tgoop.com/Islam_and_Science/6039
Last Update:
በስምምነቱ መሰረት ሸሪፍ ሁሴን በኸሊፋው ላይ አመፅ እንዲያነሳ የሚለው ሀሳብ ይገኝበታል፡፡ አሳዛኝ የሙስሊም መሪነት አስተሳሰብ ነበር፡፡ ሙስሊሞች በስልጣን ጥም ተሸንግለው በራሳቸው መሪ ላይ አመፅ ለማንሳት የቋመጡበት የታሪከ አብነት፡፡
በሚስጢር የተደረገው ስምምነት ዶሴ ሙሉ በሙሉ ግልፅ ባልሆኑ ሀሳቦች የተሞሉ ነበሩ፡፡ ሸሪፍ ሁሴን ይህን ጉዳይ ሳያዉቀው እንዳልቀረ ብዙ ምሁራን ያምናሉ፡፡ የሸሪፉ ፍላጎት ስምምነቱ የሚሰጠውን ዉጤት ብቻ መጠበቅ አልነበረም፡፡ ዋና ግቡ ከእንግሊዛዊያኑ በቂ የጦርና ሎጂስቲክስ እርዳታ ማግኘት ነበር፡፡ ዉላቸው ላይፀና ቢችል የራሱን መንገድ እንደሚከተል ያስተዋለ ይመስላል ይላሉ ምሁራኑ፡፡ እንግሊዛዊያኑ ያሉትን ተቀብሎ ለፈረመላቸው ሸሪፍ ታዲያ መሳሪያዎችን ከመስጠት ጀምሮ በቂ የጦር ስልጠና ጭምር በመስጠት አልደከሙም፡፡ የኦቶማንን መንግስት ለመጣል ወሳኝ እድል ያገኙት በሙስሊም ዓረቦች በኩል መሆኑን አስረግጠው ይረዳሉና፡፡ እነሱም ለትግል አጋርነት ካልሆነ ለዓረቦች የገቡትን ቃል እንደማይቀጠሉበት ይገባቸዋል፡፡ እንግሊዝ ከዓረቢያ አንድ ጥግ (የፐርሺያ ሰላጤ አባዳን መንደር) የፈለቀውን ነዳጅ መቆጣጠር ችላለች፡፡
በዚያ ላይ በቀጠናው በተከታታይ ነዳጅ እንደሚፈልቅ እየተነገረ መሆኑን ዊንስተን ቸርችል አስተዉሏል፡፡ ከሁሉም የአዉሮፓ መሪዎች ቀድሞ ይህን በማስተዋሉ አካባቢውን በበላይነት መቆጣጠር የእንግሊዝ ብቻ እድል እንዲሆን ጥልቅ ዓላማ ይዟል፡፡ ስለዚህ ሁሉም በየስሜቱ የያዘውን ይዞ ሱልጣኑን መጣል ስለሚቀድም ብቻ ተግባብተው አለፉ፡፡
#ክፍል ➋
ይቀጥላል......
ለአስተያየት🔽
T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
join👇👇👇
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
BY ISLAMIC SCHOOL
Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/6039