Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
የአጥፊዎችን ስም በግልፅ ማንሳት
(መረጃ ለሚያከብሩ ብቻ!)
~
ዛሬ ዛሬ የቢድዐ አራማጆች ወይም ተሻጋሪ ጥፋት የሚያደርሱ አካላት ላይ ስማቸውን ጠቅሶ ምላሽ መስጠትን እንደ አፍራሽ ተግባር የሚቆጥሩ ብዙ ናቸው። እንዲያውም "ለምን ስም ሳትጠቅሱ ሃሳቡ ላይ ብቻ እርምት አትሰጡም?" ይላሉ። የሚገርመው እነዚህ "የሰው ስም አታንሱ" የሚሉ አካላት ራሳቸው የሚጠሉትን ሰው ትልቅ ዓሊም እንኳ ቢሆን ስሙን ጠርተው ከማብጠልጠል የማይመለሱ መሆናቸው ነው። ቢሆንም ዳኛችን እልህ ሳይሆን መረጃ መሆን አለበትና በመረጃ እንነጋገራለን።
በቅድሚያ በረባ ባልረባ ስም መጥቀስ እንደማይገባ ለመግለፅ እወዳለሁ። በተለይ ጥፋቱ ህዝብ ጋር ካልደረሰ፣ የተለየ ምክንያት ካልኖረ በስተቀር፣ ወይ በግል መምከር ወይ ሌሎችም እንዲማሩበት ስም ሳይጠቅሱት በደፈናው እርምት መስጠት የነብዩ ﷺ ሱና ነው። ነገር ግን ጥፋቱ አደባባይ ከወጣና ባለበት ቢትተው ህዝብ የሚጎዳ ከሆነ ባደባባይ ምላሽ ይሰጣል። ስለዚህ "በደፈናው ጥፋቱን ማረም ይሻላል ወይስ ስም ጠቅሶ እርምት መስጠት ይሻላል?" የሚለውን መገምገም ወግ ነው። ዛሬ እያየን ያለነው ግን ከነ ጭራሹ ስም ጠቅሶ መናገር ወንጀል እንደሆነ ሰፊውን ህዝብ የሚግቱ አካላትን ነው። አጥፊ በየትኛውም ሁኔታ ስሙ ሊነሳ አይገባም ማለት በኢስላም ታሪክ ፈፅሞ የሌለ፣ ከዐቅልም ያፈነገጠ፣ ከመረጃም የተኳረፈ አስተሳሰብ ነው።
1 - የዐቅል ማስረጃ፦
ሰዎች ላይ ዱንያቸውንም ይሁን ኣኺራቸውን የሚጎዳ ጥፋት የሚያደርስ አካል ስሙን ጠቅሰን ብናስጠነቅቅ ጉዳቱን ማስቀረት ወይም መቀነስ የሚቻል ከሆነ ይህንን ማድረግ እንደሚገባ የትኛውም ጤነኛ ዐቅል የሚገነዘበው ነው። ማንም የሚገነዘባቸው ምሳሌዎች ልጥቀስ፦
* ምሳሌ 1 - የምታውቁት ጊዜው ያለፈበት መድሃኒት የሚሸጥ ፋርማሲ አለ እንበል። መድሃኒት ለመግዛት የወጣ ሰው ወደዚያ ሲሄድ ብታዩት ሃሜት እንዳይሆን ብላችሁ ዝም ትላላችሁ? ዝም ብትሉ በሚደርሰው ጉዳት ወንጀለኛ ትሆናላችሁ።
* ምሳሌ 2 - አንድ የህክምና ትምህርት እንደሌለው የምታውቁት ሰው በፎርጂድ ወረቀት ክሊኒክ ቢከፍት አይናችሁ እያየ ህዝብ ላይ ጉዳት ሲያደርስ ሃሜት ይሆናል ብላችሁ ዝም ትላላችሁ ወይስ አስፈላጊውን እርምጃ ትወስዳላችሁ? የሰዎች የኣኺራ ደህንነት ከዱንያዊ ህይወታቸው በላይ ነው።
* ምሳሌ 3 - የሰፈራችሁ አትክልት ቤት ሚዛን የሚቀሽብ እንደሆነ ብታውቁ ልጃችሁ ከዚያ እንዳይገዛ ትናገራላችሁ ወይስ ሃሜት እንዳይሆን በሚል በዝምታ ሐቃችሁ እየተወሰደ ዝም ትላላችሁ? ታዲያ የዲናችን ዋጋ ከቲማቲም ያነሰ ሆኖ ነው ወይ ቢድዐ የሚዘራ፣ ህዝብ የሚያሳስት ሰው ስሙ ሲነሳ የሚጎረብጠን? ብዙ ምሳሌዎችን መዘርዘር ቢቻልም በቀረቡት ልብቃቃ። "ጨዋ ጥቆማ ይበቃዋል።"
2 - የሐዲሥ ማስረጃ
ሀ - ፋጢማህ ቢንት ቀይስ - ረዲየላሁ ዐንሃ - ሁለት ሰዎች ለትዳር ጠየቋት፣ አቡ ጀህም እና ሙዓዊያህ። ጉዳዩን ለነብዩ ﷺ ስታማክራቸው እንዲህ አሏት ፡-
أَمَّا أَبُو جَهْمٍ، فَلَا يَضَعُ عَصَاهُ عَنْ عَاتِقِهِ، وَأَمَّا مُعَاوِيَةُ، فَصُعْلُوكٌ، لَا مَالَ لَهُ، انْكِحِي أُسَامَةَ بْنَ زَيْدٍ
“አቡ ጀህም ዱላውን ከትከሻው አያወርድም (ይማታል)። ሙዓዊያ ደግሞ ድሃ ነው፣ ገንዘብ የለውም። ይልቅ ኡሳመቱ ብኑ ዘይድን አግቢ።” [ሶሒሕ ሙስሊም: 3770]
ልብ በሉ! ሰዎቹን በሌሉበት ነው ስማቸውን ያነሱት። በአንዲት ሴት የትዳር ጉዳይ አስፈላጊ ሲሆን የሰዎችን ስም ማንሳት ከተቻለ፣ ዲንን የሚያጠለሹ፣ ወደ ቢድዐ የሚጣሩ ሰዎችን ስም ጠቅሶ ማስጠንቀቅ ደግሞ የበለጠ ተገቢ ነው።
ለ - እናታችን ዓኢሻህ - ረዲየላሁ ዐንሃ - እንዲህ ብላለች፦
قالت هِنْدُ امْرَأةُ أَبي سفْيَانَ للنَّبيِّ صلى الله عليه وسلم: إنَّ أَبَا سُفْيَانَ رَجُلٌ شَحِيحٌ وَلَيْسَ يُعْطِينِي مَا يَكْفيني وولَدِي إِلا مَا أَخَذْتُ مِنْهُ، وَهُوَ لا يَعْلَمُ؟ قَالَ: ((خُذِي مَا يَكْفِيكِ وَوَلدَكِ بِالمَعْرُوفِ
"የአቡ ሱፍያን ሚስት ሂንድ ለነብዩ ﷺ 'አባ ሱፍያን ስስታም ሰው ነው። እሱ ሳያውቅ የምወስድበት ካልሆነ በቀር ለኔና ለልጄ የሚበቃንን አይሰጠንም' አለቻቸው። 'ላንቺም ለልጅሽም የሚበቃ በልኩ ውሰጂ' አሏት።'' [አልቡኻሪይ፡ 5364] [ሙስሊም፡ 3532]
ልብ በሉ! የአቡ ሱፍያን ነውር በሌለበት ሲነሳ "ሃሜት ነው ተይ!" አላሏትም።
የነዚህን ሐዲሦች መልእክት ዋጋ ለማሳጣት ውሃ የማያነሳ ትንታኔ የሚሰጡ፣ በዱንያዊ ጉዳይ ላይ ብቻ የሚገድቡ ሰዎች አሉ። ይሄ ግን ግልፅ ስህተት ነው። ጉዳዩን እኛ ስናነሳው ለማይዋጣቸው አካላት በሚያከብሯቸው ሸይኽ እንሞግታቸዋለን። ነወዊይ በታዋቂው ሪያዱ ሷሊሒን ኪታባቸው ላይ "باب مَا يباح من الغيبة" የሚል ሰዎችን በሌሉበት ነውራቸውን ማንሳት የሚቻልበት ሁኔታ ለማሳየት አንድ ርእስ ቋጥረዋል። በስሩም ሰዎችን ስማቸውን ማንሳት የሚቻልባቸው ስድስት ምክንያቶች እንዳሉ የዘረዘሩ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ አራተኛ ላይ የጠቀሱት እንዲህ የሚል ነው፦
الرَّابعُ: تَحْذِيرُ المُسْلِمينَ مِنَ الشَّرِّ وَنَصِيحَتُهُمْ
"ሙስሊሞችን ከነዚህ ሰዎች ክፋት ለማስጠንቀቅና ምክር ለመለገስ ነው።"
ዝርዝር የፈለገ ማብራሪያቸውን ይመልከት።
3 - የሰለፎች ፈለግ
ከነወዊይ ይልቅ ይበልጥ ክብደት ያለው ደግሞ የሰለፎች ፈለግ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ያሉ የሰለፎች ንግግሮች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው። ልብ በሉ! የምጠቅሳቸው አካላት ሁሉም ከሞቱ ከአንድ ሺህ አመት በላይ ያለፋቸው ቀደምት የኢስላም ሊቃውንት ናቸው።
ሀ. ታቢዒዩ ሐሰን አልበስሪይ (110 ሂ.):- “ለቢድዐ ሰው ሃሜት የለውም! (ስሙ መነሳቱ ከሃሜት አይቆጠርም)። አመፁን ባደባባይ ለሚያወጣ አመፀኛም ሃሜት የለም” ብለዋል። [ሸርሑ ኡሱሊ ሱናህ፣ ላለካኢ፡ 1/158]
ለ. ታቢዒዩ ቀታዳህ ብኑ ዲዓማ አሰዱሲይ (117 ሂ.)
ዓሲም አልአሕወል እንዲህ ይላሉ፡- “ቀታዳ ዘንድ ተቀምጬ ነበር። ዐምር ብኑ ዑበይድ ስሙ ሲወሳ በክፉ አነሳው። 'ዑለማኦች አንዱ በሌላው ላይ እንደሚናገር አላውቅም ነበር' ስለው 'አሕወል ሆይ! አንድ ሰው ቢድዐ ሲያንፀባርቅ ሰዎች ይጠነቀቁት ዘንድ ስሙ ሊጠቀስ እንደሚገባ አታውቅም'ንዴ?' አለኝ።” [አልሚዛን፡ 5/330]
ሐ. ዐብዱላህ ብኑል ሙባረክ (181 ሂ.):-
በአንድ ወቅት “ሙዐላ ብኑ ሂላል ጥሩ ሰው ነበር በሐዲሥ ላይ ይዋሻል እንጂ” ይላሉ። በዚህን ጊዜ የሆነ ሱፊይ ሰማቸውና “የዐብዱረሕማን አባት ሆይ! እንዴት ሰው ታማለህ?” አላቸው። ኢብኑ ሙባረክ ታዲያ፡ “ዝም በል! ግልፅ ካላደረግን እውነትና ሃሰት እንዴት ይልለያል?!” አሉት። [አልኪፋያህ፡ 9]
መ. ዑቅባህ ብኑ ዐልቀማህ (204 ሂ.) እንዲህ ይላሉ፡-
(መረጃ ለሚያከብሩ ብቻ!)
~
ዛሬ ዛሬ የቢድዐ አራማጆች ወይም ተሻጋሪ ጥፋት የሚያደርሱ አካላት ላይ ስማቸውን ጠቅሶ ምላሽ መስጠትን እንደ አፍራሽ ተግባር የሚቆጥሩ ብዙ ናቸው። እንዲያውም "ለምን ስም ሳትጠቅሱ ሃሳቡ ላይ ብቻ እርምት አትሰጡም?" ይላሉ። የሚገርመው እነዚህ "የሰው ስም አታንሱ" የሚሉ አካላት ራሳቸው የሚጠሉትን ሰው ትልቅ ዓሊም እንኳ ቢሆን ስሙን ጠርተው ከማብጠልጠል የማይመለሱ መሆናቸው ነው። ቢሆንም ዳኛችን እልህ ሳይሆን መረጃ መሆን አለበትና በመረጃ እንነጋገራለን።
በቅድሚያ በረባ ባልረባ ስም መጥቀስ እንደማይገባ ለመግለፅ እወዳለሁ። በተለይ ጥፋቱ ህዝብ ጋር ካልደረሰ፣ የተለየ ምክንያት ካልኖረ በስተቀር፣ ወይ በግል መምከር ወይ ሌሎችም እንዲማሩበት ስም ሳይጠቅሱት በደፈናው እርምት መስጠት የነብዩ ﷺ ሱና ነው። ነገር ግን ጥፋቱ አደባባይ ከወጣና ባለበት ቢትተው ህዝብ የሚጎዳ ከሆነ ባደባባይ ምላሽ ይሰጣል። ስለዚህ "በደፈናው ጥፋቱን ማረም ይሻላል ወይስ ስም ጠቅሶ እርምት መስጠት ይሻላል?" የሚለውን መገምገም ወግ ነው። ዛሬ እያየን ያለነው ግን ከነ ጭራሹ ስም ጠቅሶ መናገር ወንጀል እንደሆነ ሰፊውን ህዝብ የሚግቱ አካላትን ነው። አጥፊ በየትኛውም ሁኔታ ስሙ ሊነሳ አይገባም ማለት በኢስላም ታሪክ ፈፅሞ የሌለ፣ ከዐቅልም ያፈነገጠ፣ ከመረጃም የተኳረፈ አስተሳሰብ ነው።
1 - የዐቅል ማስረጃ፦
ሰዎች ላይ ዱንያቸውንም ይሁን ኣኺራቸውን የሚጎዳ ጥፋት የሚያደርስ አካል ስሙን ጠቅሰን ብናስጠነቅቅ ጉዳቱን ማስቀረት ወይም መቀነስ የሚቻል ከሆነ ይህንን ማድረግ እንደሚገባ የትኛውም ጤነኛ ዐቅል የሚገነዘበው ነው። ማንም የሚገነዘባቸው ምሳሌዎች ልጥቀስ፦
* ምሳሌ 1 - የምታውቁት ጊዜው ያለፈበት መድሃኒት የሚሸጥ ፋርማሲ አለ እንበል። መድሃኒት ለመግዛት የወጣ ሰው ወደዚያ ሲሄድ ብታዩት ሃሜት እንዳይሆን ብላችሁ ዝም ትላላችሁ? ዝም ብትሉ በሚደርሰው ጉዳት ወንጀለኛ ትሆናላችሁ።
* ምሳሌ 2 - አንድ የህክምና ትምህርት እንደሌለው የምታውቁት ሰው በፎርጂድ ወረቀት ክሊኒክ ቢከፍት አይናችሁ እያየ ህዝብ ላይ ጉዳት ሲያደርስ ሃሜት ይሆናል ብላችሁ ዝም ትላላችሁ ወይስ አስፈላጊውን እርምጃ ትወስዳላችሁ? የሰዎች የኣኺራ ደህንነት ከዱንያዊ ህይወታቸው በላይ ነው።
* ምሳሌ 3 - የሰፈራችሁ አትክልት ቤት ሚዛን የሚቀሽብ እንደሆነ ብታውቁ ልጃችሁ ከዚያ እንዳይገዛ ትናገራላችሁ ወይስ ሃሜት እንዳይሆን በሚል በዝምታ ሐቃችሁ እየተወሰደ ዝም ትላላችሁ? ታዲያ የዲናችን ዋጋ ከቲማቲም ያነሰ ሆኖ ነው ወይ ቢድዐ የሚዘራ፣ ህዝብ የሚያሳስት ሰው ስሙ ሲነሳ የሚጎረብጠን? ብዙ ምሳሌዎችን መዘርዘር ቢቻልም በቀረቡት ልብቃቃ። "ጨዋ ጥቆማ ይበቃዋል።"
2 - የሐዲሥ ማስረጃ
ሀ - ፋጢማህ ቢንት ቀይስ - ረዲየላሁ ዐንሃ - ሁለት ሰዎች ለትዳር ጠየቋት፣ አቡ ጀህም እና ሙዓዊያህ። ጉዳዩን ለነብዩ ﷺ ስታማክራቸው እንዲህ አሏት ፡-
أَمَّا أَبُو جَهْمٍ، فَلَا يَضَعُ عَصَاهُ عَنْ عَاتِقِهِ، وَأَمَّا مُعَاوِيَةُ، فَصُعْلُوكٌ، لَا مَالَ لَهُ، انْكِحِي أُسَامَةَ بْنَ زَيْدٍ
“አቡ ጀህም ዱላውን ከትከሻው አያወርድም (ይማታል)። ሙዓዊያ ደግሞ ድሃ ነው፣ ገንዘብ የለውም። ይልቅ ኡሳመቱ ብኑ ዘይድን አግቢ።” [ሶሒሕ ሙስሊም: 3770]
ልብ በሉ! ሰዎቹን በሌሉበት ነው ስማቸውን ያነሱት። በአንዲት ሴት የትዳር ጉዳይ አስፈላጊ ሲሆን የሰዎችን ስም ማንሳት ከተቻለ፣ ዲንን የሚያጠለሹ፣ ወደ ቢድዐ የሚጣሩ ሰዎችን ስም ጠቅሶ ማስጠንቀቅ ደግሞ የበለጠ ተገቢ ነው።
ለ - እናታችን ዓኢሻህ - ረዲየላሁ ዐንሃ - እንዲህ ብላለች፦
قالت هِنْدُ امْرَأةُ أَبي سفْيَانَ للنَّبيِّ صلى الله عليه وسلم: إنَّ أَبَا سُفْيَانَ رَجُلٌ شَحِيحٌ وَلَيْسَ يُعْطِينِي مَا يَكْفيني وولَدِي إِلا مَا أَخَذْتُ مِنْهُ، وَهُوَ لا يَعْلَمُ؟ قَالَ: ((خُذِي مَا يَكْفِيكِ وَوَلدَكِ بِالمَعْرُوفِ
"የአቡ ሱፍያን ሚስት ሂንድ ለነብዩ ﷺ 'አባ ሱፍያን ስስታም ሰው ነው። እሱ ሳያውቅ የምወስድበት ካልሆነ በቀር ለኔና ለልጄ የሚበቃንን አይሰጠንም' አለቻቸው። 'ላንቺም ለልጅሽም የሚበቃ በልኩ ውሰጂ' አሏት።'' [አልቡኻሪይ፡ 5364] [ሙስሊም፡ 3532]
ልብ በሉ! የአቡ ሱፍያን ነውር በሌለበት ሲነሳ "ሃሜት ነው ተይ!" አላሏትም።
የነዚህን ሐዲሦች መልእክት ዋጋ ለማሳጣት ውሃ የማያነሳ ትንታኔ የሚሰጡ፣ በዱንያዊ ጉዳይ ላይ ብቻ የሚገድቡ ሰዎች አሉ። ይሄ ግን ግልፅ ስህተት ነው። ጉዳዩን እኛ ስናነሳው ለማይዋጣቸው አካላት በሚያከብሯቸው ሸይኽ እንሞግታቸዋለን። ነወዊይ በታዋቂው ሪያዱ ሷሊሒን ኪታባቸው ላይ "باب مَا يباح من الغيبة" የሚል ሰዎችን በሌሉበት ነውራቸውን ማንሳት የሚቻልበት ሁኔታ ለማሳየት አንድ ርእስ ቋጥረዋል። በስሩም ሰዎችን ስማቸውን ማንሳት የሚቻልባቸው ስድስት ምክንያቶች እንዳሉ የዘረዘሩ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ አራተኛ ላይ የጠቀሱት እንዲህ የሚል ነው፦
الرَّابعُ: تَحْذِيرُ المُسْلِمينَ مِنَ الشَّرِّ وَنَصِيحَتُهُمْ
"ሙስሊሞችን ከነዚህ ሰዎች ክፋት ለማስጠንቀቅና ምክር ለመለገስ ነው።"
ዝርዝር የፈለገ ማብራሪያቸውን ይመልከት።
3 - የሰለፎች ፈለግ
ከነወዊይ ይልቅ ይበልጥ ክብደት ያለው ደግሞ የሰለፎች ፈለግ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ያሉ የሰለፎች ንግግሮች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው። ልብ በሉ! የምጠቅሳቸው አካላት ሁሉም ከሞቱ ከአንድ ሺህ አመት በላይ ያለፋቸው ቀደምት የኢስላም ሊቃውንት ናቸው።
ሀ. ታቢዒዩ ሐሰን አልበስሪይ (110 ሂ.):- “ለቢድዐ ሰው ሃሜት የለውም! (ስሙ መነሳቱ ከሃሜት አይቆጠርም)። አመፁን ባደባባይ ለሚያወጣ አመፀኛም ሃሜት የለም” ብለዋል። [ሸርሑ ኡሱሊ ሱናህ፣ ላለካኢ፡ 1/158]
ለ. ታቢዒዩ ቀታዳህ ብኑ ዲዓማ አሰዱሲይ (117 ሂ.)
ዓሲም አልአሕወል እንዲህ ይላሉ፡- “ቀታዳ ዘንድ ተቀምጬ ነበር። ዐምር ብኑ ዑበይድ ስሙ ሲወሳ በክፉ አነሳው። 'ዑለማኦች አንዱ በሌላው ላይ እንደሚናገር አላውቅም ነበር' ስለው 'አሕወል ሆይ! አንድ ሰው ቢድዐ ሲያንፀባርቅ ሰዎች ይጠነቀቁት ዘንድ ስሙ ሊጠቀስ እንደሚገባ አታውቅም'ንዴ?' አለኝ።” [አልሚዛን፡ 5/330]
ሐ. ዐብዱላህ ብኑል ሙባረክ (181 ሂ.):-
በአንድ ወቅት “ሙዐላ ብኑ ሂላል ጥሩ ሰው ነበር በሐዲሥ ላይ ይዋሻል እንጂ” ይላሉ። በዚህን ጊዜ የሆነ ሱፊይ ሰማቸውና “የዐብዱረሕማን አባት ሆይ! እንዴት ሰው ታማለህ?” አላቸው። ኢብኑ ሙባረክ ታዲያ፡ “ዝም በል! ግልፅ ካላደረግን እውነትና ሃሰት እንዴት ይልለያል?!” አሉት። [አልኪፋያህ፡ 9]
መ. ዑቅባህ ብኑ ዐልቀማህ (204 ሂ.) እንዲህ ይላሉ፡-
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
“በአንድ ወቅት ከአርጣህ ብኑ ሙንዚር ጋር ነበርኩኝ። በቦታው ከነበሩ ሰዎች አንዱ ‘ከአህሉ ሱና ጋር እየተቀመጠ፣ እየተቀላቀላቸው ስለ ቢድዐ ሰዎች ሲወራ ግን ‘ተውን እንግዲህ ስማቸውን አታንሱ’ ስለሚል ሰው ምን ትላላችሁ’ ሲል ጠየቀ። አርጣህ፡ ‘እሱ እራሱ ከነሱ ነው። እንዳያታልላችሁ!’ አለ።
ይሄ የአርጣህ ንግግር አልተመቸኝምና ወደ አውዛዒይ ሄድኩኝ። አውዛዒይ እንዲህ አይነት ነገሮች ሲደርሱት ገላጭ ነበር። ጠየቅኩት። ‘አርጣህ እውነት ተናግሯል። ሐቁ እሱ ያለው ነው። ይሄ ሰውየ ስማቸው እንዳይነሳ ይከለክላል። ስማቸው ካልተገለፀ እንዴት ሰዎች ይጠነቀቋቸዋል?!’ አለ።” [ታሪኹ ዲመሽቅ፡ 8/15]
ሠ. ኢማሙ አሕመድ (241 ሂ.):-
ሙሐመድ ብኑ በንዳር፡ “በውኑ እኔ እከሌ እንዲህ ነው፣ እከሌ እንዲህ ነው ማለት ይከብደኛል” ቢላቸው፣ ኢማሙ አሕመድ፡ “አንተም ዝም ካልክ፣ እኔም ዝም ካልኩ መሀ .ይም የሆነ ሰው ጤነኛውን ከበሽ .ተኛው እንዴት ይለየው?!” ብለው መለሱላቸው። [አልፈታዋ፡ 28/231]
4 - ኢጅማዕ
አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የአጥፊዎችን ስም ጠቅሶ መናገር የዑለማእ ኢጅማዕ እንዳለበት ኢብኑ ረጀብ ጠቅሰዋል። [አልፈርቅ በይነ ነሲሐ ወትተዕዪር፡ 25]
በድጋሜ የማስታውሰው ከነዚህ የሰው ስም አታንሱ ከሚሉ ሰዎች ውስጥ የሰው ስም የማያነሳ የለም። “ስም አታንሱ” የሚሉት የኛ በሚሉት አካል ላይ የሚሰጠውን ሂስ ዝም ለማሰኘት እንጂ አነሰም በዛ ራሳቸውም የሰው ስም ከማንሳት የሚቆጠቡ አይደሉም።
ሰላም።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ የካቲት ዐ4/2009)
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
ይሄ የአርጣህ ንግግር አልተመቸኝምና ወደ አውዛዒይ ሄድኩኝ። አውዛዒይ እንዲህ አይነት ነገሮች ሲደርሱት ገላጭ ነበር። ጠየቅኩት። ‘አርጣህ እውነት ተናግሯል። ሐቁ እሱ ያለው ነው። ይሄ ሰውየ ስማቸው እንዳይነሳ ይከለክላል። ስማቸው ካልተገለፀ እንዴት ሰዎች ይጠነቀቋቸዋል?!’ አለ።” [ታሪኹ ዲመሽቅ፡ 8/15]
ሠ. ኢማሙ አሕመድ (241 ሂ.):-
ሙሐመድ ብኑ በንዳር፡ “በውኑ እኔ እከሌ እንዲህ ነው፣ እከሌ እንዲህ ነው ማለት ይከብደኛል” ቢላቸው፣ ኢማሙ አሕመድ፡ “አንተም ዝም ካልክ፣ እኔም ዝም ካልኩ መሀ .ይም የሆነ ሰው ጤነኛውን ከበሽ .ተኛው እንዴት ይለየው?!” ብለው መለሱላቸው። [አልፈታዋ፡ 28/231]
4 - ኢጅማዕ
አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የአጥፊዎችን ስም ጠቅሶ መናገር የዑለማእ ኢጅማዕ እንዳለበት ኢብኑ ረጀብ ጠቅሰዋል። [አልፈርቅ በይነ ነሲሐ ወትተዕዪር፡ 25]
በድጋሜ የማስታውሰው ከነዚህ የሰው ስም አታንሱ ከሚሉ ሰዎች ውስጥ የሰው ስም የማያነሳ የለም። “ስም አታንሱ” የሚሉት የኛ በሚሉት አካል ላይ የሚሰጠውን ሂስ ዝም ለማሰኘት እንጂ አነሰም በዛ ራሳቸውም የሰው ስም ከማንሳት የሚቆጠቡ አይደሉም።
ሰላም።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ የካቲት ዐ4/2009)
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ደዕዋ ላይ ለተሰማራችሁ ወይም ሃሳቡ ላላችሁ ሁሉ!
~
ኢስላምን ማስተማር አቻ የሌለው ዘርፍ ነው። ከዐርሹ በላይ የሆነው አላህ እንዲህ ይላል፦
{ وَمَنۡ أَحۡسَنُ قَوۡلࣰا مِّمَّن دَعَاۤ إِلَى ٱللَّهِ وَعَمِلَ صَـٰلِحࣰا وَقَالَ إِنَّنِی مِنَ ٱلۡمُسۡلِمِینَ }
"ወደ አላህ ከጠራና መልካምንም ከሠራ፣ 'እኔ ከሙስሊሞች ነኝ' ካለም ሰው ይበልጥ ቃሉ ያማረ ማን ነው?" [አልፉሲለት፡: 33]
የሃገራችን ቁርኣንን የማስተማር ስልት በጣም ደካማ ነው። ወደ ገጠሩ ደግሞ ችግሩ ይብሳል። ስለዚህ ራሳችሁን በሚገባ አዘጋጁና ቁርኣንን አስተምሩ። ቁርኣንን ማስተማር :-
1- ከፍ ያለ ደረጃን ለመጎናፀፍ ወሳኝ ሰበብ ነው። ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
خَيْرُكُمْ مَنْ تَعَلَّمَ الْقُرْآنَ وَعَلَّمَهُ
"ከናንተ በላጫችሁ ቁርኣንን ተምሮ ያስተማረ ነው።" [ቡኻሪይ ፡ 5027]
2. ቁርኣንን ማስተማር ትውልድ መገንቢያ ሁነኛ መንገድ ነው። ልጆች በዚህ እድሜያቸው ገና ሱስ አያውቁም። አእምሯቸው ከብልሹ አመለካከቶች ንፁህ ነው። ስለዚህ ቁርኣንን በጥሩ ሁኔታ ካስተማርናቸው በሂደት ከስር ጀምረን መሰረታዊ ትምህርቶችን በማስከተል ለመኮትኮት ሰፊ እድል እናገኛለን። የዒልም ጉጉት እንዲያድርባቸውም ማድረግ እንችላለን።
3. ወላጅ በአብዛኛው ለቁርኣን ልዩ ቦታ አለው። እኛ ልጆቹን በአካባቢው ካሉት በተሻለ መንገድ ካስተማርናቸው እና ፍሬው በግልፅ የሚታይ ከሆነ አጠቃላይ የደዕዋ አካሄዳችን ላይ እንቅፋት የመሆን እድሉ አናሳ ነው። ስለዚህ የአካባቢያችንን የዲን ግንዛቤ ለመቀየር እጅግ ትርጉም ያለው ስራ መስራት እንችላለን።
ነገር ግን እነዚህን ፍሬዎች ለማግኘት የማስተማር ስልታችን በአካባቢው ካሉት የተሻለ አያያዝ ያለው፣ ጥራት ያለው፣ በንፅፅር በአጭር ጊዜ ለውጥ የሚታይበት ሊሆን ይገባል። ቢቻል በርብርብ፣ ካልሆነ ለብቻችንም ቢሆን መስራት እንችላለን። የማስተማሩ ስራ በወንድም፣ በሴትም፣ በመስጂድም፣ በቤትም መሆን ይችላል። እናስብበት። አላህ ያግዘናል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
ኢስላምን ማስተማር አቻ የሌለው ዘርፍ ነው። ከዐርሹ በላይ የሆነው አላህ እንዲህ ይላል፦
{ وَمَنۡ أَحۡسَنُ قَوۡلࣰا مِّمَّن دَعَاۤ إِلَى ٱللَّهِ وَعَمِلَ صَـٰلِحࣰا وَقَالَ إِنَّنِی مِنَ ٱلۡمُسۡلِمِینَ }
"ወደ አላህ ከጠራና መልካምንም ከሠራ፣ 'እኔ ከሙስሊሞች ነኝ' ካለም ሰው ይበልጥ ቃሉ ያማረ ማን ነው?" [አልፉሲለት፡: 33]
የሃገራችን ቁርኣንን የማስተማር ስልት በጣም ደካማ ነው። ወደ ገጠሩ ደግሞ ችግሩ ይብሳል። ስለዚህ ራሳችሁን በሚገባ አዘጋጁና ቁርኣንን አስተምሩ። ቁርኣንን ማስተማር :-
1- ከፍ ያለ ደረጃን ለመጎናፀፍ ወሳኝ ሰበብ ነው። ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
خَيْرُكُمْ مَنْ تَعَلَّمَ الْقُرْآنَ وَعَلَّمَهُ
"ከናንተ በላጫችሁ ቁርኣንን ተምሮ ያስተማረ ነው።" [ቡኻሪይ ፡ 5027]
2. ቁርኣንን ማስተማር ትውልድ መገንቢያ ሁነኛ መንገድ ነው። ልጆች በዚህ እድሜያቸው ገና ሱስ አያውቁም። አእምሯቸው ከብልሹ አመለካከቶች ንፁህ ነው። ስለዚህ ቁርኣንን በጥሩ ሁኔታ ካስተማርናቸው በሂደት ከስር ጀምረን መሰረታዊ ትምህርቶችን በማስከተል ለመኮትኮት ሰፊ እድል እናገኛለን። የዒልም ጉጉት እንዲያድርባቸውም ማድረግ እንችላለን።
3. ወላጅ በአብዛኛው ለቁርኣን ልዩ ቦታ አለው። እኛ ልጆቹን በአካባቢው ካሉት በተሻለ መንገድ ካስተማርናቸው እና ፍሬው በግልፅ የሚታይ ከሆነ አጠቃላይ የደዕዋ አካሄዳችን ላይ እንቅፋት የመሆን እድሉ አናሳ ነው። ስለዚህ የአካባቢያችንን የዲን ግንዛቤ ለመቀየር እጅግ ትርጉም ያለው ስራ መስራት እንችላለን።
ነገር ግን እነዚህን ፍሬዎች ለማግኘት የማስተማር ስልታችን በአካባቢው ካሉት የተሻለ አያያዝ ያለው፣ ጥራት ያለው፣ በንፅፅር በአጭር ጊዜ ለውጥ የሚታይበት ሊሆን ይገባል። ቢቻል በርብርብ፣ ካልሆነ ለብቻችንም ቢሆን መስራት እንችላለን። የማስተማሩ ስራ በወንድም፣ በሴትም፣ በመስጂድም፣ በቤትም መሆን ይችላል። እናስብበት። አላህ ያግዘናል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
ሲጋራ ማጨስም፣ መነገዱም ሐራም ነው!
~
ሲጋራ ማጨስ አጫሹም ይሁን በቅርቡ ያሉ ሰዎችን ከባድ የጤና ጉዳት የሚያደርስ ሱስ ነው። ጎጂ ነገር በኢስላም ሐራም ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
وَلا تُلْقُوا بِأَيْدِيكُمْ إِلَى التَّهْلُكَةِ
"ራሳችሁን ወደ ጥፋት አትጣሉ።" [አልበቀራ፡ 195]
ነብያችንም ﷺ "መጉዳትም መበቀልም የለም (አይፈቀድም)" ብለዋል። ኢብኑ ማጀህ ዘግበውታል (2341)። አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 7517]
ስለሆነም ጎጂ ነገርን መጠቀምም በጎጂ ነገር መነገድም ሐራም ነው። ሸይኽ ኢብኑል ዑሠይሚን - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
"ለማንም ሰው ሲጋራ ሊሸጥ አይፈቀድለትም። ምክንያቱም ሲጋራ የተከለከለ ነውና። አላህ አንድን ነገር ከከለከለ የሽያጭ ዋጋውንም ነው የሚከለክለው። እንዲሁም ሲጋራን መሸጥ በወንጀልና ወሰን በመተላለፍ ላይ መተባበር ነው።" [አሊቃኡ ሸህሪይ፡ 22/57]
ኢብኑ ባዝ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ብለዋል፦
"ሲጋራ ማጨሱም፣ መሸጡም፣ በሱ መነገዱም አይፈቀድም። በዚህ ላይ ከባድ ጉዳትና መጥፎ ፍፃሜ አለበትና።" [አልፈታዋ፡ 6/456]
ሲጋራ ለሌሎች መግዛትም አይፈቀድም። በሐራም ነገር መተባበርም አይቻልም። አላህ እንዲህ ብሏል፦
{ وَلَا تَعَاوَنُوا۟ عَلَى ٱلۡإِثۡمِ وَٱلۡعُدۡوَ ٰنِۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَۖ إِنَّ ٱللَّهَ شَدِیدُ ٱلۡعِقَابِ }
"በኃጢአትና ወሰንን በማለፍ አትረዳዱ። አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና።" [አልማኢደህ: 2]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
ሲጋራ ማጨስ አጫሹም ይሁን በቅርቡ ያሉ ሰዎችን ከባድ የጤና ጉዳት የሚያደርስ ሱስ ነው። ጎጂ ነገር በኢስላም ሐራም ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
وَلا تُلْقُوا بِأَيْدِيكُمْ إِلَى التَّهْلُكَةِ
"ራሳችሁን ወደ ጥፋት አትጣሉ።" [አልበቀራ፡ 195]
ነብያችንም ﷺ "መጉዳትም መበቀልም የለም (አይፈቀድም)" ብለዋል። ኢብኑ ማጀህ ዘግበውታል (2341)። አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 7517]
ስለሆነም ጎጂ ነገርን መጠቀምም በጎጂ ነገር መነገድም ሐራም ነው። ሸይኽ ኢብኑል ዑሠይሚን - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
"ለማንም ሰው ሲጋራ ሊሸጥ አይፈቀድለትም። ምክንያቱም ሲጋራ የተከለከለ ነውና። አላህ አንድን ነገር ከከለከለ የሽያጭ ዋጋውንም ነው የሚከለክለው። እንዲሁም ሲጋራን መሸጥ በወንጀልና ወሰን በመተላለፍ ላይ መተባበር ነው።" [አሊቃኡ ሸህሪይ፡ 22/57]
ኢብኑ ባዝ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ብለዋል፦
"ሲጋራ ማጨሱም፣ መሸጡም፣ በሱ መነገዱም አይፈቀድም። በዚህ ላይ ከባድ ጉዳትና መጥፎ ፍፃሜ አለበትና።" [አልፈታዋ፡ 6/456]
ሲጋራ ለሌሎች መግዛትም አይፈቀድም። በሐራም ነገር መተባበርም አይቻልም። አላህ እንዲህ ብሏል፦
{ وَلَا تَعَاوَنُوا۟ عَلَى ٱلۡإِثۡمِ وَٱلۡعُدۡوَ ٰنِۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَۖ إِنَّ ٱللَّهَ شَدِیدُ ٱلۡعِقَابِ }
"በኃጢአትና ወሰንን በማለፍ አትረዳዱ። አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና።" [አልማኢደህ: 2]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ሸውካኒ እና መውሊድ (ወሳኝ ነጥቦች የተዳሰሱበት)
~
ሙሐመድ ብኑ ዐሊ አሸውካኒ በ1250 ሂ. የሞቱ ታላቅ የመናዊ ዓሊም ናቸው፡፡ በሰፊው የሚታወቁ ስለሆኑ እሳቸውን በማስተዋወቅ ረጅሙን ፅሑፌን ይበልጥ ማስረዘም አልሻም፡፡ ሸውካኒ መውሊድ ላይ እጅግ የሰላ ትችት ሰንዝረዋል፡፡ ዛሬ በተደጋጋሚ ከምንሰማቸው መውሊድ ተኮር ጥያቄዎች ውስጥ የተወሰኑትን በመምዘዝ በሸውካኒ ንግግር ምላሽ እሰጣለሁ፡፡ ሙሉ ንግግራቸውን መመልከት የፈለገ ሰው “አልፈትሑ ረባኒ ሚን ፈታዋ አልኢማሚ ሸውካኒ” በተሰኘው የፈትዋ መድብላቸው ውስጥ ሁለተኛውን ጥራዝ ከገፅ 1087-1101 ድረስ መመልከት ይችላል፡፡ (ፅሑፉ ስለ ረዘመ ዐረብኛውን ማካተት አልቻልኩም፡፡)
1. መውሊድ የሸሪዐ መነሻ አለውን?
ሸውካኒ፡- “እስካሁን ድረስ ከቁርኣንም፣ ከሱናም፣ ከኢጅማዕም፣ ከቂያስም (ንፅፅራዊ ምልከታም) መሰረት እንዳለው የሚያመላክት መረጃ አላገኘሁለትም፡፡” [ገፅ፡ 2/1087]
2. መውሊድን ሰለፎች ያውቁታል?
ሸውካኒ፡- “እንዲያውም ከዘመናት ሁሉ ምርጡ በሆነው (የሶሐቦች) ዘመንም፣ ከነሱ ቀጥሎ በነበሩትም፣ ቀጥሎ በነበሩትም (ዘመን) እንዳልነበር ሙስሊሞች ወጥ አቋም ይዘዋል (ኢጅማዕ አድርገዋል፡፡)” [ገፅ፡ 2/1087]
3. ቢድዐ በመሆኑ ላይ ልዩነት አለ?
ሸውካኒ፡- “ቢድዐ በመሆኑ ላይ ከሙስሊሞች አንድ እንኳን የተቃወመ የለም፡፡” [ገፅ፡ 2/1088] “ይሄ ነገር ቢድዐ በመሆኑ ላይ ከሁሉም ሙስሊሞች ኢጅማዕ እንዳለበት አረጋግጠንልሃል፡፡” [ገፅ፡ 2/1091]
4. መውሊድን በሚደግፉ መሻይኾች ማስፈራራት ያዋጣል?
ሸውካኒ፡- “በምርጡ ነብይ ﷺ የማያሻማ ምስክርነት ቢድዐ ሁሉ ጥመት እንደሆነ ተነግሮ ሳለ የመውሊድን ቢድዐ መሆን ካመነ በኋላ ይፈቀዳል የሚል ሰው የተናገረው ከንፁሁ ሸሪዐ ጋር የሚፃረር ንግግር ነው፡፡ ያለ አንድ ተጨባጭ እውቀታዊ መነሻ ቢድዐን ወደተለያዩ ክፍሎች ለከፈለ ሰው በጭፍን ከመከተል ያለፈ ነገርም የለውም፡፡ የትኛውንም አቋም ይቻላል የሚልን ሰው ይህንን ቢድዐ በተለየ የሚመለከት ማስረጃ ካቀረበ በኋላ እንጂ አንቀበለውም፡፡ … እንጂ ‘እከሌ እንዲህ አለ’፣ ‘እከሌ እንዲህ አይነት ኪታብ አዘጋጅቷል’ የሚል ባዶ ንግግር ፋይዳ የለውም፡፡ ሐቅ ከየትኛውም አካል ይበልጣልና፡፡” [ገፅ፡ 2/1088 - 1089]
“ከነሱ (ከፈቃጆቹ) ውስጥ ቢድዐነቱን አምኖ መጥፎ ነገር ካልተቆራኘው በሚል መስፈርት የፈቀደው አለ፡፡ ምንም ማስረጃ ግን አላመጣም፡፡” [ገፅ፡ 2/1094]
ኢብኑ ሐጀር እንዳደረገው የዓሹራን ፆም ማስረጃ ማድረግ፣ ወይም ሲዩጢ እንዳደረገው ከነብይነት በኋላ ለራሳቸው ዐቂቃ ማውጣታቸውን መመርኮዝ ቢድዐን የማፅናት ፍቅር እንዲህ አይነት ነገር ላይ እንደሚጥል ከሚያሳዩ አስገራሚ ነገሮች ውስጥ ነው፡፡ [ገፅ፡ 1095]
5. መውሊድ የብዙሃን ሙስሊሞች ድጋፍ ነበረውን?
ሸውካኒ፡- “በሰዎች ንግግሮች ላይ የምንመረኮዝ ከሆንና የእንቶ ፈንቶ ጅራቶችን የምንጨብጥ ከሆንን መታወቅ ያለበት ነገር ቢኖር ‘ይፈቀዳል’ ባዮቹ ከሙስሊሞች በአቋም ያፈነገጡ ናቸው፡፡ …” [ገፅ፡ 2/1087-1089]
“ሲጨመቅ የመውሊድ ፈቃጆች ከከልካዮቹ አንፃር ሲታዩ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ለዚያውም እነሱም ቢሆኑ ምግብ ለማብላትና ለዚክር ካልሆነ በስተቀር እንደማይቻል ተስማምተዋል፡፡” [ገፅ፡ 1095–1099]
(አስተውሉ! ይህ እንግዲህ በሸውካኒ ዘመን ነው፡፡ የሞቱት በ1250 ሂ. ሲሆን ሁለት መቶ አመት ሊሞላቸው ጥቂት ነው የቀራቸው፡፡ ሱፊያ ደፋር ነውና የዛሬን የመውሊድ ጨፋሪዎች በመመልከት ሸውካኒን “ውሸታም ነው” እንዳይሉ እሰጋለሁ፡፡)
6. መውሊድ እንዴት ተስፋፋ?
ሸውካኒ፡- “ግና ቢድዐን በማፅናትም ሆነ በማጥፋት ላይ ንጉሳን ተፅእኖ አላቸው፡፡ ይህንን ቢድዐ (በሱኒው ዓለም ውስጥ) የፈጠረው ያ ንጉስ (ሙዞፈር) ሲሆን ኢብኑ ዲሕያ ደግሞ ‘አተንዊር ፊ መውሊዲል በሺር ነዚር’ የተሰኘ ኪታብ በማዘጋጀት አግዞታል፡፡ ሰውየው በዘገባ እውቀት ላይ የጠለቀ ከመሆኑም ጋር በዚህ ኪታቡ ግን ግልፅ ማስረጃ አላቀረበም፡፡ ለዚህ ስራው - ኢብኑ ኸሊካን እንደጠቀሱት - አንድ ሺህ ዲናር በንጉሱ መሸለሙ ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ የዱንያ ፍቅር ከዚህም በላይ ያደርሳል፡፡” [ገፅ፡ 2/1091]
“የቢድዐ ስርጭት ከእሳት ስርጭት የፈጠነ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ መውሊድ፡፡ ምክንያቱም የመሃይማን ነፍሶች ጥግ የደረሰ መናፈቅን ይናፍቁታልና፡፡ በተለይ ደግሞ ከምሁራን፣ ከክቡራንና መሪዎች በርከት ያለ ሰው ከተካፈለበት በኋላ ይሄ ቢድዐ ወሳኝ ከሆኑ ሱናዎች ይመስላቸዋል፡፡ … እንደ መውሊድና አምሳያዎቹ ያሉ ለሐራም ነገሮች የሚያመቻቹ የጥፋት መዳረሻዎች መሃይሞች ፈጥነው እንደሚገቡባቸው አያጠራጥርም፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ በዒልም፣ በክብርና በስልጣን ዝና ያለው ሰው መካፈል ሲታከልበት ሐራም ነገሮችን እንደ ፈጣሪ ትእዛዛት ሲፈፅሙ፣ በድንቁርናና በጥመት ሸለቆች ውስጥ ገብተው ሲዘባርቁ፣ “የተከበሩ እከሌ፣ እከሌ፣ እከሌ፣… ተገኝተዋል” እያሉ ከተቃውሞ ሲያመልጡ የባሰ ይሆናል፡፡
መሃይሙ ህዝብ ይቅርና አንዱ በዒልም ፍለጋ ላይ ገኖ የወጣ ሰው አንዳንድ የኢጅቲሃድ እውቀቶችን ለመማር ከፊቴ ተቀምጦ ነበር፡፡ በዚህ ወር ከተከናወኑ መውሊዶች ውስጥ በአንዱ አዳር ላይ እንደተካፈለ ሲነግረኝ ተቃወምኩት፡፡ አንገሸገሸኝ፡፡ በዚህን ጊዜ ‘ሰዪዲ እከሌ፣ እከሌ፣ እከሌ፣… ተካፍለዋልኮ’ አለኝ፡፡ በነዚህ ታዋቂ ሰዎች ፊት የነበረውን አፈፃፀም ስጠይቀው እንዲህ አለኝ፡-
‘እነዚያ ታዋቂ ሰዎች እየዘፈኑና እያዳመጡ መንዙማውን አንድ ዱርየ አነበበ፡፡ ከዚያም አንዱ ልክ ከእስር የተነሳ ይመስል አፈፍ ብሎ ተነስቶ “መርሐባ ያ ኑረ ዐይኒ፣ መርሐባ” (እንኳን መጣህ ያይኔ ብርሃን እንኳን መጣህ!) ሲል ታዳሚው በመላ ታዋቂዎቹን ጨምሮ ተከትለውት ቆሙ፡፡ እነሱ በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ ቆሞ ማጓራት ያዘ፡፡ አንዱ ታዳሚ ደክሞት ቢቀመጥ ከታዋቂዎቹ ውስጥ አንዱ ንዴቱ ከፊቱ ላይ እየታየ ‘ተነስ! ጨዋታኮ አይደለም!’ ብሎ ጮኸበት፡፡ ቃል በቃል! የአላህ መልእክተኛ ﷺ በዚያች ሰዓት ከነሱ ዘንድ እንደደረሱ ጭራሽ አይጠራጠሩም፡፡ ከዚያም ተጨባበጡ፡፡ ከመሀይማን ከፊሎቹ በእጆቻቸው ሽቶ በመያዝ በፍጥነት ቀቡ፣ ተቀቡ፡፡ ልክ የሳቸውን ﷺ መገኘት ለመጠቀም፡፡’
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን! የዲን ክብር የት ገባ?! ይህም ከጠፋ አይናፋርነት፣ ግብረ ገብነት፣ ህሊና የት ገባ?” [ገፅ፡ 2/1089-91]
7. መውሊድን የነብዩ ﷺ ቤተሰቦች ይደግፉታል?
መውሊድን የሚያከብሩ ሰዎች “ከኛ በላይ ነብዩን ﷺ የሚወድ ላሳር!” የሚሉ ናቸው፡፡ እውነት ለመናገር የነብዩ ﷺ ዘሮች ሙእሚኖች ከሆኑ ለነብዩ ﷺ ያላቸው ፍቅር ልዩ ነው፡፡ መውሊዱ የፍቅር መገለጫ ቢሆን ኖሮ ከማንም ቀድመው ባከበሩት ነበር፡፡ ግን ከነሱ የተገኘው መውሊድን ማክበር፣ ማስከበር፣ ለሱ ሽንጥን ገትሮ መሟገት ነውን?
ሸውካኒ፡- “ከነብዩ ﷺ ንፁሕ ቤተሰብም ይሁን ከተከታዮቻቸው ይህ ነገር እንደሚፈቀድ የተናገረ አንድም ፊደል አላገኘንም፡፡ እንዲያውም ይህቺ ቢድዐ ከተከሰተች ጀምሮ ወደ ጥፋቶች ከሚያሻግሩ አስቀያሚ መዳረሻዎች አንዷ እንደሆነች ንግግሮቻቸው ከሞላ ጎደል ተስማምተዋል፡፡” [ገፅ፡ 1089]
~
ሙሐመድ ብኑ ዐሊ አሸውካኒ በ1250 ሂ. የሞቱ ታላቅ የመናዊ ዓሊም ናቸው፡፡ በሰፊው የሚታወቁ ስለሆኑ እሳቸውን በማስተዋወቅ ረጅሙን ፅሑፌን ይበልጥ ማስረዘም አልሻም፡፡ ሸውካኒ መውሊድ ላይ እጅግ የሰላ ትችት ሰንዝረዋል፡፡ ዛሬ በተደጋጋሚ ከምንሰማቸው መውሊድ ተኮር ጥያቄዎች ውስጥ የተወሰኑትን በመምዘዝ በሸውካኒ ንግግር ምላሽ እሰጣለሁ፡፡ ሙሉ ንግግራቸውን መመልከት የፈለገ ሰው “አልፈትሑ ረባኒ ሚን ፈታዋ አልኢማሚ ሸውካኒ” በተሰኘው የፈትዋ መድብላቸው ውስጥ ሁለተኛውን ጥራዝ ከገፅ 1087-1101 ድረስ መመልከት ይችላል፡፡ (ፅሑፉ ስለ ረዘመ ዐረብኛውን ማካተት አልቻልኩም፡፡)
1. መውሊድ የሸሪዐ መነሻ አለውን?
ሸውካኒ፡- “እስካሁን ድረስ ከቁርኣንም፣ ከሱናም፣ ከኢጅማዕም፣ ከቂያስም (ንፅፅራዊ ምልከታም) መሰረት እንዳለው የሚያመላክት መረጃ አላገኘሁለትም፡፡” [ገፅ፡ 2/1087]
2. መውሊድን ሰለፎች ያውቁታል?
ሸውካኒ፡- “እንዲያውም ከዘመናት ሁሉ ምርጡ በሆነው (የሶሐቦች) ዘመንም፣ ከነሱ ቀጥሎ በነበሩትም፣ ቀጥሎ በነበሩትም (ዘመን) እንዳልነበር ሙስሊሞች ወጥ አቋም ይዘዋል (ኢጅማዕ አድርገዋል፡፡)” [ገፅ፡ 2/1087]
3. ቢድዐ በመሆኑ ላይ ልዩነት አለ?
ሸውካኒ፡- “ቢድዐ በመሆኑ ላይ ከሙስሊሞች አንድ እንኳን የተቃወመ የለም፡፡” [ገፅ፡ 2/1088] “ይሄ ነገር ቢድዐ በመሆኑ ላይ ከሁሉም ሙስሊሞች ኢጅማዕ እንዳለበት አረጋግጠንልሃል፡፡” [ገፅ፡ 2/1091]
4. መውሊድን በሚደግፉ መሻይኾች ማስፈራራት ያዋጣል?
ሸውካኒ፡- “በምርጡ ነብይ ﷺ የማያሻማ ምስክርነት ቢድዐ ሁሉ ጥመት እንደሆነ ተነግሮ ሳለ የመውሊድን ቢድዐ መሆን ካመነ በኋላ ይፈቀዳል የሚል ሰው የተናገረው ከንፁሁ ሸሪዐ ጋር የሚፃረር ንግግር ነው፡፡ ያለ አንድ ተጨባጭ እውቀታዊ መነሻ ቢድዐን ወደተለያዩ ክፍሎች ለከፈለ ሰው በጭፍን ከመከተል ያለፈ ነገርም የለውም፡፡ የትኛውንም አቋም ይቻላል የሚልን ሰው ይህንን ቢድዐ በተለየ የሚመለከት ማስረጃ ካቀረበ በኋላ እንጂ አንቀበለውም፡፡ … እንጂ ‘እከሌ እንዲህ አለ’፣ ‘እከሌ እንዲህ አይነት ኪታብ አዘጋጅቷል’ የሚል ባዶ ንግግር ፋይዳ የለውም፡፡ ሐቅ ከየትኛውም አካል ይበልጣልና፡፡” [ገፅ፡ 2/1088 - 1089]
“ከነሱ (ከፈቃጆቹ) ውስጥ ቢድዐነቱን አምኖ መጥፎ ነገር ካልተቆራኘው በሚል መስፈርት የፈቀደው አለ፡፡ ምንም ማስረጃ ግን አላመጣም፡፡” [ገፅ፡ 2/1094]
ኢብኑ ሐጀር እንዳደረገው የዓሹራን ፆም ማስረጃ ማድረግ፣ ወይም ሲዩጢ እንዳደረገው ከነብይነት በኋላ ለራሳቸው ዐቂቃ ማውጣታቸውን መመርኮዝ ቢድዐን የማፅናት ፍቅር እንዲህ አይነት ነገር ላይ እንደሚጥል ከሚያሳዩ አስገራሚ ነገሮች ውስጥ ነው፡፡ [ገፅ፡ 1095]
5. መውሊድ የብዙሃን ሙስሊሞች ድጋፍ ነበረውን?
ሸውካኒ፡- “በሰዎች ንግግሮች ላይ የምንመረኮዝ ከሆንና የእንቶ ፈንቶ ጅራቶችን የምንጨብጥ ከሆንን መታወቅ ያለበት ነገር ቢኖር ‘ይፈቀዳል’ ባዮቹ ከሙስሊሞች በአቋም ያፈነገጡ ናቸው፡፡ …” [ገፅ፡ 2/1087-1089]
“ሲጨመቅ የመውሊድ ፈቃጆች ከከልካዮቹ አንፃር ሲታዩ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ለዚያውም እነሱም ቢሆኑ ምግብ ለማብላትና ለዚክር ካልሆነ በስተቀር እንደማይቻል ተስማምተዋል፡፡” [ገፅ፡ 1095–1099]
(አስተውሉ! ይህ እንግዲህ በሸውካኒ ዘመን ነው፡፡ የሞቱት በ1250 ሂ. ሲሆን ሁለት መቶ አመት ሊሞላቸው ጥቂት ነው የቀራቸው፡፡ ሱፊያ ደፋር ነውና የዛሬን የመውሊድ ጨፋሪዎች በመመልከት ሸውካኒን “ውሸታም ነው” እንዳይሉ እሰጋለሁ፡፡)
6. መውሊድ እንዴት ተስፋፋ?
ሸውካኒ፡- “ግና ቢድዐን በማፅናትም ሆነ በማጥፋት ላይ ንጉሳን ተፅእኖ አላቸው፡፡ ይህንን ቢድዐ (በሱኒው ዓለም ውስጥ) የፈጠረው ያ ንጉስ (ሙዞፈር) ሲሆን ኢብኑ ዲሕያ ደግሞ ‘አተንዊር ፊ መውሊዲል በሺር ነዚር’ የተሰኘ ኪታብ በማዘጋጀት አግዞታል፡፡ ሰውየው በዘገባ እውቀት ላይ የጠለቀ ከመሆኑም ጋር በዚህ ኪታቡ ግን ግልፅ ማስረጃ አላቀረበም፡፡ ለዚህ ስራው - ኢብኑ ኸሊካን እንደጠቀሱት - አንድ ሺህ ዲናር በንጉሱ መሸለሙ ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ የዱንያ ፍቅር ከዚህም በላይ ያደርሳል፡፡” [ገፅ፡ 2/1091]
“የቢድዐ ስርጭት ከእሳት ስርጭት የፈጠነ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ መውሊድ፡፡ ምክንያቱም የመሃይማን ነፍሶች ጥግ የደረሰ መናፈቅን ይናፍቁታልና፡፡ በተለይ ደግሞ ከምሁራን፣ ከክቡራንና መሪዎች በርከት ያለ ሰው ከተካፈለበት በኋላ ይሄ ቢድዐ ወሳኝ ከሆኑ ሱናዎች ይመስላቸዋል፡፡ … እንደ መውሊድና አምሳያዎቹ ያሉ ለሐራም ነገሮች የሚያመቻቹ የጥፋት መዳረሻዎች መሃይሞች ፈጥነው እንደሚገቡባቸው አያጠራጥርም፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ በዒልም፣ በክብርና በስልጣን ዝና ያለው ሰው መካፈል ሲታከልበት ሐራም ነገሮችን እንደ ፈጣሪ ትእዛዛት ሲፈፅሙ፣ በድንቁርናና በጥመት ሸለቆች ውስጥ ገብተው ሲዘባርቁ፣ “የተከበሩ እከሌ፣ እከሌ፣ እከሌ፣… ተገኝተዋል” እያሉ ከተቃውሞ ሲያመልጡ የባሰ ይሆናል፡፡
መሃይሙ ህዝብ ይቅርና አንዱ በዒልም ፍለጋ ላይ ገኖ የወጣ ሰው አንዳንድ የኢጅቲሃድ እውቀቶችን ለመማር ከፊቴ ተቀምጦ ነበር፡፡ በዚህ ወር ከተከናወኑ መውሊዶች ውስጥ በአንዱ አዳር ላይ እንደተካፈለ ሲነግረኝ ተቃወምኩት፡፡ አንገሸገሸኝ፡፡ በዚህን ጊዜ ‘ሰዪዲ እከሌ፣ እከሌ፣ እከሌ፣… ተካፍለዋልኮ’ አለኝ፡፡ በነዚህ ታዋቂ ሰዎች ፊት የነበረውን አፈፃፀም ስጠይቀው እንዲህ አለኝ፡-
‘እነዚያ ታዋቂ ሰዎች እየዘፈኑና እያዳመጡ መንዙማውን አንድ ዱርየ አነበበ፡፡ ከዚያም አንዱ ልክ ከእስር የተነሳ ይመስል አፈፍ ብሎ ተነስቶ “መርሐባ ያ ኑረ ዐይኒ፣ መርሐባ” (እንኳን መጣህ ያይኔ ብርሃን እንኳን መጣህ!) ሲል ታዳሚው በመላ ታዋቂዎቹን ጨምሮ ተከትለውት ቆሙ፡፡ እነሱ በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ ቆሞ ማጓራት ያዘ፡፡ አንዱ ታዳሚ ደክሞት ቢቀመጥ ከታዋቂዎቹ ውስጥ አንዱ ንዴቱ ከፊቱ ላይ እየታየ ‘ተነስ! ጨዋታኮ አይደለም!’ ብሎ ጮኸበት፡፡ ቃል በቃል! የአላህ መልእክተኛ ﷺ በዚያች ሰዓት ከነሱ ዘንድ እንደደረሱ ጭራሽ አይጠራጠሩም፡፡ ከዚያም ተጨባበጡ፡፡ ከመሀይማን ከፊሎቹ በእጆቻቸው ሽቶ በመያዝ በፍጥነት ቀቡ፣ ተቀቡ፡፡ ልክ የሳቸውን ﷺ መገኘት ለመጠቀም፡፡’
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን! የዲን ክብር የት ገባ?! ይህም ከጠፋ አይናፋርነት፣ ግብረ ገብነት፣ ህሊና የት ገባ?” [ገፅ፡ 2/1089-91]
7. መውሊድን የነብዩ ﷺ ቤተሰቦች ይደግፉታል?
መውሊድን የሚያከብሩ ሰዎች “ከኛ በላይ ነብዩን ﷺ የሚወድ ላሳር!” የሚሉ ናቸው፡፡ እውነት ለመናገር የነብዩ ﷺ ዘሮች ሙእሚኖች ከሆኑ ለነብዩ ﷺ ያላቸው ፍቅር ልዩ ነው፡፡ መውሊዱ የፍቅር መገለጫ ቢሆን ኖሮ ከማንም ቀድመው ባከበሩት ነበር፡፡ ግን ከነሱ የተገኘው መውሊድን ማክበር፣ ማስከበር፣ ለሱ ሽንጥን ገትሮ መሟገት ነውን?
ሸውካኒ፡- “ከነብዩ ﷺ ንፁሕ ቤተሰብም ይሁን ከተከታዮቻቸው ይህ ነገር እንደሚፈቀድ የተናገረ አንድም ፊደል አላገኘንም፡፡ እንዲያውም ይህቺ ቢድዐ ከተከሰተች ጀምሮ ወደ ጥፋቶች ከሚያሻግሩ አስቀያሚ መዳረሻዎች አንዷ እንደሆነች ንግግሮቻቸው ከሞላ ጎደል ተስማምተዋል፡፡” [ገፅ፡ 1089]
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
“ከነብዩ ﷺ ቤተሰቦች እና ከተከታዮቻቸው ውስጥ ‘መውሊድ ይፈቀዳል’ ያለ አንድ እንኳን እንደሌለ ከተገለፀልህ ከነሱ ውጭ ያሉትን አቋም ልታውቅ ከፈለግክ ከሁሉም ሙስሊሞች ዘንድ ቢድዐ በመሆኑ ላይ ኢጅማዕ እንዳለ አረጋግጠንልሃል እንላለን፡፡” [ገፅ፡ 1091]
8. መውሊድ ውስጥ ሺርክ ወይም ሌላ ጥፋቶች ከሌሉበትስ ይፈቀዳል?
ሸውካኒ፡- “ ‘መውሊዱ ላይ ለምግብ መሰባሰብና ዚክር ብቻ ከሆነ ይፈቀዳል፣ አብረውት የሚያጅቡት ነገሮች ክልክል መሆናቸው ክልክልነቱን አያስይዝም’ የሚሉ ሰዎች ማመሀኛ ፉርሽነቱ ከዚህ ላይ ግልፅ ይሆንልሀል፡፡ ምክንያቱም እኛ እራስህ እንዳመንከው መውሊድ ቢድዐ ከመሆኑ ጋር በልምድ ከብዙ መጥፎ ነገሮች ጋር የተቆራኘና ለብዙ ጥፋቶች መዳረሻ ሆኗል እንላለንና፡፡ ደግሞም ከምግብና ከዚክር ውጭ ያሉ ነገሮችን የማያካትቱ መውሊዶችን ማግኘት ከቀይ ድኝ የበለጠ ፈታኝ ነው፡፡” [ገፅ፡ 2/1090-1091]
“የመውሊድ ፈቃጆች ከከልካዮቹ ጋር ሲነፃፀሩ ጥቂቶች ከመሆናቸው ጋር ለምግብና ለዚክር ብቻ በሚል መስፈርት ካልሆነ በስተቀር እንደማይቻል ተስማምተዋል፡፡ ለብዙ ጥፋቶች መዳረሻ እንደሆነ ደግሞ ይሄው አሳውቀንሃል፡፡ ይህን ከግምት በማስገባት ላይ አንድም አይፃረርም፡፡ ዛሬ የሚከሰተው የዚህ አይነቱ (ጥፋቱ የበዛበት) መውሊድ ግን በወጥ ስምምነት የተከለከለ ነው፡፡” [ገፅ፡ 2/1098-1099]
“ወደ ጥፋት የሚያደርሱ መንገዶችን መዝጋትና ወደማይፈቀድ ነገር መንጠላጠያ ገመዶችን መቁረጥ ብዙሃን ምሁራን እርግጠኛ ከሆኑባቸው ወሳኝ ሸሪዐዊ መርሆዎች ውስጥ ነው፡፡ አንተ እራስህ እንጥፍጣፊ ሚዛናዊነት ቀርቶህ ከሆነ ይህንን ሐቅ አትክድም፡፡” [ገፅ፡ 2/1091]
9. መውሊድ የልዩነት መንስኤ ነውን?
ሸውካኒ፡- “ደግሞም ይሄ መውሊድ ከተከሰተ በኋላ ውዝግቡ ተጧጡፏል፡፡ በዚህም ላይ የሚፃፉት ኪታቦች ከከልካዩም ከፈቃጁም በዝተዋል፡፡” [ገፅ፡ 2/1091]
10. መውሊድ ውስጥ አስቀያሚ ጥፋቶች ከኖሩበትስ?
ሸውካኒ፡- “ሀሳቡ ሲጨመቅ የመውሊድ ፈቃጆች ከከልካዮቹ አንፃር ሲታዩ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ለዚያውም እነሱም ቢሆኑ ምግብ ለማብላትና ለዚክር ካልሆነ በስተቀር እንደማይቻል ተስማምተዋል፡፡ ለጥፋቶች መዳረሻ እንደሆነ ደግሞ በርግጥም አሳውቀንሃል፡፡ ከዚህ አንፃር ሲታይ አንድም የሚወዛገብ የለም፡፡ የዚህ አይነቱ ዛሬ እየተከሰተ ያለው መውሊድ በዑለማእ ስምምነት ክልክል ነው፡፡ ርእሱ የፈቃጆቹን ንግግሮች እያቀረቡ ዘለግ ባለ መልኩ መመለስ የሚጠይቅ ቢሆንም ለጊዜው እዚህ ላይ ይበቃናል፡፡” ከዚያም በሙታን ላይ የሚፈፀመውን ሺርክና የጣኦት አምልኮ ጠቅሰው በጥብቅ ከኮነኑ በኋላ “እኛ ማስጠንቀቅና ማድረስ እንጂ ሌላ አቅም የለንም፡፡ ይህንን ይሄው አድርገናል፡፡ አላህ ሆይ! ለዲንህ ተቆጣ! ከነዚህ ቀብር አምላኪ ሸይጧኖች ቆሻሻም አፅዳው፡፡ ከነዚህ የጠንካራውን እምነት ንፅህና ካጠለሹ ቆሻሻዎችም አሳርፈን፡፡” [ገፅ፡ 1095–1101]
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 25/2012)
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
8. መውሊድ ውስጥ ሺርክ ወይም ሌላ ጥፋቶች ከሌሉበትስ ይፈቀዳል?
ሸውካኒ፡- “ ‘መውሊዱ ላይ ለምግብ መሰባሰብና ዚክር ብቻ ከሆነ ይፈቀዳል፣ አብረውት የሚያጅቡት ነገሮች ክልክል መሆናቸው ክልክልነቱን አያስይዝም’ የሚሉ ሰዎች ማመሀኛ ፉርሽነቱ ከዚህ ላይ ግልፅ ይሆንልሀል፡፡ ምክንያቱም እኛ እራስህ እንዳመንከው መውሊድ ቢድዐ ከመሆኑ ጋር በልምድ ከብዙ መጥፎ ነገሮች ጋር የተቆራኘና ለብዙ ጥፋቶች መዳረሻ ሆኗል እንላለንና፡፡ ደግሞም ከምግብና ከዚክር ውጭ ያሉ ነገሮችን የማያካትቱ መውሊዶችን ማግኘት ከቀይ ድኝ የበለጠ ፈታኝ ነው፡፡” [ገፅ፡ 2/1090-1091]
“የመውሊድ ፈቃጆች ከከልካዮቹ ጋር ሲነፃፀሩ ጥቂቶች ከመሆናቸው ጋር ለምግብና ለዚክር ብቻ በሚል መስፈርት ካልሆነ በስተቀር እንደማይቻል ተስማምተዋል፡፡ ለብዙ ጥፋቶች መዳረሻ እንደሆነ ደግሞ ይሄው አሳውቀንሃል፡፡ ይህን ከግምት በማስገባት ላይ አንድም አይፃረርም፡፡ ዛሬ የሚከሰተው የዚህ አይነቱ (ጥፋቱ የበዛበት) መውሊድ ግን በወጥ ስምምነት የተከለከለ ነው፡፡” [ገፅ፡ 2/1098-1099]
“ወደ ጥፋት የሚያደርሱ መንገዶችን መዝጋትና ወደማይፈቀድ ነገር መንጠላጠያ ገመዶችን መቁረጥ ብዙሃን ምሁራን እርግጠኛ ከሆኑባቸው ወሳኝ ሸሪዐዊ መርሆዎች ውስጥ ነው፡፡ አንተ እራስህ እንጥፍጣፊ ሚዛናዊነት ቀርቶህ ከሆነ ይህንን ሐቅ አትክድም፡፡” [ገፅ፡ 2/1091]
9. መውሊድ የልዩነት መንስኤ ነውን?
ሸውካኒ፡- “ደግሞም ይሄ መውሊድ ከተከሰተ በኋላ ውዝግቡ ተጧጡፏል፡፡ በዚህም ላይ የሚፃፉት ኪታቦች ከከልካዩም ከፈቃጁም በዝተዋል፡፡” [ገፅ፡ 2/1091]
10. መውሊድ ውስጥ አስቀያሚ ጥፋቶች ከኖሩበትስ?
ሸውካኒ፡- “ሀሳቡ ሲጨመቅ የመውሊድ ፈቃጆች ከከልካዮቹ አንፃር ሲታዩ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ለዚያውም እነሱም ቢሆኑ ምግብ ለማብላትና ለዚክር ካልሆነ በስተቀር እንደማይቻል ተስማምተዋል፡፡ ለጥፋቶች መዳረሻ እንደሆነ ደግሞ በርግጥም አሳውቀንሃል፡፡ ከዚህ አንፃር ሲታይ አንድም የሚወዛገብ የለም፡፡ የዚህ አይነቱ ዛሬ እየተከሰተ ያለው መውሊድ በዑለማእ ስምምነት ክልክል ነው፡፡ ርእሱ የፈቃጆቹን ንግግሮች እያቀረቡ ዘለግ ባለ መልኩ መመለስ የሚጠይቅ ቢሆንም ለጊዜው እዚህ ላይ ይበቃናል፡፡” ከዚያም በሙታን ላይ የሚፈፀመውን ሺርክና የጣኦት አምልኮ ጠቅሰው በጥብቅ ከኮነኑ በኋላ “እኛ ማስጠንቀቅና ማድረስ እንጂ ሌላ አቅም የለንም፡፡ ይህንን ይሄው አድርገናል፡፡ አላህ ሆይ! ለዲንህ ተቆጣ! ከነዚህ ቀብር አምላኪ ሸይጧኖች ቆሻሻም አፅዳው፡፡ ከነዚህ የጠንካራውን እምነት ንፅህና ካጠለሹ ቆሻሻዎችም አሳርፈን፡፡” [ገፅ፡ 1095–1101]
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 25/2012)
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ለዐረብ ሀገር ወንድምና እህቶች
~
① ከሁሉም በፊት ለዲናችሁ ቅድሚያ ስጡ። ከተውሒድ ጀምራችሁ ግንዛቤያችሁን በተለያዩ መንገዶች አስፉ። ለአላህ ምስጋና ይግባውና በዚህ በኩል ብዙ ወንድሞችና እህቶች ዘንድ ጥሩ ተነሳሽነት ይታያል።
② ለአሰሪዎቻችሁ ታማኞች ሁኑ። የሰው ሀላፊነት እስከተቀበላችሁ ድረስ አላህን ፈርታችሁ ሀላፊነታችሁን ባግባቡ ተወጡ። በሰዐትም፣ በስራም፣ በገንዘብም፣ በክብርም፣ በልጆችም የምትታመኑ ሁኑ። አማናን መወጣት ትልቅ ሃላፊነት ነው።
③ በተቻላችሁ ከአላስፈላጊ የወንድና የሴት ቅልቅል ተጠንቀቁ። በጋራ የኪራይ ቤቶች ሊፈፀሙ ከሚችሉ አደጋዎች እራሳችሁን ጠብቁ።
④ እርስ በርስ ተዛዘኑ። ስራ ለሌለው ስራ በመፈለግ፣ ለተቸገረው በብድር ወይም እራስን በማይጎዳ መዋጮ ተጋገዙ።
⑤ ከወንጀለኞች ራቁ። ዐረብ ሀገር በርካታ ኢትዮጵያውያን በወንጀል ስራ ላይ መሰማራታቸው የሚታወቅ ነው። በነሱ ሳቢያ ኢትዮጵያውያን ባጠቃላይ በተደጋጋሚ ስማቸው ይጠፋል። የሚገርመው ብዙ ለነዚህ ወንጀለኞች ሽፋን የሚሰጡ ኢትዮጵያውያን መኖራቸው ነው። በነሱ ጥፋት አብራችሁ እንዳትጎዱ ተጠንቀቁ። እንዲያውም ለሌላ የሚተርፍ የተረጋገጠ ወንጀል ካያችሁ ለሚመለከተው አካል ጠቁሙ። ይሄ ለዲናችሁም ለገፅታችሁም ዋጋ አለው።
⑥ ቤተሰቦቻችሁን አትርሱ። ወላጅ ወላጅ ስለሆነ ብቻ ከባድ ሐቅ እንዳለው እሙን ነው። ከዚያም ባለፈ ስንት ፍዳቸውን አይተው አሳድገዋል። ዐረብ ሀገር ትሄዱ ዘንድ የተቸገሩላችሁም ብዙ ናቸው። እነዚህን ታሳቢ በማድረግ ወላጆቻችሁን አትርሱ። በዚያ ላይ አንዳንዶቻችሁ ወደ ወላጆቻችሁ ልጅ የላካችሁ ትኖራላችሁ። በዚህን ጊዜ ሐቁ ድርብርብ ነውና ኣኺራችሁን እንዳታጨልሙ ተጠንቀቁ።
⑦ እራሳችሁን አትርሱ። የወጣችሁት እንጀራ ፍለጋ ነው። ከፋም ደላ የሰው ሀገር የሰው ነው። ህልማችሁ ቋጥሮ ወደ ሀገር ለመመለስ እንጂ በልቶ ለመውዛት፣ ለብሶ ለመድመቅ አይደለም። ለዚህ ደግሞ ብልጥ መሆን ያስፈልጋል። መስራቱን ቻሉበት። መያዙንም ቻሉበት። ወጭ ቀንሱ። ለቤተሰብ ስትልኩም አቅማችሁንም፣ ኑሯቸውንም፣ ሁኔታቸውንም እያገናዘባችሁ ይሁን። ለጎረምሳ ጫት መቃሚያና መንሸራሸሪያ አትላኩ። በዚህ ወንድሞቻችሁን ታበላሻላችሁ እንጂ አትጠቅሟቸውም። ገንዘባችሁንም አጥታችሁ ወንጀለኛም ትሆናላችሁ። ባጭሩ የምትሰሩትን ገንዘብ ቁም ነገር ላይ ለማዋል ተጣጣሩ። ባዶ እጃችሁን ላለመግባት በተቻላችሁ ተጠንቀቁ። ችግር መጥፎ ነው። ቤተሰብ እንኳን እንዲገፋችሁ ያደርጋል። አገራችን ለባዶ እጅ ቀርቶ ለያዘም እየከበደ ነው።
⑧ እቅድ ይኑራችሁ። ለቆይታችሁ ገደብ አስቀምጡለት። በግምት አትኑሩ። ሁለት አመት ሰራርቼ አገሬ እገባለሁ ብለው ሃያ አመት የኖሩ አሉ። ከአላማ ካልተወጣ ክፋት አልነበረውም። እየባከኑ ሲሆን ግን ያሳዝናል። "ምን ይዤ ልግባ?" እያሉ እየተብከነከኑ መኖር ይጎዳል። ስለዚህ ገደብ ያለው እቅድ ይኑራችሁ። ለእቅዳችሁም በትጋት አስቡ፣ በትጋት ስሩ። መገናኘታችሁ እቅዳችሁን የሚያሰናክል፣ ለትርጉም የለሽ ወጭ የሚዳርግ ከሆነ ተራራቁ።
⑨ ሴቶች ሆይ! መንገደኛ አታግቡ። እስኪ አሁን ሂንዲ፣ ፓኪስታኒ፣ ባንጋሊ ማግባት ምን ይባላል? እንዲህ አይነቱ ትዳር ዘላቂ የመሆን እድሉ እጅግ የጠበበ ነው። ልጅ ከመጣም ከነ ጭራሹ አባቱ ጋር አይኖርም። ስለዚህ ለራስም ለልጅም ፈተና ነው።
(10) ለኸይር ስራ እጃችሁን ስትዘረጉ ጥንቁቅ ሁኑ። ኸይር አትስሩ አይባልም። ግን በትክክል ለታለመለት ግብ የሚደርስ መሆኑን ቢያንስ ሚዛን የሚደፋ ግምት ያዙ።
(11) ለትዳር ክብር ይኑራችሁ። ትዳርን መስፈርት በማያሟላ በተጨመላለቀ መልኩ ሳይሆን በሥርዓት ፈፅሙ። አትበዳደሉ። ኣኺራችሁን በማይጎዳ መልኩ በስርኣት ኑሩ። ለጋብቻ የተጋነነ ወጭ አታውጡ። ከሰሞንኛ ሆይሆይታ ይልቅ ለዘላቂው ትዳራችሁ ቅድሚያ ስጡ። መለያየት ግድ ካለም ባግባቡ ይሁን።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 4፣ 2013)
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
① ከሁሉም በፊት ለዲናችሁ ቅድሚያ ስጡ። ከተውሒድ ጀምራችሁ ግንዛቤያችሁን በተለያዩ መንገዶች አስፉ። ለአላህ ምስጋና ይግባውና በዚህ በኩል ብዙ ወንድሞችና እህቶች ዘንድ ጥሩ ተነሳሽነት ይታያል።
② ለአሰሪዎቻችሁ ታማኞች ሁኑ። የሰው ሀላፊነት እስከተቀበላችሁ ድረስ አላህን ፈርታችሁ ሀላፊነታችሁን ባግባቡ ተወጡ። በሰዐትም፣ በስራም፣ በገንዘብም፣ በክብርም፣ በልጆችም የምትታመኑ ሁኑ። አማናን መወጣት ትልቅ ሃላፊነት ነው።
③ በተቻላችሁ ከአላስፈላጊ የወንድና የሴት ቅልቅል ተጠንቀቁ። በጋራ የኪራይ ቤቶች ሊፈፀሙ ከሚችሉ አደጋዎች እራሳችሁን ጠብቁ።
④ እርስ በርስ ተዛዘኑ። ስራ ለሌለው ስራ በመፈለግ፣ ለተቸገረው በብድር ወይም እራስን በማይጎዳ መዋጮ ተጋገዙ።
⑤ ከወንጀለኞች ራቁ። ዐረብ ሀገር በርካታ ኢትዮጵያውያን በወንጀል ስራ ላይ መሰማራታቸው የሚታወቅ ነው። በነሱ ሳቢያ ኢትዮጵያውያን ባጠቃላይ በተደጋጋሚ ስማቸው ይጠፋል። የሚገርመው ብዙ ለነዚህ ወንጀለኞች ሽፋን የሚሰጡ ኢትዮጵያውያን መኖራቸው ነው። በነሱ ጥፋት አብራችሁ እንዳትጎዱ ተጠንቀቁ። እንዲያውም ለሌላ የሚተርፍ የተረጋገጠ ወንጀል ካያችሁ ለሚመለከተው አካል ጠቁሙ። ይሄ ለዲናችሁም ለገፅታችሁም ዋጋ አለው።
⑥ ቤተሰቦቻችሁን አትርሱ። ወላጅ ወላጅ ስለሆነ ብቻ ከባድ ሐቅ እንዳለው እሙን ነው። ከዚያም ባለፈ ስንት ፍዳቸውን አይተው አሳድገዋል። ዐረብ ሀገር ትሄዱ ዘንድ የተቸገሩላችሁም ብዙ ናቸው። እነዚህን ታሳቢ በማድረግ ወላጆቻችሁን አትርሱ። በዚያ ላይ አንዳንዶቻችሁ ወደ ወላጆቻችሁ ልጅ የላካችሁ ትኖራላችሁ። በዚህን ጊዜ ሐቁ ድርብርብ ነውና ኣኺራችሁን እንዳታጨልሙ ተጠንቀቁ።
⑦ እራሳችሁን አትርሱ። የወጣችሁት እንጀራ ፍለጋ ነው። ከፋም ደላ የሰው ሀገር የሰው ነው። ህልማችሁ ቋጥሮ ወደ ሀገር ለመመለስ እንጂ በልቶ ለመውዛት፣ ለብሶ ለመድመቅ አይደለም። ለዚህ ደግሞ ብልጥ መሆን ያስፈልጋል። መስራቱን ቻሉበት። መያዙንም ቻሉበት። ወጭ ቀንሱ። ለቤተሰብ ስትልኩም አቅማችሁንም፣ ኑሯቸውንም፣ ሁኔታቸውንም እያገናዘባችሁ ይሁን። ለጎረምሳ ጫት መቃሚያና መንሸራሸሪያ አትላኩ። በዚህ ወንድሞቻችሁን ታበላሻላችሁ እንጂ አትጠቅሟቸውም። ገንዘባችሁንም አጥታችሁ ወንጀለኛም ትሆናላችሁ። ባጭሩ የምትሰሩትን ገንዘብ ቁም ነገር ላይ ለማዋል ተጣጣሩ። ባዶ እጃችሁን ላለመግባት በተቻላችሁ ተጠንቀቁ። ችግር መጥፎ ነው። ቤተሰብ እንኳን እንዲገፋችሁ ያደርጋል። አገራችን ለባዶ እጅ ቀርቶ ለያዘም እየከበደ ነው።
⑧ እቅድ ይኑራችሁ። ለቆይታችሁ ገደብ አስቀምጡለት። በግምት አትኑሩ። ሁለት አመት ሰራርቼ አገሬ እገባለሁ ብለው ሃያ አመት የኖሩ አሉ። ከአላማ ካልተወጣ ክፋት አልነበረውም። እየባከኑ ሲሆን ግን ያሳዝናል። "ምን ይዤ ልግባ?" እያሉ እየተብከነከኑ መኖር ይጎዳል። ስለዚህ ገደብ ያለው እቅድ ይኑራችሁ። ለእቅዳችሁም በትጋት አስቡ፣ በትጋት ስሩ። መገናኘታችሁ እቅዳችሁን የሚያሰናክል፣ ለትርጉም የለሽ ወጭ የሚዳርግ ከሆነ ተራራቁ።
⑨ ሴቶች ሆይ! መንገደኛ አታግቡ። እስኪ አሁን ሂንዲ፣ ፓኪስታኒ፣ ባንጋሊ ማግባት ምን ይባላል? እንዲህ አይነቱ ትዳር ዘላቂ የመሆን እድሉ እጅግ የጠበበ ነው። ልጅ ከመጣም ከነ ጭራሹ አባቱ ጋር አይኖርም። ስለዚህ ለራስም ለልጅም ፈተና ነው።
(10) ለኸይር ስራ እጃችሁን ስትዘረጉ ጥንቁቅ ሁኑ። ኸይር አትስሩ አይባልም። ግን በትክክል ለታለመለት ግብ የሚደርስ መሆኑን ቢያንስ ሚዛን የሚደፋ ግምት ያዙ።
(11) ለትዳር ክብር ይኑራችሁ። ትዳርን መስፈርት በማያሟላ በተጨመላለቀ መልኩ ሳይሆን በሥርዓት ፈፅሙ። አትበዳደሉ። ኣኺራችሁን በማይጎዳ መልኩ በስርኣት ኑሩ። ለጋብቻ የተጋነነ ወጭ አታውጡ። ከሰሞንኛ ሆይሆይታ ይልቅ ለዘላቂው ትዳራችሁ ቅድሚያ ስጡ። መለያየት ግድ ካለም ባግባቡ ይሁን።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 4፣ 2013)
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
መቼም ቢሆን ከዒልም ፍለጋ ልንዘናጋ አይገባም። የትኛውም ቀናችን አነሰም በዛ የሆነ ነገር ልንሸምትበት ይገባል። በዚህ ሳምንት ምን ተምረናል? ምን አዳምጠናል? ምን አንብበናል? ለቀጣይስ ምን አስበናል? በዚህ ዓመት ስንት ኪታብ አየን? ለቀጣይስ ምን አሰብን? አነሰም በዛም ጊዜያችን ከዒልም ፍለጋ የተራቆተ ሊሆን አይገባም።
ጊዜ የለንም ብለን አንዘናጋ። እንደምንም ብለን ጊዜ እንስጥ። ተረጋግተን ተቀምጠን የምንከታተልበት ጊዜ ቢያጥረን ስራችንን እየሰራን ብዙ ደርሶችን፣ ደዕዋዎችን ማዳመጥ እንችላለን። በየቀኑ ከቤቱ ተነስቶ ስራ ቦታ የሚሄድ ሰው፣ ረጃጅም የወረፋ ሰልፍ ላይ የሚቆም ሰው፣ ... ፀጥታ ካለ ቁርአኑን መቅራት ይችላል። እሱ ባይመች ኪታብ ማንበብ፣ ዚክር ማድረግ፣ በኤርፎን ደርስ ማዳመጥ ይችላል። አንዴ ካስለመድነው ህይወታችን ጋር ይዋሃዳል። ቀላል የሚመስለን ጊዜ ብዙ ልንጠቀምበት እንችላለን።
ዋናው ነገር ውስጣችን ለመማር ዝግጁ ይሁን። የምር ካሰብንበት በየቀኑ የሆነ እውቀት መጨመር እንችላለን። ከልብ ካለቀሱ እምባ አይገድም።
ዐብዱላህ ኢብኑል ሙባረክ ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦
"አንድ ሰው እውቀትን ፍለጋ ላይ እስከሆነ ድረስ አዋቂ ከመሆን አይወገድም። እንዳወቀ ያሰበ እለት ያኔ አላዋቂ ሆኗል።" [አልሙጃለሳህ : 2/186]
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
ጊዜ የለንም ብለን አንዘናጋ። እንደምንም ብለን ጊዜ እንስጥ። ተረጋግተን ተቀምጠን የምንከታተልበት ጊዜ ቢያጥረን ስራችንን እየሰራን ብዙ ደርሶችን፣ ደዕዋዎችን ማዳመጥ እንችላለን። በየቀኑ ከቤቱ ተነስቶ ስራ ቦታ የሚሄድ ሰው፣ ረጃጅም የወረፋ ሰልፍ ላይ የሚቆም ሰው፣ ... ፀጥታ ካለ ቁርአኑን መቅራት ይችላል። እሱ ባይመች ኪታብ ማንበብ፣ ዚክር ማድረግ፣ በኤርፎን ደርስ ማዳመጥ ይችላል። አንዴ ካስለመድነው ህይወታችን ጋር ይዋሃዳል። ቀላል የሚመስለን ጊዜ ብዙ ልንጠቀምበት እንችላለን።
ዋናው ነገር ውስጣችን ለመማር ዝግጁ ይሁን። የምር ካሰብንበት በየቀኑ የሆነ እውቀት መጨመር እንችላለን። ከልብ ካለቀሱ እምባ አይገድም።
ዐብዱላህ ኢብኑል ሙባረክ ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦
"አንድ ሰው እውቀትን ፍለጋ ላይ እስከሆነ ድረስ አዋቂ ከመሆን አይወገድም። እንዳወቀ ያሰበ እለት ያኔ አላዋቂ ሆኗል።" [አልሙጃለሳህ : 2/186]
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
በባለ ትዳሮች መሀል የሚገጥም መጠራጠር
~
ባሏን በሐራም የምትጠራጠር ሴት፣ ወይም ሚስቱን በሐራም ግንኙነት የሚጠራጠር ወንድ ሲያጋጥም በቅድሚያ "አላህን ፍሩ! አትጠራጠሩ!" በማለት አፍ ለማስያዝ ከመሞከር በፊት ሁኔታውን ማየት ያስፈልጋል። ለጥርጣሬ የሚጋብዝ ተጨባጭ መነሻ አለ ወይ?
* ሰበብ ካለ "አትጠራጠሩ " ሳይሆን የሚባለው "ለጥርጣሬ የሚጋብዘውን ክፍተት አስተካክሉ" ነው መሆን ያለበት። ሰበብ ባለበት ሁኔታ በችኮላ "እንዴት ሲባል ልጃችንን ትጠረጥራታለህ?/ ትጠረጥሪዋለሽ?" የሚል የቤተሰብ መከላከያ ኋላ ራሳችንን ሊያሳፍረን ይችላልና በቅድሚያ ሚዛናዊ ሆነን እንመልከት። አዋዋል፣ አነጋገር፣ የስልክ አጠቃቀም፣ ... ላይ ችግሮች ካሉ ፈርጠም ብሎ ማስተካከል ወይም እንዲስተካከል መስራት ይገባል።
* ጥርጣሬው መሰረት የሌለው ቅጥ ያጣ የባህሪ ችግር ከሆነ ያኔ "አላህን ፍሩ! ከጥርጣሬ ራቁ" ብሎ መገሰፅ ይገባል። አጉል ጥርጣሬ ህይወትን ፈተና ያደርጋል። ቤትንም ያፈርሳል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
ባሏን በሐራም የምትጠራጠር ሴት፣ ወይም ሚስቱን በሐራም ግንኙነት የሚጠራጠር ወንድ ሲያጋጥም በቅድሚያ "አላህን ፍሩ! አትጠራጠሩ!" በማለት አፍ ለማስያዝ ከመሞከር በፊት ሁኔታውን ማየት ያስፈልጋል። ለጥርጣሬ የሚጋብዝ ተጨባጭ መነሻ አለ ወይ?
* ሰበብ ካለ "አትጠራጠሩ " ሳይሆን የሚባለው "ለጥርጣሬ የሚጋብዘውን ክፍተት አስተካክሉ" ነው መሆን ያለበት። ሰበብ ባለበት ሁኔታ በችኮላ "እንዴት ሲባል ልጃችንን ትጠረጥራታለህ?/ ትጠረጥሪዋለሽ?" የሚል የቤተሰብ መከላከያ ኋላ ራሳችንን ሊያሳፍረን ይችላልና በቅድሚያ ሚዛናዊ ሆነን እንመልከት። አዋዋል፣ አነጋገር፣ የስልክ አጠቃቀም፣ ... ላይ ችግሮች ካሉ ፈርጠም ብሎ ማስተካከል ወይም እንዲስተካከል መስራት ይገባል።
* ጥርጣሬው መሰረት የሌለው ቅጥ ያጣ የባህሪ ችግር ከሆነ ያኔ "አላህን ፍሩ! ከጥርጣሬ ራቁ" ብሎ መገሰፅ ይገባል። አጉል ጥርጣሬ ህይወትን ፈተና ያደርጋል። ቤትንም ያፈርሳል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
በአካላችን ላይ የተገጠሙ ምስክሮች!
~
ኸይርም ይሁን ሸር ዛሬ ስለምንሰራው ሁሉ ነገ በቂያማ ቀን የአካል ክፍሎቻችን ምስክሮች ናቸው። የማይዛነፍ፣ በጉቦ የማይታለፍ፣ በዘመድ፣ በትውውቅ የማይሸወድ የፍትህ ችሎት አለ ነገ። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
{ یَوۡمَ تَشۡهَدُ عَلَیۡهِمۡ أَلۡسِنَتُهُمۡ وَأَیۡدِیهِمۡ وَأَرۡجُلُهُم بِمَا كَانُوا۟ یَعۡمَلُونَ }
"በእነሱ ላይ ምላሶቻቸው፣ እጆቻቸውና እግሮቻቸውም ይሠሩት በነበሩት ነገር በሚመሰክሩባቸው ቀን (ከባድ ቅጣት አላቸው)።" [አንኑር: 24]
{ ٱلۡیَوۡمَ نَخۡتِمُ عَلَىٰۤ أَفۡوَ ٰهِهِمۡ وَتُكَلِّمُنَاۤ أَیۡدِیهِمۡ وَتَشۡهَدُ أَرۡجُلُهُم بِمَا كَانُوا۟ یَكۡسِبُونَ }
"ዛሬ በአፎቻቸው ላይ እናትምና እጆቻቸው ያነጋግሩናል። እግሮቻቸውም ይሠሩት በነበሩት ሁሉ ይመሰክራሉ።" [ያሲን፡ 65]
በዚያ ቀን አካሎቻችን ብቻ አይደሉም። ምድርም በላዩዋ ላይ የተፈፀመባትን ሁሉ ትናገራለች። ምን ይታወቃል? እጃችን ላይ የሚውለው የሞባይል ስልክም ይመሰክርልን ወይም ይመሰክርብን ይሆናል። ሸይኽ ዐብዱልዐዚዝ አልቡረዒይ - አላህ ይጠብቃቸውና - "የሞባይል ስልክ ለባለቤቱ በሰራው መልካም ወይም ክፉ ነገር ላይ በትንሣኤ ቀን ይመሰክራልን ወይ" ተብለው ተጠይቀው ነበር። ምላሻቸው እንዲህ የሚል ነው፦
"አላህ ያውቃል። ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ሌሎች ምስክሮች አሉ። ዓይን ይመሰክራል፣ ጆሮ ይመሰክራል፣ በስልኩ ላይ የተንቀሳቀሱ ጣቶች ይመሰክራሉ። ስለዚህ ምስክሮች ብዙ ናቸው።"
ለዚያ ቀን ዛሬ ነው መዘጋጀት። ዛሬ ነው መጠንቀቅ። ዛሬ ነው መሰነቅ። መቼስ ሁላችንም ወደዚያው ጉዞ ላይ ነው። እዚህ ሰፈር በብዛት የሚዘዋወር አንድ የሸይኽ ሙሐመድ ወሌ ረሒመሁላህ እንዲህ የሚል ስንኝ አለ፦
ሁሉም ይጓዛታል - ያቺን የሩቅ ጉዞ
የሌለው ባዶውን - ያለውን ስንቁን ይዞ።"
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
ኸይርም ይሁን ሸር ዛሬ ስለምንሰራው ሁሉ ነገ በቂያማ ቀን የአካል ክፍሎቻችን ምስክሮች ናቸው። የማይዛነፍ፣ በጉቦ የማይታለፍ፣ በዘመድ፣ በትውውቅ የማይሸወድ የፍትህ ችሎት አለ ነገ። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
{ یَوۡمَ تَشۡهَدُ عَلَیۡهِمۡ أَلۡسِنَتُهُمۡ وَأَیۡدِیهِمۡ وَأَرۡجُلُهُم بِمَا كَانُوا۟ یَعۡمَلُونَ }
"በእነሱ ላይ ምላሶቻቸው፣ እጆቻቸውና እግሮቻቸውም ይሠሩት በነበሩት ነገር በሚመሰክሩባቸው ቀን (ከባድ ቅጣት አላቸው)።" [አንኑር: 24]
{ ٱلۡیَوۡمَ نَخۡتِمُ عَلَىٰۤ أَفۡوَ ٰهِهِمۡ وَتُكَلِّمُنَاۤ أَیۡدِیهِمۡ وَتَشۡهَدُ أَرۡجُلُهُم بِمَا كَانُوا۟ یَكۡسِبُونَ }
"ዛሬ በአፎቻቸው ላይ እናትምና እጆቻቸው ያነጋግሩናል። እግሮቻቸውም ይሠሩት በነበሩት ሁሉ ይመሰክራሉ።" [ያሲን፡ 65]
በዚያ ቀን አካሎቻችን ብቻ አይደሉም። ምድርም በላዩዋ ላይ የተፈፀመባትን ሁሉ ትናገራለች። ምን ይታወቃል? እጃችን ላይ የሚውለው የሞባይል ስልክም ይመሰክርልን ወይም ይመሰክርብን ይሆናል። ሸይኽ ዐብዱልዐዚዝ አልቡረዒይ - አላህ ይጠብቃቸውና - "የሞባይል ስልክ ለባለቤቱ በሰራው መልካም ወይም ክፉ ነገር ላይ በትንሣኤ ቀን ይመሰክራልን ወይ" ተብለው ተጠይቀው ነበር። ምላሻቸው እንዲህ የሚል ነው፦
"አላህ ያውቃል። ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ሌሎች ምስክሮች አሉ። ዓይን ይመሰክራል፣ ጆሮ ይመሰክራል፣ በስልኩ ላይ የተንቀሳቀሱ ጣቶች ይመሰክራሉ። ስለዚህ ምስክሮች ብዙ ናቸው።"
ለዚያ ቀን ዛሬ ነው መዘጋጀት። ዛሬ ነው መጠንቀቅ። ዛሬ ነው መሰነቅ። መቼስ ሁላችንም ወደዚያው ጉዞ ላይ ነው። እዚህ ሰፈር በብዛት የሚዘዋወር አንድ የሸይኽ ሙሐመድ ወሌ ረሒመሁላህ እንዲህ የሚል ስንኝ አለ፦
ሁሉም ይጓዛታል - ያቺን የሩቅ ጉዞ
የሌለው ባዶውን - ያለውን ስንቁን ይዞ።"
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
لَا تُطْرُونِي كَمَا أَطْرَتِ النَّصَارَى ابْنَ مَرْيَمَ، فَإِنَّمَا أَنَا عَبْدُهُ، فَقُولُوا : عَبْدُ اللَّهِ وَرَسُولُهُ "
"ክርስቲያኖች የመርየምን ልጅ (ዒሳን) እንዳጋነኑ እኔን አታጋንኑ። እኔ የአላህ ባሪያው ነኝና፣ 'የአላህ ባሪያውና መልዕክተኛው' በሉኝ።" [አልቡኻሪይ ፡ 3445]
በሌላም ሐዲሥ እንዲህ ብለዋል፦
مَنْ تَشَبَّهَ بِقَوْمٍ فَهُوَ مِنْهُمْ
"አንድን ሕዝብ የተመሳሰለ (የተከተለ) ከእነርሱ ነው (እንደነርሱ ይቆጠራል)።" [አቡ ዳውድ ፡ 4031]
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
لَا تُطْرُونِي كَمَا أَطْرَتِ النَّصَارَى ابْنَ مَرْيَمَ، فَإِنَّمَا أَنَا عَبْدُهُ، فَقُولُوا : عَبْدُ اللَّهِ وَرَسُولُهُ "
"ክርስቲያኖች የመርየምን ልጅ (ዒሳን) እንዳጋነኑ እኔን አታጋንኑ። እኔ የአላህ ባሪያው ነኝና፣ 'የአላህ ባሪያውና መልዕክተኛው' በሉኝ።" [አልቡኻሪይ ፡ 3445]
በሌላም ሐዲሥ እንዲህ ብለዋል፦
مَنْ تَشَبَّهَ بِقَوْمٍ فَهُوَ مِنْهُمْ
"አንድን ሕዝብ የተመሳሰለ (የተከተለ) ከእነርሱ ነው (እንደነርሱ ይቆጠራል)።" [አቡ ዳውድ ፡ 4031]
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
መውሊድን የሚፈቅዱትም አይፈቅዱትም!
~
የመውሊድ ደጋፊዎች ለዚህ ቢድዐ የሚያጣቅሱት ትልቁ ማስረጃ እነ እከሌ ደግፈውታል እያሉ ዑለማዎችን ማጣቀስ ነው። ሐቂቃው ግን እነዚህ ዓሊሞች ዛሬ መውሊድ ላይ በሚታየው መልኩ የፈቀዱ አለመሆናቸው ነው። ይሄውና አይታችሁ ታዘቡ፡-
1. አተዝመንቲ (682 ሂ.?)፡-
“የመውሊድ ተግባር በመልካም ቀደምቶች የኢስላም ቀዳሚ ዘመን አልተከሰተም።” “መውሊድ …ፈፃሚው ደጋጎችን መሰብሰብ፣ በነብዩ ላይ ሶለዋት ማውረድ፣ ድሆችንና ምስኪኖችን ምግብ ማብላትን ካሰበ መልካም ቢድዐ ነው። በዚህ ልክና በዚህ ሸርጥ (መስፈርት) ከሆነ ይመነዳበታል። እንጂ ቂላቂሎችን መሰብሰብ፣ ዜማ ማዳመጥ፣ መደነስና ልብስ ማውለቅ … ካለበት አይወደድም። እንዲያውም ሊወገዝ የቀረበ ነው። መልካም ቀደምቶች ካልሰሩት ነገር ውስጥ መልካም የለም።” [አሲረቱ ሻሚያህ፡ 1/441-442]
ሁለት ነገሮችን ያዙ፦
አንድ፦ የመውሊድ በዓል በመልካም ቀደምቶች ዘመን እንደማይታወቅ።
ሁለት ፦ በጥፋት የታጀበ መውሊድ እንደማይደግፍ። ዛሬ ደግሞ እሱ ካወገዘው በላይ መውሊድ እጅግ በርካታ ሰቅጣጭ ጥፋቶችን ያጨቀ ሆኗል።
2. ኢብኑል ሓጅ (737 ሂ.)፦
“ትልልቅ ከሆኑ ዒባዳዎችና የዲን መገለጫዎች እንደሆነ በማመን ሰዎች ከፈጠሯቸው ቢድዐዎች የሚካተተው በረቢዐል አወል ላይ የሚሰሩት መውሊድ ነው። በርግጥም በርካታ ቢድዐዎችንና ክልክል ነገሮችን አጭቋል። ከዚህ ውስጥ ዘፈኖችን መጠቀማቸው ተጠቃሽ ነው። ከነሱ ጋር ከበሮ፣ ዋሽንትና ሌሎችም የሙዚቃ መሳሪያዎች ይኖራሉ። በዚህም የዘፈን ድግስ አድርገውታል። አንተንም እኛንም አላህ ይዘንልንና ምን ያክል ንፁህ የሆነችዋን ሱና መፃረር እንዳለ፣ ምንኛ አስቀያሚ እንደሆነ፣ ምንኛ አስነዋሪ እንደሆነ፣ እንዴት ወደ ሐራም ነገሮች እንደሚጎትት ተመልከት። ንፁህ የሆነችዋን ሱና በተፃረሩ ጊዜ፣ መውሊድንም በፈፀሙ ጊዜ መውሊዱ ላይ ብቻ እንዳልተገደቡ አታይምን?! ይልቁንም የተወሱትን በርካታ ከንቱ ነገሮች ጨመሩበት። እድለኛ የታደለ ማለት ቁርኣንና ሱናን በመተግበርና ወደዚያ በሚያደርስ ነገርም ላይ እጆቹን ያሰረ ነው። እሷም ያለፉትን ቀደምቶች መከተል ነው፣ ሁሉንም አላህ መልካም ስራዎቻቸውን ይውደድላቸውና። ምክንያቱም እነሱ ከኛ የበለጠ ሱናን የሚያውቁ ናቸውና። ምክንያቱም ንግግርን ይበልጥ የሚያውቁ፣ ሁኔታንም ይበልጥ የሚረዱ ናቸውና። ልክ እንዲሁ እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ በመልካም የተከተላቸውን መከተል ይገባል። ከዘመናችን ሰዎች ባህሎችና ዝቃጭ ባህሎችን ከሚፈፅሙ ሰዎች ይጠንቀቅ።
ዘፈን ከኖረ እነዚህ ጥፋቶች በመውሊድ ተግባር ላይ የተደራረቡ ናቸው። ከሱ የፀዳ ሆኖ ምግብ ብቻ ካዘጋጀ በዚህም መውሊድን ካሰበና ወንድሞችን ወደሱ ከጠራ፣ ቀደም ብለን ከጠቀስነው ሁሉ ነፃ ከሆነ በኒያው ብቻ ቢድዐ ይሆናል። ምክንያቱም ይሄ በዲን ላይ ጭማሬ ነውና። ካለፉ ቀደምቶች ስራም አይደለምና። እናም እነሱ ከነበሩበት ተፃራሪ የሆነ ኒያ ከመጨመር ይልቅ ቀደምቶችን መከተል በላጭ ነው። ኧረ እንዲያውም ግዴታ ነው። ምክንያቱም እነሱ የአላህ መልእክተኛን ﷺ ሱና በመከተል፣ እሳቸውንና ሱናቸውን በማላቅ ከሰው ሁሉ በላጮች ነበሩና። ለነሱ ወደዚህ በመሽቀዳደም በኩል የቀዳሚነት ማእረግ አላቸው። ከነሱ ከአንዳቸውም መውሊድን እንዳሰበ አልተላለፈም። እኛም ለነሱ ተከታዮች ነን። ስለሆነም የበቃቸው ይበቃናል።” [አልመድኸል፡ 2/204-312]
ስለ ጭፈራና ማጨብጨብ ደግሞ እንዲህ ይላል፡- “የሆነ ሰው በ661 እንዲህ የሚል ጥያቄ አዘጋጅቶ ወደ አራቱም መዝሀብ ምሁራን ዘንድ አመራ፡- ‘ክቡራን የዲን መሪዎች የሆኑ ምሁራንና ሙስሊም ዑለማዎች አላህ እሱን ለመታዘዝ ያድላቸው፣ በውዴታውም ላይ ያግዛቸውና የሆኑ የሙስሊም ስብስቦች ወደሆነ ሃገር ሄዱና ወደ መስጂድ አመሩ። በውስጡም ማጨብጨብ፣ መዝፈንና አንዲሁም አንዳንዴ በእጃቸው አንዳንዴ በድቤዎችና በዋሺንቶች መጨፈር ያዙ። በሸሪዐ ይህን መስጂድ ውስጥ መፈፀም ይቻላልን? አላህ ምንዳችሁን ይክፈላችሁና ፈትዋ ስጡን ..’ የዚህን ጊዜ
* ሻፊዒያዎች፡- ‘እንዲህ አይነት መዝሙር መስማት የተጠላ ነው። ባጢል ነው የሚመስለው። ይህን የሚዘምር ሰው ምስክርነቱ ተቀባይነት አይኖረውም። ወላሁ አዕለም’ አሉ።
* ማሊኪያዎች፡- ‘በመሪዎች ላይ እነዚህን ተውበት አድርገው ወደ አላህ እስከሚመለሱ ድረስ ሊከለክሏቸውና ከመስጂድ ሊያስወጧቸው ግዴታ አለባቸው። ወላሁ አዕለም’ አሉ።
* ሐንበሊያዎች፡- ‘ይህን የሚሰራ ሰው ከኋላው አይሰገድም። ምስክርነቱ ተቀባይነት የለውም። ዳኛ ከሆነ ፍርዱ ተቀባይነት የለውም። ኒካሕ ካሰረም ኒካሑ ውድቅ ነው። ወላሁ አዕለም’ አሉ።
* ሐነፍያዎች፡- ‘የተጨፈረባት ምንጣፍ እስከምትታጠብ ድረስ አይሰገድባትም። የተጨፈረባት መሬትም አፈሯ ተቆፍሮ እስከሚወገድ ድረስ አይሰገድባትም። ወላሁ አዕለም’ አሉ።” [አልመድኸል፡ 3/99]
3. አልወንሺሪሲ (834 ሂ.)፡-
“ሙስሊሞች ዘንድ የተከበረ ቢሆንም ነገር ግን በሱ ውስጥ አንዳንድ ቢድዐዎች እስከሚፈፀሙበት ያደረሱት ጉዳዮች አሉ። ይህም በብዛት በዘፈን መሳሪያዎች መገኘትና በሌሎችም ያልተፈቀዱ ፈጠራዎች ምክንያት ነው። እሳቸውን ﷺ ማላቅ ሊሆን የሚገባው ሱናቸውን በመከተልና ፈለጎቻቸውን በመፈፀም ነው። እንጂ መልካም ቀደምቶች ዘንድ ያልነበሩ ቢድዐዎችን በመፍጠር አይደለም።” [አልሚዕያሩል ሙዕሪብ፡ 1/357-358]
4. ኢብኑ ሐጀር (852 ሂ.)፡-
የመውሊድ ደጋፊዎች የሚያጣቅሱት የኢብኑ ሐጀር ንግግር እንዲህ የሚል ነው፡- “የመውሊድ ተግባር መሰረቱ ቢድዐ ነው። በሶስቱ ክፍለ ዘመናት ከነበሩት መልካም ቀደምቶች ከአንድም አልተላለፈም። ይህም ከመሆኑ ጋር ግን መልካም ነገሮችንም አፍራሾችንም ይዟል። በዚህ ተግባር ላይ አፍራሾቹን ርቆ መልካሞቹ ላይ ያነጣጠረ መልካም ቢድዐ ይሆናል። ካልሆነ ግን አይቻልም።” ” [አልሓዊ፡ 1/228]
አስተውሉ!
* መውሊድ ከኢብኑ ሐጀር ዘንድ ቢድዐ እንጂ ሱና አይደለም።
* “በሶስቱ ክፍለ ዘመናት ከነበሩት መልካም ቀደምቶች (ሶሐቦች፣ ታቢዒዮችና አትባዑ ታቢዒን) ከአንድም አልተላለፈም” ማለቱ ደግሞ “ነብዩ ﷺ እና ሶሐቦቻቸው አክብረውታል” የሚሉ ቀጣ. ፊዎችን ወሽመጣቸውን የሚቆርጥ ነው።
* መውሊድ ውስጥ ጥፋቶች እንደሚገኙ መግለፁ የዛሬ መውሊድ ጨፋሪዎች ዘንድ የማይገኝ ምስክርነት ነው።
* አፍራሽ ነገሮቹ ካልተራቁ መውሊዱ እንደማይፈቀድ መናገሩ ደግሞ ከዛሬ መውሊድ አክባሪዎች ጋር ፈፅሞ እንደማይገጥም ማሳያ ነው።
እነዚህን ነጥቦች ያስተዋለ ሰው እንጥፍጣፊ ታክል ሚዛናዊነት ካለው ኢብኑ ሐጀርን ዛሬ ለሚፈፀመው መውሊድ ለማጣቀስ አይዳፈርም።
5. ሲዩጢ (911 ሂ.)፡-
“ሰዎች ተሰባስበው ከቁርኣን የተወሰነ ቢቀሩ፣ ስለ ነብዩ ﷺ ሁኔታ አጀማመርና ሲወለዱ የነበሩ ተአምራትን የሚያወሱ ዘገባዎችን ቢያወሱ ከዚያም ማእድ ቀርቦ ተመግበው ቢመለሱና በዚህ ላይ ምንም ካልጨመሩ ይሄ ባለቤቱ የሚመነዳበት ከመልካም ቢድዐ ነው።…” [አልሓዊ፡ 1/220-221]
~
የመውሊድ ደጋፊዎች ለዚህ ቢድዐ የሚያጣቅሱት ትልቁ ማስረጃ እነ እከሌ ደግፈውታል እያሉ ዑለማዎችን ማጣቀስ ነው። ሐቂቃው ግን እነዚህ ዓሊሞች ዛሬ መውሊድ ላይ በሚታየው መልኩ የፈቀዱ አለመሆናቸው ነው። ይሄውና አይታችሁ ታዘቡ፡-
1. አተዝመንቲ (682 ሂ.?)፡-
“የመውሊድ ተግባር በመልካም ቀደምቶች የኢስላም ቀዳሚ ዘመን አልተከሰተም።” “መውሊድ …ፈፃሚው ደጋጎችን መሰብሰብ፣ በነብዩ ላይ ሶለዋት ማውረድ፣ ድሆችንና ምስኪኖችን ምግብ ማብላትን ካሰበ መልካም ቢድዐ ነው። በዚህ ልክና በዚህ ሸርጥ (መስፈርት) ከሆነ ይመነዳበታል። እንጂ ቂላቂሎችን መሰብሰብ፣ ዜማ ማዳመጥ፣ መደነስና ልብስ ማውለቅ … ካለበት አይወደድም። እንዲያውም ሊወገዝ የቀረበ ነው። መልካም ቀደምቶች ካልሰሩት ነገር ውስጥ መልካም የለም።” [አሲረቱ ሻሚያህ፡ 1/441-442]
ሁለት ነገሮችን ያዙ፦
አንድ፦ የመውሊድ በዓል በመልካም ቀደምቶች ዘመን እንደማይታወቅ።
ሁለት ፦ በጥፋት የታጀበ መውሊድ እንደማይደግፍ። ዛሬ ደግሞ እሱ ካወገዘው በላይ መውሊድ እጅግ በርካታ ሰቅጣጭ ጥፋቶችን ያጨቀ ሆኗል።
2. ኢብኑል ሓጅ (737 ሂ.)፦
“ትልልቅ ከሆኑ ዒባዳዎችና የዲን መገለጫዎች እንደሆነ በማመን ሰዎች ከፈጠሯቸው ቢድዐዎች የሚካተተው በረቢዐል አወል ላይ የሚሰሩት መውሊድ ነው። በርግጥም በርካታ ቢድዐዎችንና ክልክል ነገሮችን አጭቋል። ከዚህ ውስጥ ዘፈኖችን መጠቀማቸው ተጠቃሽ ነው። ከነሱ ጋር ከበሮ፣ ዋሽንትና ሌሎችም የሙዚቃ መሳሪያዎች ይኖራሉ። በዚህም የዘፈን ድግስ አድርገውታል። አንተንም እኛንም አላህ ይዘንልንና ምን ያክል ንፁህ የሆነችዋን ሱና መፃረር እንዳለ፣ ምንኛ አስቀያሚ እንደሆነ፣ ምንኛ አስነዋሪ እንደሆነ፣ እንዴት ወደ ሐራም ነገሮች እንደሚጎትት ተመልከት። ንፁህ የሆነችዋን ሱና በተፃረሩ ጊዜ፣ መውሊድንም በፈፀሙ ጊዜ መውሊዱ ላይ ብቻ እንዳልተገደቡ አታይምን?! ይልቁንም የተወሱትን በርካታ ከንቱ ነገሮች ጨመሩበት። እድለኛ የታደለ ማለት ቁርኣንና ሱናን በመተግበርና ወደዚያ በሚያደርስ ነገርም ላይ እጆቹን ያሰረ ነው። እሷም ያለፉትን ቀደምቶች መከተል ነው፣ ሁሉንም አላህ መልካም ስራዎቻቸውን ይውደድላቸውና። ምክንያቱም እነሱ ከኛ የበለጠ ሱናን የሚያውቁ ናቸውና። ምክንያቱም ንግግርን ይበልጥ የሚያውቁ፣ ሁኔታንም ይበልጥ የሚረዱ ናቸውና። ልክ እንዲሁ እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ በመልካም የተከተላቸውን መከተል ይገባል። ከዘመናችን ሰዎች ባህሎችና ዝቃጭ ባህሎችን ከሚፈፅሙ ሰዎች ይጠንቀቅ።
ዘፈን ከኖረ እነዚህ ጥፋቶች በመውሊድ ተግባር ላይ የተደራረቡ ናቸው። ከሱ የፀዳ ሆኖ ምግብ ብቻ ካዘጋጀ በዚህም መውሊድን ካሰበና ወንድሞችን ወደሱ ከጠራ፣ ቀደም ብለን ከጠቀስነው ሁሉ ነፃ ከሆነ በኒያው ብቻ ቢድዐ ይሆናል። ምክንያቱም ይሄ በዲን ላይ ጭማሬ ነውና። ካለፉ ቀደምቶች ስራም አይደለምና። እናም እነሱ ከነበሩበት ተፃራሪ የሆነ ኒያ ከመጨመር ይልቅ ቀደምቶችን መከተል በላጭ ነው። ኧረ እንዲያውም ግዴታ ነው። ምክንያቱም እነሱ የአላህ መልእክተኛን ﷺ ሱና በመከተል፣ እሳቸውንና ሱናቸውን በማላቅ ከሰው ሁሉ በላጮች ነበሩና። ለነሱ ወደዚህ በመሽቀዳደም በኩል የቀዳሚነት ማእረግ አላቸው። ከነሱ ከአንዳቸውም መውሊድን እንዳሰበ አልተላለፈም። እኛም ለነሱ ተከታዮች ነን። ስለሆነም የበቃቸው ይበቃናል።” [አልመድኸል፡ 2/204-312]
ስለ ጭፈራና ማጨብጨብ ደግሞ እንዲህ ይላል፡- “የሆነ ሰው በ661 እንዲህ የሚል ጥያቄ አዘጋጅቶ ወደ አራቱም መዝሀብ ምሁራን ዘንድ አመራ፡- ‘ክቡራን የዲን መሪዎች የሆኑ ምሁራንና ሙስሊም ዑለማዎች አላህ እሱን ለመታዘዝ ያድላቸው፣ በውዴታውም ላይ ያግዛቸውና የሆኑ የሙስሊም ስብስቦች ወደሆነ ሃገር ሄዱና ወደ መስጂድ አመሩ። በውስጡም ማጨብጨብ፣ መዝፈንና አንዲሁም አንዳንዴ በእጃቸው አንዳንዴ በድቤዎችና በዋሺንቶች መጨፈር ያዙ። በሸሪዐ ይህን መስጂድ ውስጥ መፈፀም ይቻላልን? አላህ ምንዳችሁን ይክፈላችሁና ፈትዋ ስጡን ..’ የዚህን ጊዜ
* ሻፊዒያዎች፡- ‘እንዲህ አይነት መዝሙር መስማት የተጠላ ነው። ባጢል ነው የሚመስለው። ይህን የሚዘምር ሰው ምስክርነቱ ተቀባይነት አይኖረውም። ወላሁ አዕለም’ አሉ።
* ማሊኪያዎች፡- ‘በመሪዎች ላይ እነዚህን ተውበት አድርገው ወደ አላህ እስከሚመለሱ ድረስ ሊከለክሏቸውና ከመስጂድ ሊያስወጧቸው ግዴታ አለባቸው። ወላሁ አዕለም’ አሉ።
* ሐንበሊያዎች፡- ‘ይህን የሚሰራ ሰው ከኋላው አይሰገድም። ምስክርነቱ ተቀባይነት የለውም። ዳኛ ከሆነ ፍርዱ ተቀባይነት የለውም። ኒካሕ ካሰረም ኒካሑ ውድቅ ነው። ወላሁ አዕለም’ አሉ።
* ሐነፍያዎች፡- ‘የተጨፈረባት ምንጣፍ እስከምትታጠብ ድረስ አይሰገድባትም። የተጨፈረባት መሬትም አፈሯ ተቆፍሮ እስከሚወገድ ድረስ አይሰገድባትም። ወላሁ አዕለም’ አሉ።” [አልመድኸል፡ 3/99]
3. አልወንሺሪሲ (834 ሂ.)፡-
“ሙስሊሞች ዘንድ የተከበረ ቢሆንም ነገር ግን በሱ ውስጥ አንዳንድ ቢድዐዎች እስከሚፈፀሙበት ያደረሱት ጉዳዮች አሉ። ይህም በብዛት በዘፈን መሳሪያዎች መገኘትና በሌሎችም ያልተፈቀዱ ፈጠራዎች ምክንያት ነው። እሳቸውን ﷺ ማላቅ ሊሆን የሚገባው ሱናቸውን በመከተልና ፈለጎቻቸውን በመፈፀም ነው። እንጂ መልካም ቀደምቶች ዘንድ ያልነበሩ ቢድዐዎችን በመፍጠር አይደለም።” [አልሚዕያሩል ሙዕሪብ፡ 1/357-358]
4. ኢብኑ ሐጀር (852 ሂ.)፡-
የመውሊድ ደጋፊዎች የሚያጣቅሱት የኢብኑ ሐጀር ንግግር እንዲህ የሚል ነው፡- “የመውሊድ ተግባር መሰረቱ ቢድዐ ነው። በሶስቱ ክፍለ ዘመናት ከነበሩት መልካም ቀደምቶች ከአንድም አልተላለፈም። ይህም ከመሆኑ ጋር ግን መልካም ነገሮችንም አፍራሾችንም ይዟል። በዚህ ተግባር ላይ አፍራሾቹን ርቆ መልካሞቹ ላይ ያነጣጠረ መልካም ቢድዐ ይሆናል። ካልሆነ ግን አይቻልም።” ” [አልሓዊ፡ 1/228]
አስተውሉ!
* መውሊድ ከኢብኑ ሐጀር ዘንድ ቢድዐ እንጂ ሱና አይደለም።
* “በሶስቱ ክፍለ ዘመናት ከነበሩት መልካም ቀደምቶች (ሶሐቦች፣ ታቢዒዮችና አትባዑ ታቢዒን) ከአንድም አልተላለፈም” ማለቱ ደግሞ “ነብዩ ﷺ እና ሶሐቦቻቸው አክብረውታል” የሚሉ ቀጣ. ፊዎችን ወሽመጣቸውን የሚቆርጥ ነው።
* መውሊድ ውስጥ ጥፋቶች እንደሚገኙ መግለፁ የዛሬ መውሊድ ጨፋሪዎች ዘንድ የማይገኝ ምስክርነት ነው።
* አፍራሽ ነገሮቹ ካልተራቁ መውሊዱ እንደማይፈቀድ መናገሩ ደግሞ ከዛሬ መውሊድ አክባሪዎች ጋር ፈፅሞ እንደማይገጥም ማሳያ ነው።
እነዚህን ነጥቦች ያስተዋለ ሰው እንጥፍጣፊ ታክል ሚዛናዊነት ካለው ኢብኑ ሐጀርን ዛሬ ለሚፈፀመው መውሊድ ለማጣቀስ አይዳፈርም።
5. ሲዩጢ (911 ሂ.)፡-
“ሰዎች ተሰባስበው ከቁርኣን የተወሰነ ቢቀሩ፣ ስለ ነብዩ ﷺ ሁኔታ አጀማመርና ሲወለዱ የነበሩ ተአምራትን የሚያወሱ ዘገባዎችን ቢያወሱ ከዚያም ማእድ ቀርቦ ተመግበው ቢመለሱና በዚህ ላይ ምንም ካልጨመሩ ይሄ ባለቤቱ የሚመነዳበት ከመልካም ቢድዐ ነው።…” [አልሓዊ፡ 1/220-221]
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ዛሬ እንደሚታየው በዚህ ላይ ብዙ ነገር ከተጨመረስ? ሌሎች ብልግናዎች ይቅሩና ጭፈራውን አስመልክቶ እራሱ እንዲህ ብሏል፦ “ከነዚህም (ከቢድዐዎች) ውስጥ የሆነው በመስጂድ ውስጥ የሚፈፀም ጭፈራ፣ ዘፈን፣ ድቤ መምታት፣ ረባብና ሌሎችም የሙዚቃ መሳሪያዎች ናቸው። ይህንን ከመስጂድ ውስጥ የፈፀመ ሊባረርና ሊደበደብ የሚገባው ጠማማ ሙብተዲዕ ነው። ምክንያቱም አላህ እንዲላቅ ያዘዘውን ነገር እያቃለለ ነውና። … (ከመስጂድ ውስጥ) የዘፈነ ወይም የጨፈረ ቅጣት የሚገባው የሆነ ጠሞ አጥማሚ ሙብተዲዕ ነው።” [ሐቂቀቱ ሱና ወልቢድዐ፡ 191]
6. አልሀይተሚ (974 ሂ.)፡-
“እኛ ዘንድ የሚተገበሩት ብዙዎቹ መውሊዶች እንደ ሶደቃ፣ ዚክር፣ በነብዩ ሶላትና ሰላም ማድረስና እሳቸውን ማወደስን የመሳሰሉ ብዙ ኸይሮች ያሉት ሲሆን እንዲሁም ሸርም ኧረ እንዲያውም ብዙ ሸሮችም ያሉበት ነው። ሴቶች ባእድ የሆኑ ወንዶችን ከመመልከት ያለፈ ሌላ ጥፋት ባይኖር እንኳን ይሄ እራሱ በቂ ጥፋት ነው። ከፊሎቹ (መውሊዶች) ሸር የለባቸውም። ግን ይሄ አልፎ አልፎ ነው ያለው። የመጀመሪያው አይነት የተከለከለ ለመሆኑ ጥርጥር የለውም።” [አልፈታወል ሐዲሢያህ፡ 109]
አስተውሉ! የመውሊድ ደጋፊ ከመሆናቸው ጋር አብዛኞቹ መውሊዶች ብዙ ጥፋት ያለባቸው በመሆናቸው የተከለከሉ ለመሆናቸው ጥርጥር የለም እያሉ ነው።
7. ሙሐመድ ዒሊሽ (1217 ሂ.)፡-
“ለነብዩ ﷺ መውሊድ ማዘጋጀት የተወደደ አይደለም፣ በተለይ ደግሞ የድምፅ ቅላፄን ከፍ ዝቅ እያደረጉ እንደመቅራትና እንደ ዘፈን ያለ የተጠላ ነገር ካካተተ። በዚህ ዘመን ደግሞ ከዚህ ይቅርና ከዚህ የከፋ ከሆነም ነገር አይተርፍም።” [ፈትሑል ዐልዪል ማሊክ፡ 1/171]
ስናጠቃልል ለመውሊድ ማጣቀሻ ተደርገው የሚነሱት ዓሊሞች ይህንን በብዙ ጥፋቶች የተሞላውን መውሊድ እንደማይደግፉ እናረጋግጣለን። በዚህ ላይ ፈቃጅ የሚባሉት ዓሊሞች ከተቃዋሚዎች የተለዩ አይደሉም። ስለዚህ ይሄ በብዙ ፀያፍ ነገሮች የታጀበው መውሊድ በኢጅማዕ የተወገዘ ነው ማለት ነው። ሸውካኒ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦ “ዛሬ የሚከሰተው የዚህ አይነቱ (ጥፋቱ የበዛበት) መውሊድ ግን በአንድ ድምፅ (ኢጅማዕ) የተከለከለ ነው።” [አልፈትሑ ረባኒ፡ 2/1087-1099]
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 3/2014)
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
6. አልሀይተሚ (974 ሂ.)፡-
“እኛ ዘንድ የሚተገበሩት ብዙዎቹ መውሊዶች እንደ ሶደቃ፣ ዚክር፣ በነብዩ ሶላትና ሰላም ማድረስና እሳቸውን ማወደስን የመሳሰሉ ብዙ ኸይሮች ያሉት ሲሆን እንዲሁም ሸርም ኧረ እንዲያውም ብዙ ሸሮችም ያሉበት ነው። ሴቶች ባእድ የሆኑ ወንዶችን ከመመልከት ያለፈ ሌላ ጥፋት ባይኖር እንኳን ይሄ እራሱ በቂ ጥፋት ነው። ከፊሎቹ (መውሊዶች) ሸር የለባቸውም። ግን ይሄ አልፎ አልፎ ነው ያለው። የመጀመሪያው አይነት የተከለከለ ለመሆኑ ጥርጥር የለውም።” [አልፈታወል ሐዲሢያህ፡ 109]
አስተውሉ! የመውሊድ ደጋፊ ከመሆናቸው ጋር አብዛኞቹ መውሊዶች ብዙ ጥፋት ያለባቸው በመሆናቸው የተከለከሉ ለመሆናቸው ጥርጥር የለም እያሉ ነው።
7. ሙሐመድ ዒሊሽ (1217 ሂ.)፡-
“ለነብዩ ﷺ መውሊድ ማዘጋጀት የተወደደ አይደለም፣ በተለይ ደግሞ የድምፅ ቅላፄን ከፍ ዝቅ እያደረጉ እንደመቅራትና እንደ ዘፈን ያለ የተጠላ ነገር ካካተተ። በዚህ ዘመን ደግሞ ከዚህ ይቅርና ከዚህ የከፋ ከሆነም ነገር አይተርፍም።” [ፈትሑል ዐልዪል ማሊክ፡ 1/171]
ስናጠቃልል ለመውሊድ ማጣቀሻ ተደርገው የሚነሱት ዓሊሞች ይህንን በብዙ ጥፋቶች የተሞላውን መውሊድ እንደማይደግፉ እናረጋግጣለን። በዚህ ላይ ፈቃጅ የሚባሉት ዓሊሞች ከተቃዋሚዎች የተለዩ አይደሉም። ስለዚህ ይሄ በብዙ ፀያፍ ነገሮች የታጀበው መውሊድ በኢጅማዕ የተወገዘ ነው ማለት ነው። ሸውካኒ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦ “ዛሬ የሚከሰተው የዚህ አይነቱ (ጥፋቱ የበዛበት) መውሊድ ግን በአንድ ድምፅ (ኢጅማዕ) የተከለከለ ነው።” [አልፈትሑ ረባኒ፡ 2/1087-1099]
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 3/2014)
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
በቢድዐ አንጃዎች ላይ ምላሽ መስጠት፣ የተሸወደባቸው አካላት እውነቱን እንዲለይ መጣር ትልቅ ጂሃድ ነው። ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦
" الراد على أهل البدع مجاهد حتى كان يحيى بن يحيى يقول : الذب عن السنة أفضل من الجهاد "
"የቢድዐ ባለቤቶች ላይ ምላሽ የሚሰጥ ሰው እንደ ሙጃሂድ (በአላህ መንገድ ላይ እንደሚታገል) ይቆጠራል። እንዲያውም የሕያ ኢብን የሕያ
'ሱናን (የነቢዩን መንገድ) መከላከል ከጂሃድ የበለጠ ነው' ይሉ ነበር።" [አልፈታዋ ፡ 4/13]
አጥፊዎቹን ዝም ብለው የእርምት ትምህርት ሲሰጥ ጊዜ በውስጥ ክፍፍል አትጠመዱ የሚሉ አካላትን ቦታ መስጠት አይገባም። አንድነት በዚህ መልኩ አይረጋገጥም። እነዚህ አካላት የተውሒድ ጉዳይ የሚያሳስባቸው አይደሉም። ተከታትላችሁ አረጋግጡ። የሙታን አምልኮውን፣ ቁርኣን የአላህ ቃል አይደለም የሚለውን፣ የአላህን ሲፋት የሚያራቁተውን ሁሉ ዝም በሉ ይላሉ። እዚህ ላይ ዝም ካልን ከዚህ በኋላ ምን የቀረ ዲን አለ?!
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
" الراد على أهل البدع مجاهد حتى كان يحيى بن يحيى يقول : الذب عن السنة أفضل من الجهاد "
"የቢድዐ ባለቤቶች ላይ ምላሽ የሚሰጥ ሰው እንደ ሙጃሂድ (በአላህ መንገድ ላይ እንደሚታገል) ይቆጠራል። እንዲያውም የሕያ ኢብን የሕያ
'ሱናን (የነቢዩን መንገድ) መከላከል ከጂሃድ የበለጠ ነው' ይሉ ነበር።" [አልፈታዋ ፡ 4/13]
አጥፊዎቹን ዝም ብለው የእርምት ትምህርት ሲሰጥ ጊዜ በውስጥ ክፍፍል አትጠመዱ የሚሉ አካላትን ቦታ መስጠት አይገባም። አንድነት በዚህ መልኩ አይረጋገጥም። እነዚህ አካላት የተውሒድ ጉዳይ የሚያሳስባቸው አይደሉም። ተከታትላችሁ አረጋግጡ። የሙታን አምልኮውን፣ ቁርኣን የአላህ ቃል አይደለም የሚለውን፣ የአላህን ሲፋት የሚያራቁተውን ሁሉ ዝም በሉ ይላሉ። እዚህ ላይ ዝም ካልን ከዚህ በኋላ ምን የቀረ ዲን አለ?!
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
4_5861896121495854515.pdf
357.9 KB
አሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱላሂ ወበረካቱሁ ቀን 18/12/2017 E.C
በ2018 የትምህርት ዘመን ዐረብኛ ቋንቋን በኤክስቴንሽን መርሃ ግብር በዲግሪ ደረጃ ለመማር ማመልከት (መመዝገብ) ለሚፈልጉ ወንድሞችና እህቶች የማመልከቻው ጊዜው ከነሐሴ 20/12/2017 -15/01/ 2018 ዓ.ል መኾኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።
ስለዚህ መማር ለሚፈልጉ ወንድሞች እህቶች ይህ መረጃው ይደርሳቸው ዘንድ ሁላችንም የበኩላችንን እንወጣ በተለያዩ ግሩፖች ሸር እናድርገው የኸይር በር እንሁን።
✅ ስለዚህ ይኽን መረጃ:~
🌹ለደሴ፣
🌹ለኮምቦልቻ፣
🌹 ለሐይቅ
🌹 ለሐርቡ፣
🌹 ለደጋን፣
🌹 ለገርባ፣
🌹 ለባቲና፣
🌹 ለኸሚሴ ጀመዓዎች አሰራጩት !!!
የመመዝገቢያ መስፈርቶቹን ከዚህ ፒ ዲ ኤፍ(PDF) ውስጥ ማግኘት የምትችሉ መኾኑን እንገልጻለን፡፡
💐💐 ዐረብኛ ቋንቋ ለመማር ማመልከት ለሚፈልጉ ተማሪዎች ሲመጡ ሊይዟቸው የሚገቡ ነገሮች የሚከተሉት ናቸው 💐💐
1/ የ8ኛ ክፍል ካርድ፣
2/ የ9ኛና የ10ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
3/ የ10ኛ ክፍል ማትሪክ ካርድ፣
4/ የ11ኛና የ12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
5/ የ12ኛ ክፍል ማትሪክ ካርድ 2ቅጅና
6/ 2 ጉርድ ፎቶ ያስፈልጋችኋል።
በ2018 የትምህርት ዘመን ዐረብኛ ቋንቋን በኤክስቴንሽን መርሃ ግብር በዲግሪ ደረጃ ለመማር ማመልከት (መመዝገብ) ለሚፈልጉ ወንድሞችና እህቶች የማመልከቻው ጊዜው ከነሐሴ 20/12/2017 -15/01/ 2018 ዓ.ል መኾኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።
ስለዚህ መማር ለሚፈልጉ ወንድሞች እህቶች ይህ መረጃው ይደርሳቸው ዘንድ ሁላችንም የበኩላችንን እንወጣ በተለያዩ ግሩፖች ሸር እናድርገው የኸይር በር እንሁን።
✅ ስለዚህ ይኽን መረጃ:~
🌹ለደሴ፣
🌹ለኮምቦልቻ፣
🌹 ለሐይቅ
🌹 ለሐርቡ፣
🌹 ለደጋን፣
🌹 ለገርባ፣
🌹 ለባቲና፣
🌹 ለኸሚሴ ጀመዓዎች አሰራጩት !!!
የመመዝገቢያ መስፈርቶቹን ከዚህ ፒ ዲ ኤፍ(PDF) ውስጥ ማግኘት የምትችሉ መኾኑን እንገልጻለን፡፡
💐💐 ዐረብኛ ቋንቋ ለመማር ማመልከት ለሚፈልጉ ተማሪዎች ሲመጡ ሊይዟቸው የሚገቡ ነገሮች የሚከተሉት ናቸው 💐💐
1/ የ8ኛ ክፍል ካርድ፣
2/ የ9ኛና የ10ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
3/ የ10ኛ ክፍል ማትሪክ ካርድ፣
4/ የ11ኛና የ12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
5/ የ12ኛ ክፍል ማትሪክ ካርድ 2ቅጅና
6/ 2 ጉርድ ፎቶ ያስፈልጋችኋል።