tgoop.com/Islam_and_Science/6088
Last Update:
1979 በሀረም ላይ ምን ተፈጠረ?
ክፍል 2
ሙሐመድ አልቃሕጣኒ እና ጁሀይማን አልዑተይቢ የሀረምን ማይኮሮፎን እያበሩ ውስጥ ላሉት የሐረም እንግዶች እና መስጂዱን ከበው ለተቀመጡት የፖሊስ አዛዦች የማስፈራሪያ እና መህዲን ተቀበሉ መልእክት ያስተላልፋሉ። በከባቢው ላይ የተሰማሩት ፖሊሶች ሀረምን መግባት እንችል እንደው ብለው ወደ በሩ ጠጋ ባሉ ቁጥር ሚናራዎች ላይ የተጠመዱት ስናይፐሮች ስራቸውን ይሰራሉ።
በቦታው ያሉት የፖሊስ ሀይላት ጉዳዩ በቀላል እንደማትፈታ ስለገባቸው የሀገሬው ሰራዊት ስራውን እንዲከውን ወደ መከላከያ ሚኒስትሩ ስልካቸውን አንቃጨሉና የሱዑዲያ ወታደሮች በተራቸው ሀረምን ከበው እገታውን ለመስበር ያላቸውን ሀይል ሁሉ አፈሰሱ። ሁኔታው ግን ምንም አልተለወጠም።
በመሆኑም አጋቾቹን ለማዳከም የሀረም ውሀ አገልግሎት እና የመብራት ስርጭት ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጥ ተደረገ። ግን የተጠበቀው ውጤት ተቀልብሶ ከአጋቾቹ ይልቅ የሐረም እንግዶች በጥማት እና ረሐብ በየቦታው መወዳደቅ ጀመሩ። ንጉስ ዃሊድ ቢጨንቀው ሽማግሌ አስልኮ ከበዛ ንትርክ በኋላ በመጅጂዱ ክልል ያሉ ህፃናት እና ሴቶች ያለምንም መታኮስ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ ተፈቀደላቸው። እርግጥ እነ ዑተይቢ ስንቅ እያለቃቸው ስለነበር ከዚህ የተለየ የመደራደሪያ መንገድ አልነበራቸውም።
ሀረም እንዲህ በእገታ በተሟሟቀችበት ወቅት አሜሪካ እና ኢራን የጉዳዩ ጠንሳሽ አንቺ ነሽ! አንቺ ነሽ! እየተባባሉ አጋጣሚውን ለፖለቲካ ጥቅማቸው መጓተቻ ለማድረግ በየሚዲያው ይንተፋተፋሉ።
እንዳይታኮሱበት ሀረም ፤ ዝም እንዳይሉም መንግስት ግልበጣ ሆኖባቸው የተወዛገቡት ባለስልጣናት ጉዳዩን ወደ ፈታዋ ምክር ቤት መርተው የሀረምን ክብር ለማስጠበቅ ሲባል ወታደራዊ እንቅስቃሴ በውስጡ ማድረግን የሚፈቅድ አዲስ ፈታዋ ተቀብለው በየጋዜጣው እና ሚዲያ ማሰራጨት ጀመሩ።
BY ISLAMIC SCHOOL

Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6088