትን ያገኛል" አሉት፡፡

“ጌታዬ በትንሳኤ ቀን እንዳያጋልጠኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “በትንሳኤ ቀን ጌታህ እንዳያጋልጥህ ከፈለግክ ብልትህን ከዝሙት ጠብቅ” አሉት፡፡

“ጌታዬ በትንሳኤ ቀን ገመናዬን እንዲደብቅልኝ እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>የወንድሞችህን ገመና ደብቅ፡ አላህ ያንተን ገመና በትንሳኤ ቀን ይደብቅልሃል" አሉት፡፡

ከኃጢአቶችና ከስህተት ነፃ የሚያደርግ ነገር ምንድን ነው?” አላቸው፡፡
>>"እንባ፣ ቅን ታዛዥነትና በሽታዎች ናቸው" አሉት፡፡

በአላህ ዘንድ በላጩ ምንዳ የትኛው ነው? አላቸው፡፡
>>“መልካም ሥነ-ምግባር፣ መተናነስና በመከራ ጊዜ ትዕግስት ማድረግ ናቸው˚ አሉት፡፡

በአላህ ዘንድ በጣም ትልቁ ኃጢአት የትኛው ነው?" አላቸው፡፡
>>መጥፎ ሥነ-ምግባርና ስግብግብነት ናቸው አሉት፡፡

በምድራዊውና በዘልዓለማዊጡ ዓለማት የአላህን ቁጣ የሚያበርዱ ነገሮች የትኞቹ ናቸው?" አላቸው::
>> "በድብቅ የምትሰጥ ሰደቃህ (ምፅዋት) እና ዝምድናን መቀጠል ናቸው" አሉት፡፡

በትንሳኤ ቀን የጅሀነምን እሳት የሚያጠፋ ነገር ምንድን ነው?" አላቸው፡፡
>>“በምድራዊው ዓለም ችግርና መከራ ሲያጋጥም ትዕግስት ማድረግ ነው” አሉት፡፡"

ሀምሌ17/11/2016
ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group

BY ISLAMIC SCHOOL


Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6117

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

The creator of the channel becomes its administrator by default. If you need help managing your channel, you can add more administrators from your subscriber base. You can provide each admin with limited or full rights to manage the channel. For example, you can allow an administrator to publish and edit content while withholding the right to add new subscribers. Telegram iOS app: In the “Chats” tab, click the new message icon in the right upper corner. Select “New Channel.” Commenting about the court's concerns about the spread of false information related to the elections, Minister Fachin noted Brazil is "facing circumstances that could put Brazil's democracy at risk." During the meeting, the information technology secretary at the TSE, Julio Valente, put forward a list of requests the court believes will disinformation. Hui said the messages, which included urging the disruption of airport operations, were attempts to incite followers to make use of poisonous, corrosive or flammable substances to vandalize police vehicles, and also called on others to make weapons to harm police. Telegram message that reads: "Bear Market Screaming Therapy Group. You are only allowed to send screaming voice notes. Everything else = BAN. Text pics, videos, stickers, gif = BAN. Anything other than screaming = BAN. You think you are smart = BAN.
from us


Telegram ISLAMIC SCHOOL
FROM American