Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/Islam_and_Science/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tgoop/post.php on line 50
ISLAMIC SCHOOL@Islam_and_Science P.5743
ISLAM_AND_SCIENCE Telegram 5743
📖 #የመራም_ማስታወሻ
           ክፍል ~ ➏
ፀሀፊ ☞አሚር ሰይድ



አባቴ ሱሱ ከአቅሙ በላይ ሆነበት የሚከፈለዉ ደመወዝ አልበቃዉ ሲል ማመን የሚከብድ ይሆናል ብለን አስበነዉ የማናቀዉ በአባቴ ሱስ ምክንያት ተከሰተ.......
ማለቁን በጉጉት ስንጠብቅ የነበረው የቤት ግንባታ አባቢ ከእማ ደብቆ ሽጦታል፡፡ እማ ይሄን ስትሰማ ምንም ማረግ አልቻለችም ሆዷ የብስ ቁስል ብሎ አምርራ አለቀሰች! ልቧ ደጋግሞ ቆሰለ፡፡ ከአባቢ ጋር ለመለያየት ወሰነች ግን ምን ይደረግ እናቴ ነፍሰ ጡር ነች.... እርዚቅ በአላህ እጅ ነዉ ብላ የምታምን ሴት የወሊድ መቆጣጠሪያ መዉሰድ የለባትም እናንተም አድጋችሁ ጎጆ ስቀልሱ የወሊድ መቆጣጠሪያ እንዳትወስዱ ልጅን አላህ ይሰጣል እሱዉ በእርዚቁ ያሳደገዋል ትለን ነበር... ኡሚ በሆዷ ያለው ፅንስ ከመወለዱ በፊት መለያየት አትችልም፡፡ አባቢ ቤት አልፎ አልፎ ይመጣል ለኛ ግን አለመምጣቱ ሰላም ይሰጠናል፡፡

ኡሚ እርግዝናው በጣሙን ከብዷታል እንደበፊቱ የሚንከባከባት ሰው ዛሬ ከጎኗ የለም፡፡ ጎረቤቶቻችን ግን ያዝኑላታል፡፡ በየአቅማቸው ያገኙትን ያማራትን እየሰሩ ያመጡላታል፡፡ በተለይ ደግሞ እማማየ " አይዞሽ ትንሽ ቀን ነው ልጆችሽ ይደርሱልሻል ጠንክሪ" እያሉ ያፅናኗታል፡፡

ቀን ቀንን እየተካ የጊዜ መቁጠሪያ ሰለዳ ከወር ወር እየተሽጋገረ ይሄው እኔም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ለመሆን በቃሁ፡፡ የፈይሲ ምትክ መፅናኛ ይሆነን ዘንድ ዳግም አዩብ ተወለደ፡፡ ሚስኪን አዩብ ፍቅር ጓዙን ጠቅልሎ ከመጣ በኃላ ዳግም ፍቅርን ሊመልስልን ይሆን የመጣው!? ብየ ራሴን ጠየኩ፡፡ አባቢ አዩብን ሲያይ ፊቱ በደስታ አበራ ግን ምን ዋጋ አለው፡፡ የተጠናወተው ሱስ አቋሙን አሽመድምዶ አልፈስፍሶታል! ሀላፊነትን መሸከም አይችልም፡፡ አባቢ ጥሩ ሞዴል መሆን ስላልቻለ ይሄን የተበላሸ ማንነት እያየ ማደጉ ለአዩብ ጥሩ ስላልሆነ ኡሚ ከአባቢ አርቃ ብቻዋን ማሳደግ ጀመረች፡፡ አባቢም አልተቃወመም " ከኔ የሚማመው ጥሩ ነገር የለም ልጄን አንች አሳድጊው" ብሎ ፈቀደላት፡፡

እማ ብቻዋን ሶስት ልጆችን ማሳደግ ፍርጃ ሆነባት፡፡ እንደበፊቱ ስራ ለመቀጠር ጊዜው አልፏል አሁን ድፕሎማ በድግሪ ተተክቷል፡፡ ለዚህ ደግሞ የእናቴ የሂወት ቀማኛ ሌባ እኔ ነኝ! ምክንያቱም እኔ በመወለዴ ምክንያት ነው ኡሚ ስራ ያቆመችው፡፡ ከስራ ሁሉ በላጭ እኔን አድርጋ መረጠችን! ታዳ ያኔ በፍቅር አታልየ የሰረኩዋትን ሂወት ዛሬ እንዴት ልመልስላት!?

እማ ለኛ ስትል እኛን ለማኖር ብላ የቀን ስራ መስራት ጀመረች እንጀራ መጋገር ልብስ ማጠብ ቤት ማፅዳት የእማ ቆሚ ስራዋ ሆነ፡፡
በትምህርት እንዳንሰንፍ ትመክረናለች፡፡ " እናተ ጠንክራችሁ ተማሩና ስራ ስትይዙ ከዚህ ሂወት ገላግላችሁ ታሳርፉኛላችሁ!" ትለናለች፡፡ እኔም ሆንኩ ሪም በትምህርታችን አንታማም፡፡ ለማሚ ስል እሷን ከዚህ ሂወት ለመገላገል ስል ከወትሮው በበለጠ መልኩ ጠነከርኩ፡፡


ከትምህርት ሰአት ውጭ ቆሎ፣ ስካር ድንችና የተቀቀለ እንቁላል ከ11 ሰአት በኅላ መንገድ ዳር እየሸጥኩ ኡሚን ማገዝ ጀመርኩ፡፡ ሪም አዩብን መንከባከብና መጠበቅ ስራዋ ነው፡፡ ቅዳሜና እሁድ ደግሞ የቤት ፅዳቱን እኔ እሰራለሁ፡፡ ኡሚ የምትሰራላቸው ሰወች በፊት የነበራትን ሂወት ስለሚያውቁ ያዝኑላታል፡፡ በተለይ ደግሞ ወይዘሮ ጥሩወርቅ በጣም ያዝኑልናል ከደመወዟ በላይ ጨምራ ነው የምትሰጣት ከዛ በተጨማሪ ደግሞ ሽሮ፣በርበሬ፣ የጤፍ ዱቄት እንጀራ በጋገረች ቁጥር እንጀራም ይሰጡናል፡፡ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ስራ ባይኖራቸውም ልጆቻቸው አንቀባረው ያኖሯቸዋል፡፡ ከባለቤታቸው ከአቶ አለማየሁ ጋር በተንጣለለ ጊቢ ውስጥ ከአምስት ተከራይ ጋር ይኖራሉ፡፡

እኔም እሁድ ቀን የወ/ሮ ጥሩወርቅን ቤት ለማፅዳት በጧት ሄድኩኝ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ልጃቸው ጋር ጀርመን ሂደዋል፡፡ አቶ አለማየሁ ደግሞ ሁሌም እሁድ እሁድ ቤተክርስቲያን የመሄድ ልምድ ስላላቸው በጧት የነሱን ጨርሸ ወደ ሌላ ለመሄድ አስቤ ነበር፡፡

ቤቱንም ጊቢውንም አፅድቸ እንደጨረስኩ ለመሄድ የጊቢውን በር ስከፍት አቶ አለማየሁ ጋር ፊት ለፊት ተገጣጠምን......
የሰዉ ልጅ ኑሮ አንዱን ሲይዙት ሌላዉ ይጎላል .. ጎዶሎዉን ለመሙላት ሲባል ደግሞ ባልጠበቁትና ባልገመቱት ሰአት ከሌላ አዲስ ችግር ጋር ያላትማል፡፡
አይ የኔ መከራ አለማለቁ....

አቶ አለማየሁ ምን አስበዉ ይሆን ???

#ክፍል ➐
ይቀጥላል



join👇👇

www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group



tgoop.com/Islam_and_Science/5743
Create:
Last Update:

📖 #የመራም_ማስታወሻ
           ክፍል ~ ➏
ፀሀፊ ☞አሚር ሰይድ



አባቴ ሱሱ ከአቅሙ በላይ ሆነበት የሚከፈለዉ ደመወዝ አልበቃዉ ሲል ማመን የሚከብድ ይሆናል ብለን አስበነዉ የማናቀዉ በአባቴ ሱስ ምክንያት ተከሰተ.......
ማለቁን በጉጉት ስንጠብቅ የነበረው የቤት ግንባታ አባቢ ከእማ ደብቆ ሽጦታል፡፡ እማ ይሄን ስትሰማ ምንም ማረግ አልቻለችም ሆዷ የብስ ቁስል ብሎ አምርራ አለቀሰች! ልቧ ደጋግሞ ቆሰለ፡፡ ከአባቢ ጋር ለመለያየት ወሰነች ግን ምን ይደረግ እናቴ ነፍሰ ጡር ነች.... እርዚቅ በአላህ እጅ ነዉ ብላ የምታምን ሴት የወሊድ መቆጣጠሪያ መዉሰድ የለባትም እናንተም አድጋችሁ ጎጆ ስቀልሱ የወሊድ መቆጣጠሪያ እንዳትወስዱ ልጅን አላህ ይሰጣል እሱዉ በእርዚቁ ያሳደገዋል ትለን ነበር... ኡሚ በሆዷ ያለው ፅንስ ከመወለዱ በፊት መለያየት አትችልም፡፡ አባቢ ቤት አልፎ አልፎ ይመጣል ለኛ ግን አለመምጣቱ ሰላም ይሰጠናል፡፡

ኡሚ እርግዝናው በጣሙን ከብዷታል እንደበፊቱ የሚንከባከባት ሰው ዛሬ ከጎኗ የለም፡፡ ጎረቤቶቻችን ግን ያዝኑላታል፡፡ በየአቅማቸው ያገኙትን ያማራትን እየሰሩ ያመጡላታል፡፡ በተለይ ደግሞ እማማየ " አይዞሽ ትንሽ ቀን ነው ልጆችሽ ይደርሱልሻል ጠንክሪ" እያሉ ያፅናኗታል፡፡

ቀን ቀንን እየተካ የጊዜ መቁጠሪያ ሰለዳ ከወር ወር እየተሽጋገረ ይሄው እኔም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ለመሆን በቃሁ፡፡ የፈይሲ ምትክ መፅናኛ ይሆነን ዘንድ ዳግም አዩብ ተወለደ፡፡ ሚስኪን አዩብ ፍቅር ጓዙን ጠቅልሎ ከመጣ በኃላ ዳግም ፍቅርን ሊመልስልን ይሆን የመጣው!? ብየ ራሴን ጠየኩ፡፡ አባቢ አዩብን ሲያይ ፊቱ በደስታ አበራ ግን ምን ዋጋ አለው፡፡ የተጠናወተው ሱስ አቋሙን አሽመድምዶ አልፈስፍሶታል! ሀላፊነትን መሸከም አይችልም፡፡ አባቢ ጥሩ ሞዴል መሆን ስላልቻለ ይሄን የተበላሸ ማንነት እያየ ማደጉ ለአዩብ ጥሩ ስላልሆነ ኡሚ ከአባቢ አርቃ ብቻዋን ማሳደግ ጀመረች፡፡ አባቢም አልተቃወመም " ከኔ የሚማመው ጥሩ ነገር የለም ልጄን አንች አሳድጊው" ብሎ ፈቀደላት፡፡

እማ ብቻዋን ሶስት ልጆችን ማሳደግ ፍርጃ ሆነባት፡፡ እንደበፊቱ ስራ ለመቀጠር ጊዜው አልፏል አሁን ድፕሎማ በድግሪ ተተክቷል፡፡ ለዚህ ደግሞ የእናቴ የሂወት ቀማኛ ሌባ እኔ ነኝ! ምክንያቱም እኔ በመወለዴ ምክንያት ነው ኡሚ ስራ ያቆመችው፡፡ ከስራ ሁሉ በላጭ እኔን አድርጋ መረጠችን! ታዳ ያኔ በፍቅር አታልየ የሰረኩዋትን ሂወት ዛሬ እንዴት ልመልስላት!?

እማ ለኛ ስትል እኛን ለማኖር ብላ የቀን ስራ መስራት ጀመረች እንጀራ መጋገር ልብስ ማጠብ ቤት ማፅዳት የእማ ቆሚ ስራዋ ሆነ፡፡
በትምህርት እንዳንሰንፍ ትመክረናለች፡፡ " እናተ ጠንክራችሁ ተማሩና ስራ ስትይዙ ከዚህ ሂወት ገላግላችሁ ታሳርፉኛላችሁ!" ትለናለች፡፡ እኔም ሆንኩ ሪም በትምህርታችን አንታማም፡፡ ለማሚ ስል እሷን ከዚህ ሂወት ለመገላገል ስል ከወትሮው በበለጠ መልኩ ጠነከርኩ፡፡


ከትምህርት ሰአት ውጭ ቆሎ፣ ስካር ድንችና የተቀቀለ እንቁላል ከ11 ሰአት በኅላ መንገድ ዳር እየሸጥኩ ኡሚን ማገዝ ጀመርኩ፡፡ ሪም አዩብን መንከባከብና መጠበቅ ስራዋ ነው፡፡ ቅዳሜና እሁድ ደግሞ የቤት ፅዳቱን እኔ እሰራለሁ፡፡ ኡሚ የምትሰራላቸው ሰወች በፊት የነበራትን ሂወት ስለሚያውቁ ያዝኑላታል፡፡ በተለይ ደግሞ ወይዘሮ ጥሩወርቅ በጣም ያዝኑልናል ከደመወዟ በላይ ጨምራ ነው የምትሰጣት ከዛ በተጨማሪ ደግሞ ሽሮ፣በርበሬ፣ የጤፍ ዱቄት እንጀራ በጋገረች ቁጥር እንጀራም ይሰጡናል፡፡ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ስራ ባይኖራቸውም ልጆቻቸው አንቀባረው ያኖሯቸዋል፡፡ ከባለቤታቸው ከአቶ አለማየሁ ጋር በተንጣለለ ጊቢ ውስጥ ከአምስት ተከራይ ጋር ይኖራሉ፡፡

እኔም እሁድ ቀን የወ/ሮ ጥሩወርቅን ቤት ለማፅዳት በጧት ሄድኩኝ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ልጃቸው ጋር ጀርመን ሂደዋል፡፡ አቶ አለማየሁ ደግሞ ሁሌም እሁድ እሁድ ቤተክርስቲያን የመሄድ ልምድ ስላላቸው በጧት የነሱን ጨርሸ ወደ ሌላ ለመሄድ አስቤ ነበር፡፡

ቤቱንም ጊቢውንም አፅድቸ እንደጨረስኩ ለመሄድ የጊቢውን በር ስከፍት አቶ አለማየሁ ጋር ፊት ለፊት ተገጣጠምን......
የሰዉ ልጅ ኑሮ አንዱን ሲይዙት ሌላዉ ይጎላል .. ጎዶሎዉን ለመሙላት ሲባል ደግሞ ባልጠበቁትና ባልገመቱት ሰአት ከሌላ አዲስ ችግር ጋር ያላትማል፡፡
አይ የኔ መከራ አለማለቁ....

አቶ አለማየሁ ምን አስበዉ ይሆን ???

#ክፍል ➐
ይቀጥላል



join👇👇

www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tgoop.com/IslamisUniverstiy_public_group

BY ISLAMIC SCHOOL


Share with your friend now:
tgoop.com/Islam_and_Science/5743

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Hashtags A Hong Kong protester with a petrol bomb. File photo: Dylan Hollingsworth/HKFP. 6How to manage your Telegram channel? As the broader market downturn continues, yelling online has become the crypto trader’s latest coping mechanism after the rise of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May and beginning of June, where holders made incoherent groaning sounds and role-played as urine-loving goblin creatures in late-night Twitter Spaces. best-secure-messaging-apps-shutterstock-1892950018.jpg
from us


Telegram ISLAMIC SCHOOL
FROM American