Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/Islam_and_Science/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tgoop/post.php on line 50
ISLAMIC SCHOOL@Islam_and_Science P.5921
ISLAM_AND_SCIENCE Telegram 5921
አሁንስ አትገረሚም???
ዩምና ሙሀመድ

ምን ያስገርመኛል መሰለሽ ሁሌ የረህማኑን አዛኝነት እኔ የእሱ ባሪያው እንድሆን የመሻቱ ስፋት በእኔ  መታወስ የፍላጎቱን ጥግ አስተውለሽው ይሁን?
እኔ ባላስታውሰው እኮ ሚጎድልበት ነገር የለም እሱ እኮ ስንት እሚዋደቁለት ባሪያዎች አሉት እሱ እኮ ምድር ላይ ያለች ትንሿ ጠጠር ሳትቀር የፈጠረ ጌታ እኔን ማስታወሱ አይገርምሽም?

^ ቢተወኝስ ቆይ ሲጀመር ባይፈጥረኝስ ስንት እህት እና ወንድሞቼን እናቴ ሆድ ውስጥ ባክነው እኔ መፈጠሬ ስለወደደኝም አይደለምን?
ታዲያ አይደለም የወደደኝ ጌታ የወደደኝ ሰው እኔ ላይ መብት የለውም እንዴ?
ምሳሌ ላንሳልሽ ምድር ላይ በጣም በጣም ከሚሳሱልኝ ሰዎች ውስጥ ከእናቴ ወይ ከአባቴ በላይ ፍጥረት የለም እኮ አይደል!! 
እስኪ ልጅኘታችንን ዞረሽ እይው ልጅ ናቸው በሚል ሀላፊነት የሚባል አልነበረብንም ሀላፊነት መውሰድን በትንሽ በትንሹ እንድንማር አደረጉን
አላሄዋም እስከ 15 አመት ወይም እራሳችንን እስክናውቅ ነፃነት ሰጠን ምንም ቅጣት እንደሌለብን አሳወቀን ለቤተሰቦቻችን ግን የኛን የመኮትኮት ሀላፊነት ሰጣቸው  አትገረሚም!!


.....ቡሗላ እንዳንደክም ግራ እንዳንጋባ እኮ ነው ከዛማ ልክ ስናድግ ቤተሰቦቻችን ለማስደሰት ውለታቸውን ለመመለስ እያልን ሀላፊነት እንዳለብን ሁላ ከእልጅነት እስከእውቀት  የለፉብንን  ለመመለስ ስንል እኛ ላይ መብት አላቸው እያልን እነሱን ለማስደሰት መብታቸውን ለመጠበቅ ደፋ ቀና እንላለን ታዲያ ያኡኽታ ይሄንን ሁላ ነገር አንቺ ካለነበርሽበት አስገኝቶ ጭራሽ እማያውቁሽ እማታውቂያቸውን ፍጡሮች እናት እና አባት ያውም ከእዝነት ጋር የለገሰሽ ጌታ አንቺ ላይ መብት የለውምን?

>>>>> ብርጭቆ ስትሰብሪ ሁላ እኮ እናትሽ ወይ ትቆጣሻለች ወይ ትመታሻለች እና ስለምን ሲባል የፈጠረሽ ጌታ በነገሮች ሲቆነጥጥሽ ቢጠላኝ ነው አስባለሽ?ምን ባደርገው ነው እያልሽ ከእሱ ጋር ግብግብ አስፈጠረሽ?

^^ደሞ እኮ በተከበረው ቃሉ ሲፈትንሽ እያላቀሽ  ስለመሆኑ አማኝ ስለመሆንሽ እንዲህ እያለ ነግሮሻል "አሊፍ ላም ሚም አሀሲበናሱ አዩትረኩ አመና ፈሁም ላዩፍተኑን"
^የሰው ልጆች አምነናል ካሉ ቡሗላ እንፈተናለን ብለው አላሰቡንም አልገመቱምን^ ይለናል አየሽልኝ ኡኽታ በእሱ ስለማመኔ ማመልከቻው ወይ ደሞ መለያው በሚያመጣልኝ ነገር መታገሴ ነው::
* ለትምህርት ፈተና ስል ስንቴ አነባለው ለሊት አዳር እያነጋሁኝ  እየተጨነኩኝ ካለፋሁኝ እንደምወድቅ አውቃለዋ ከወደኩኝ ደሞ ያኔ ለቤተሰቦቼ ተገቢውን ምላሽ አልሰጠሁም ማለት ነው የት ት ፈተናውን ማለፌ
ከእኔ በላይ ቤተሰቦቼ ያስደስታቸዋል አላሄዋም ሲሞክረኝ ወደእሱ እንድቀርብ አጥብቆ ይሻብኛል::

>>>>>አስተውዪማ የሆነ መስሪያ ቤት እራስሽን አስቀጥረሽ ሳዩው ከዛማ አሰሪሽ አንቺን ይወድሻል ሊያጣሽ አይፈልግም እንድትቀርቢው ይፈልጋል ምን እሚያደርግሽ ይመስልሻል?
በጣም ከምትፈልጊው እሱ ጋር ካለ ነገር ይቀንስብሻል ወይም ያስቀርብሻል ለምሳሌ ደሞዝሽን ግማሹን ወይም እሩቡን እሱ ጋር አስቀርቶ ቀሪውን ቢሰጥሽ እመኚኝ ቀሪውን ደሞዝሽ ፍለጋ አሰሪሽ ቢሮ ትመላለሻለሽ አሰሪሽም እሱ እሚፈልጋትን ሴት እስክትሆኚለት በመመላለስሽ እርካታን አግኝቶ ይቀመጣል::
____አላሄዋም ከአሰሪሽ በላይ ላንቺ እሚያስፈልግሽን ነገር ሲነጥቅሽ መርጦሽ ነው ወደእሱ እራስሽን እንድታዞሪ እየጠየቀሽ ነው ግን እኛ መመረጥን እምናውቀው ሁላ አይመስለኝም::
*ደሞ እኮ አያቆምም በቃ ተስፋ ቆርጫለው የፈጠረኝንም አስከፍቻለው ብለን ስናስብ እንዲህም አይደል የሚለን
"ቁል ያኢባዲየለዚነ አስረፋ አላ አንፉሲሂም ላተቅነጡ ሚን ራህመቲላህ ኢነላሀ ገፉሩን ረሂም"
(እናንተ በነፍሶቻቹ ላይ ድንበር ያለፋቹ ባሪያዎቼ ሆይ በአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ አላህኮ አዛኝና ማሀሪ ነው)
  ይለናል እሺ አሁንስ አትገረሚም?



አምፀነውም ወዶን በሞከረን ነገር ላይም እንዴት ብለን የእሱን መብት ለእራሳችን ሰጥተንበትም አሁንም ኑኑኑኑ ቅረቡኝ እያለን እኮ ነው::  ከእዝነቱ እንዳንሸሽ ይነግረናል ምን ያክል ለእኛ ቅርብ እንደሆነ ያሳውቀናል የእሱ እዝነት ትልቅ ስለመሆኑ ከእዝነቱ ያሻንን እንደምንወስድ እየወስድንም እንደሆነ
"ወኢን ተኡዱ ኒእመላሂ ፈላቱአዱሀ"
(የአላህን ፀጋ ብትቆጥሩት አትዘልቁትም)እያለ ያበስረናል በሰፊው እዝነቱ እንደምንኖር ስለምን በእዝነቱ እና በፀጋው ተከበን ተስፋን እንቆርጣለን አንቺዬ?
^መለስ አድርጎ ደሞ ፈተናዎቹ ብቻቸውን እንዳልመጡ ነገራቶች ሁላ መሞከሪያዎች ከእዛም ብርሀናዊ ፀጋዎች ስለመሆናተው እንዲህ ይለናል አይደል "ፈኢነማአል ኡስሪ ዩስራ" (በእርግጥም ከችግር ቡሓላ ምቾት አለ)
ብሎ ከፀጋዎቹ ውስጥ የሆነኛውን ይገልፅልናል እናም ኡኽታ ጨንቆሻል ከፍቶሻል ወይ የሆነ ይሳካልኛል ያልሽው ነገር አለመሳካቱ አዘንብሎብሻል ተሳሰቢውማ ተነሺና ውዱእ አድርገሽ መስገጃሽ ላይ ተደፍተሽ ማድረግ እየፈለግሽ ይቺን ትልቋን ነፍሲያሽን አሸንፈሽ ለአላሄዋ ብለሽ በተወሽው ነገር ተሳሰቢው ያኔ ግን ለእሱ ብለሽ የተወሽው ነገር ካጣሽ ቀድመሽ ነፍስሽን ተሳሰቢያት



tgoop.com/Islam_and_Science/5921
Create:
Last Update:

አሁንስ አትገረሚም???
ዩምና ሙሀመድ

ምን ያስገርመኛል መሰለሽ ሁሌ የረህማኑን አዛኝነት እኔ የእሱ ባሪያው እንድሆን የመሻቱ ስፋት በእኔ  መታወስ የፍላጎቱን ጥግ አስተውለሽው ይሁን?
እኔ ባላስታውሰው እኮ ሚጎድልበት ነገር የለም እሱ እኮ ስንት እሚዋደቁለት ባሪያዎች አሉት እሱ እኮ ምድር ላይ ያለች ትንሿ ጠጠር ሳትቀር የፈጠረ ጌታ እኔን ማስታወሱ አይገርምሽም?

^ ቢተወኝስ ቆይ ሲጀመር ባይፈጥረኝስ ስንት እህት እና ወንድሞቼን እናቴ ሆድ ውስጥ ባክነው እኔ መፈጠሬ ስለወደደኝም አይደለምን?
ታዲያ አይደለም የወደደኝ ጌታ የወደደኝ ሰው እኔ ላይ መብት የለውም እንዴ?
ምሳሌ ላንሳልሽ ምድር ላይ በጣም በጣም ከሚሳሱልኝ ሰዎች ውስጥ ከእናቴ ወይ ከአባቴ በላይ ፍጥረት የለም እኮ አይደል!! 
እስኪ ልጅኘታችንን ዞረሽ እይው ልጅ ናቸው በሚል ሀላፊነት የሚባል አልነበረብንም ሀላፊነት መውሰድን በትንሽ በትንሹ እንድንማር አደረጉን
አላሄዋም እስከ 15 አመት ወይም እራሳችንን እስክናውቅ ነፃነት ሰጠን ምንም ቅጣት እንደሌለብን አሳወቀን ለቤተሰቦቻችን ግን የኛን የመኮትኮት ሀላፊነት ሰጣቸው  አትገረሚም!!


.....ቡሗላ እንዳንደክም ግራ እንዳንጋባ እኮ ነው ከዛማ ልክ ስናድግ ቤተሰቦቻችን ለማስደሰት ውለታቸውን ለመመለስ እያልን ሀላፊነት እንዳለብን ሁላ ከእልጅነት እስከእውቀት  የለፉብንን  ለመመለስ ስንል እኛ ላይ መብት አላቸው እያልን እነሱን ለማስደሰት መብታቸውን ለመጠበቅ ደፋ ቀና እንላለን ታዲያ ያኡኽታ ይሄንን ሁላ ነገር አንቺ ካለነበርሽበት አስገኝቶ ጭራሽ እማያውቁሽ እማታውቂያቸውን ፍጡሮች እናት እና አባት ያውም ከእዝነት ጋር የለገሰሽ ጌታ አንቺ ላይ መብት የለውምን?

>>>>> ብርጭቆ ስትሰብሪ ሁላ እኮ እናትሽ ወይ ትቆጣሻለች ወይ ትመታሻለች እና ስለምን ሲባል የፈጠረሽ ጌታ በነገሮች ሲቆነጥጥሽ ቢጠላኝ ነው አስባለሽ?ምን ባደርገው ነው እያልሽ ከእሱ ጋር ግብግብ አስፈጠረሽ?

^^ደሞ እኮ በተከበረው ቃሉ ሲፈትንሽ እያላቀሽ  ስለመሆኑ አማኝ ስለመሆንሽ እንዲህ እያለ ነግሮሻል "አሊፍ ላም ሚም አሀሲበናሱ አዩትረኩ አመና ፈሁም ላዩፍተኑን"
^የሰው ልጆች አምነናል ካሉ ቡሗላ እንፈተናለን ብለው አላሰቡንም አልገመቱምን^ ይለናል አየሽልኝ ኡኽታ በእሱ ስለማመኔ ማመልከቻው ወይ ደሞ መለያው በሚያመጣልኝ ነገር መታገሴ ነው::
* ለትምህርት ፈተና ስል ስንቴ አነባለው ለሊት አዳር እያነጋሁኝ  እየተጨነኩኝ ካለፋሁኝ እንደምወድቅ አውቃለዋ ከወደኩኝ ደሞ ያኔ ለቤተሰቦቼ ተገቢውን ምላሽ አልሰጠሁም ማለት ነው የት ት ፈተናውን ማለፌ
ከእኔ በላይ ቤተሰቦቼ ያስደስታቸዋል አላሄዋም ሲሞክረኝ ወደእሱ እንድቀርብ አጥብቆ ይሻብኛል::

>>>>>አስተውዪማ የሆነ መስሪያ ቤት እራስሽን አስቀጥረሽ ሳዩው ከዛማ አሰሪሽ አንቺን ይወድሻል ሊያጣሽ አይፈልግም እንድትቀርቢው ይፈልጋል ምን እሚያደርግሽ ይመስልሻል?
በጣም ከምትፈልጊው እሱ ጋር ካለ ነገር ይቀንስብሻል ወይም ያስቀርብሻል ለምሳሌ ደሞዝሽን ግማሹን ወይም እሩቡን እሱ ጋር አስቀርቶ ቀሪውን ቢሰጥሽ እመኚኝ ቀሪውን ደሞዝሽ ፍለጋ አሰሪሽ ቢሮ ትመላለሻለሽ አሰሪሽም እሱ እሚፈልጋትን ሴት እስክትሆኚለት በመመላለስሽ እርካታን አግኝቶ ይቀመጣል::
____አላሄዋም ከአሰሪሽ በላይ ላንቺ እሚያስፈልግሽን ነገር ሲነጥቅሽ መርጦሽ ነው ወደእሱ እራስሽን እንድታዞሪ እየጠየቀሽ ነው ግን እኛ መመረጥን እምናውቀው ሁላ አይመስለኝም::
*ደሞ እኮ አያቆምም በቃ ተስፋ ቆርጫለው የፈጠረኝንም አስከፍቻለው ብለን ስናስብ እንዲህም አይደል የሚለን
"ቁል ያኢባዲየለዚነ አስረፋ አላ አንፉሲሂም ላተቅነጡ ሚን ራህመቲላህ ኢነላሀ ገፉሩን ረሂም"
(እናንተ በነፍሶቻቹ ላይ ድንበር ያለፋቹ ባሪያዎቼ ሆይ በአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ አላህኮ አዛኝና ማሀሪ ነው)
  ይለናል እሺ አሁንስ አትገረሚም?



አምፀነውም ወዶን በሞከረን ነገር ላይም እንዴት ብለን የእሱን መብት ለእራሳችን ሰጥተንበትም አሁንም ኑኑኑኑ ቅረቡኝ እያለን እኮ ነው::  ከእዝነቱ እንዳንሸሽ ይነግረናል ምን ያክል ለእኛ ቅርብ እንደሆነ ያሳውቀናል የእሱ እዝነት ትልቅ ስለመሆኑ ከእዝነቱ ያሻንን እንደምንወስድ እየወስድንም እንደሆነ
"ወኢን ተኡዱ ኒእመላሂ ፈላቱአዱሀ"
(የአላህን ፀጋ ብትቆጥሩት አትዘልቁትም)እያለ ያበስረናል በሰፊው እዝነቱ እንደምንኖር ስለምን በእዝነቱ እና በፀጋው ተከበን ተስፋን እንቆርጣለን አንቺዬ?
^መለስ አድርጎ ደሞ ፈተናዎቹ ብቻቸውን እንዳልመጡ ነገራቶች ሁላ መሞከሪያዎች ከእዛም ብርሀናዊ ፀጋዎች ስለመሆናተው እንዲህ ይለናል አይደል "ፈኢነማአል ኡስሪ ዩስራ" (በእርግጥም ከችግር ቡሓላ ምቾት አለ)
ብሎ ከፀጋዎቹ ውስጥ የሆነኛውን ይገልፅልናል እናም ኡኽታ ጨንቆሻል ከፍቶሻል ወይ የሆነ ይሳካልኛል ያልሽው ነገር አለመሳካቱ አዘንብሎብሻል ተሳሰቢውማ ተነሺና ውዱእ አድርገሽ መስገጃሽ ላይ ተደፍተሽ ማድረግ እየፈለግሽ ይቺን ትልቋን ነፍሲያሽን አሸንፈሽ ለአላሄዋ ብለሽ በተወሽው ነገር ተሳሰቢው ያኔ ግን ለእሱ ብለሽ የተወሽው ነገር ካጣሽ ቀድመሽ ነፍስሽን ተሳሰቢያት

BY ISLAMIC SCHOOL


Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/5921

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Over 33,000 people sent out over 1,000 doxxing messages in the group. Although the administrators tried to delete all of the messages, the posting speed was far too much for them to keep up. Hui said the messages, which included urging the disruption of airport operations, were attempts to incite followers to make use of poisonous, corrosive or flammable substances to vandalize police vehicles, and also called on others to make weapons to harm police. Hui said the time period and nature of some offences “overlapped” and thus their prison terms could be served concurrently. The judge ordered Ng to be jailed for a total of six years and six months. How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) Select: Settings – Manage Channel – Administrators – Add administrator. From your list of subscribers, select the correct user. A new window will appear on the screen. Check the rights you’re willing to give to your administrator.
from us


Telegram ISLAMIC SCHOOL
FROM American