tgoop.com/Islam_and_Science/6113
Last Update:
#ኑዓይም_ኢብኑ_መስዑድ
✍ አሚር ሰይድ
ስለ ኑዓይም ኢብኑ መስዑድ ምን ያህሎቻችን እናቃለን??
ኑዓይም ኢብኑ መስዑድ አዕምሮውንና በሳልነቱን በኸንደቅ ዘመቻ ጊዜ ሙስሊሞችን ለማጥፋት የተሰበሰቡትን አህዛቦች (ሙሽሪኮች ገጥፋኖችን፤ በኒ ቁረይዟዎችን) ለመበታተንና አንድነታቸውን ለማፈራረስ ተጠቅሞበታል፡፡ ታሪኩን ኢብኑ ኢስሀቅ እንዲህ ይተርክልናል
በአህዛብ ዘመቻ ጊዜ ረሱል ﷺ ባልደረቦቻቸዉ እጅግ በአስቸጋሪና አስጨናቂ ሁኔታ ላይ ሆነዉ ቆዩ፡፡የሁኔታዉን አስቸጋሪነት አላህ ሱ.ወ በቁርአን እንዲህ በማለት ገልፆታል፡-
{ إِذۡ جَاۤءُوكُم مِّن فَوۡقِكُمۡ وَمِنۡ أَسۡفَلَ مِنكُمۡ وَإِذۡ زَاغَتِ ٱلۡأَبۡصَـٰرُ وَبَلَغَتِ ٱلۡقُلُوبُ ٱلۡحَنَاجِرَ وَتَظُنُّونَ بِٱللَّهِ ٱلظُّنُونَا۠ }
ከበላያችሁም ከናንተ በታችም በመጡባችሁ ጊዜ፣ ዓይኖችም በቃበዙ፣ ልቦችም ላንቃዎች በደረሱና በአላህም ጥርጣሬዎችን በጠረጠራችሁ ጊዜ ያደረገላችሁን አስታውሱ፡፡(ሱራህ አህዛብ 10)
በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ ኑዓይም ኢብኑ መስዑድ ከረሱል ﷺ ዘንድ መጥቶ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! እኔ ሰልሜያለሁ ህዝቦቼ መስለሜን አያወቁም የፈለጉትን ይዘዙኝ አላቸው፡፡ ረሱልም ﷺ “አንተ በእኛ ውሰጥ አንድ ሰው ነህ ከእኛ ጋር ሆነሃል ከቻልክ ከእኛ እነሱን አጣላልን በታትንልን።ጦርነት ማለት ማታለል ነው›› አሉት፡፡
....ከዚያም ኑዓይም በኒቁረይዟዎች ዘንድ መጣ እሱ በጃሂሊያ ጊዜ መጠጥ አጣጫቸውና ወዳጃቸው ነበር። ከዚያም “በኒቁረይዟዎች ሆይ! ለእናንተ ያለኝን ፍቅር ታውቃላችሁ በተለይ በእኔና በናንተ መካከል ያለውን ፍቅር ታውቃላችሁ አላቸው፡፡ እውነት ብለህል አንተ ከእኛ ጋር የምትጠረጠር አይደለህም አሉት:: ከዚያም እንዲህ አላቸው፡-ቁረይሾችና ገጥፋኖች እንደናንተ አይደሉም። ጦርነት የጀመራችሁበት ሀገር ሀገራችሁ ነው:: ገንዘቦቻችሁ ልጆቻችሁ ሴቶቻችሁ ያሉት እዚሁ ነው:: ከዚህ ሀገር ወደ ሌላ ሀገር መቀየር (መሸሽ) አትችሉም:: ቁረይሾችና ገጥፋኖች ሙሀመድን ለመዋጋት መጥተዋል፡፡ እናንተም አግዛችኋቸዋል:: ነገር ግን የእነሱ ገንዘባቸው ልጆቻቸውና ሴቶቻቸው ያሉበት ቦታ ራቅ ያለ ነው:: በጦርነቱ መልካም ድል ካገኙ ይጠቀሙብታል። ከዚህ ውጭ ከሆነ ወደ ሀገራቸው ይሸሻሉ፡ እናንተን ለሙሀመድ አጋፍጠው ይተዋችኋል፡፡ ስለሆነም እነሱ እንዳይከዳችሁ አብራችሁ ለመጋደል መተማመኛ የሚሆኗችሁ ከተከበሩ ሰዎቻቸው ማስያዣ የሚሆኑ ሰዎች እስክትይዙ ድረስ አነዚህ ህዝቦች ጋር ሆናችሁ እንዳትጋደሉ አላቸው:: እነሱም በጣም የሚገርም ሀሳብ አመላከትከን አሉት፡፡፡
ከዚያም ኑዓይም ቁረይሾች ጋር መጣ:: ለአቡሱፍያንና ከእሱ ጋር ለነበሩት የቁረይሽ ሰዎች እንዲህ አላቸው፡- “ለእናንተ ያለኝን ፍቅርና ሙሀመድ ጋርም የተቆራረጥኩ መሆኔን ታውቃላችሁ እኔ የሆነ መረጃ ደርሶኛል፡፡ ይህም ለእናንተ እንዲሆናችሁ ለእናንተ ማሳወቅ በእኔ ላይ ግዴታ ሆኖ አግኝቻቸዋለሁ:: በሚስጥር ያዙልኝ, አላቸው:: እነሱም እሺ እንደብቅልሃለን አሉት።ከዚያም እንዲህ አላቸው- አይሁዶች በሙሀመድ ላይ በሰሩት ነገር እንደ ተፀፀቱ ታውቃላችሁ። - እንዲህ ብለው ልከውለታል፡- «እኛ በሰራነው ስራ ተፀፅተናል፡፡ ከፈለግክ ከሁለቱ ጎሳዎች ከቁረይሾችና ከገጥፋኖች የተከበሩ ከሆኑ ወንዶቻቸው ይዘን እንሰጥህና አንገታቸውን ትቀላቸዋለህ፡፡ ቀሪዎቹን ደግሞ እስኪበታተኑ ድረስ ከአንተ ጋር ሆነን እንታገላቸዋለን›› ብለውታል፡፡ እሱም እሽ ብሎ ልኮላቸዋል፡፡ ስለሆነም አይሁዶች ከእናንተ ከወንዶቻችሁ ማስያዣፈልገው ከላኩ አንድም ሰው እንዳትሰጧቸው አላቸው፡፡
ከዚያም ገጥፋኖች ጋር መጣና እናንተ የገጥፋን ስብስቦች ሆይ! እናንተ ዘሮቼ ዘመዶቼ ከሰዎች ሁሉ የምወዳችሁ ናችሁ። እኔን ትጠረጠጥሩኛላችሁ ብዬ አላስብም አላቸው:: እውነት ብለሃል አንተ የምትጠረጠር አይደለህም አሉት። እሱም ሚስጥሬን ደብቁልኝ ብሎ ለቁረይሾች የነገራቸውን አይነት ለእነሱም ነገራቸው፡፡ ያስጠነቀቃቸውን ለእነሱም አስጠነቀቃቸዉ
ከዚያም በ5ኛው ዓመተ ሃጅራ በዛው ወር ቅዳሜ ሌሊት ቁረይሾችና ገጥፋኖች ወደ በኒቁረይዟዎች እንዲህ ብለው ላኩባቸው፡- እኛ ያለነው በሰው ሀገር ነው፤ ግመሎቻችንና ፈረሶቻችን እየጠፉብን ነው ሙሀመድን ተፋልመነው እንድንገላገል ነገ በጧት ተነሱ፡፡››
በኒ ቁረይዟዎችም እንዲህ ብለው ላኩባቸው ቀኑ ቅዳሜ ነው:: በእዚህ ቀን ምንም የማንሰራበት ቀን ነው:: ከአሁን በፊት ከእኛ የሆኑ ሰዎች ቅዳሜ ቀን ስርተው ምን መከራ እንደመጣባቸው ከእናንተ የተደበቀ አይደለም:: ከዚህ በተጨማሪ መተማመኛ ይሆኑን ዘንድ ከእናንተ ማስያዣ እስክትሰጡን ድረስ ወደ ጦርነቱ አንገባም ምክንያቱም ፍልሚያው ሲበረታባችሁ ወደ ሀገራችሁ ሸሽታችሁ እኛ ብቻችንን ልንፋለመው ለማንችለው ለሆነው ሙሀመድ አጋፍጣችሁን እንዳትሄዱ እንፈራለን ብለው ላኩባቸው:: መልዕክተኞቹም በኑቁረይዟዎች ያሉትን ይዘው ሲመለሱ ቁረይሾችና ገጥፋኖችም በፈጣሪ እንምላለን ኑዓይም የነገራችሁ ነገር ትክክል ነው >> አሉና ወደ በኒ ቁረይዟዎች፡- እኛ አንድም ወንድ አንልክላችሁም ከፈለጋችሁ ውጡና ተጋደሉ›› ብለው ላኩባቸው::
.... በኒ ቁረይዟዎችም መልዕክቱ ሲደርሳቸው «ኑዓይም የነገረን እውነት ነው.. አሉ:: ወደ ቁረይሾችና ገጥፋኖች ማስያዣ እስክትሰጡን ድረስ እኛ ከእናንተ ጋር ሆነን ሙሀመድን አንዋጋም ብለው ላኩባቸው፡፡ በእነሱ ላይም አመፁባቸው:: አላህ በመሀከላቸው አጣላቸው፤ አንድነታቸውን በታተነው:: ከዚያ አስፈሪ ከሆነው ጭንቀት ተገላገሉ:: ቁረይሾይችና ገጥፋኖች እርስበርሳቸው ተጣልተው ድል ሳይቀናቸው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ:: በዚህ ኑዓይም በተጠቀመው ብልሃት ሰበብ ረሱል ﷺባለድል ሆኑ።
ለዚህ ድል እንዲበቁ ያደረጋቸዉ ኑዓይም(ረ.ዐ)ነበር
ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6113