HUETHICS Telegram 115
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ Main Campus '‘ሙስናን መታገል በተግባር’' በሚል መሪ ቃል ዓለም ዓቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በዛሬው ዕለት ተከብሯል፡፡

የምርምርና ቴ/ሽ/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ ሙስናና የስነ ምግባር ችግር ለአለምችን እና ለሰው ልጆች ፈተና ሆኖ የቆየ ሲሆን በተለይ በአፍሪካ በሚገኙ ሀገራት እጅግ በጣም ብዙ ሀብቶች እንደሚመዘበሩና በዚህ ችግር ውስጥም እየዳከሩ እንደሚገኙ በርካታ ጥናቶች እንደሚያሳዩ ጠቅሰው አለማችን ለመሰረታዊ ፍላጎት የሚሆን በቂ ሃብት ቢኖራትም ጥቂቶች በስግብግብነታቸው የተነሳ የብዙሃኖችን ሃብት በመመዝበር ያለቅጥ በማከማቸታቸው ምክንያት ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዳይኖር፣ የሰዎች የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲደፈርስና በየቦታው ግጭት እየነገሰ እንዲመጣ ሆኗዋል ብለዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስነ-ምግባርና ፀረሙስና ክበብ አስተማሪና ትምህርታዊ የሆነ ጭውውት እንዲሁም ሙስናን በተመለከተ ድንቅ የሆነ መነባነብ ለታዳሚው አቅርበዋል።

በተጨማሪም በፕሮግራሙ ላይ አቶ አባይነህ ገናሌ የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ተወካይ ዳይሬክተር ሙስናን መታገል በተግባር እንዴት ይቻላል በሚል ሃሳብ ላይ የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎችም የተለያዩ ነጥቦችን አንስተው ተወያይተዋል፡፡

በመጨረሻም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አያኖ በራሶ እንደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ከከፍተኛ አመራር ጀምሮ መምህራኖችና የአስተዳደር ሰራተኞች ለስራ የተመደበላቸውን ጊዜና ሰዓት እንዲሁም መገልገያ ቁሳቁሶችን በአግባቡ ከመጠቀም አንስቶ ሙስናን እና የስነ ምግባር ብልሽቶችን በመጋፈጥ እና ተማሪዎችም በስነ ምግባር የታነፁ ብቁ ዜጋ እንዲሆኑ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበው ፕሮግራሙ ተጠናቋል።


https://www.tgoop.com/HUethics



tgoop.com/HUethics/115
Create:
Last Update:

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ Main Campus '‘ሙስናን መታገል በተግባር’' በሚል መሪ ቃል ዓለም ዓቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በዛሬው ዕለት ተከብሯል፡፡

የምርምርና ቴ/ሽ/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ ሙስናና የስነ ምግባር ችግር ለአለምችን እና ለሰው ልጆች ፈተና ሆኖ የቆየ ሲሆን በተለይ በአፍሪካ በሚገኙ ሀገራት እጅግ በጣም ብዙ ሀብቶች እንደሚመዘበሩና በዚህ ችግር ውስጥም እየዳከሩ እንደሚገኙ በርካታ ጥናቶች እንደሚያሳዩ ጠቅሰው አለማችን ለመሰረታዊ ፍላጎት የሚሆን በቂ ሃብት ቢኖራትም ጥቂቶች በስግብግብነታቸው የተነሳ የብዙሃኖችን ሃብት በመመዝበር ያለቅጥ በማከማቸታቸው ምክንያት ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዳይኖር፣ የሰዎች የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲደፈርስና በየቦታው ግጭት እየነገሰ እንዲመጣ ሆኗዋል ብለዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስነ-ምግባርና ፀረሙስና ክበብ አስተማሪና ትምህርታዊ የሆነ ጭውውት እንዲሁም ሙስናን በተመለከተ ድንቅ የሆነ መነባነብ ለታዳሚው አቅርበዋል።

በተጨማሪም በፕሮግራሙ ላይ አቶ አባይነህ ገናሌ የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ተወካይ ዳይሬክተር ሙስናን መታገል በተግባር እንዴት ይቻላል በሚል ሃሳብ ላይ የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎችም የተለያዩ ነጥቦችን አንስተው ተወያይተዋል፡፡

በመጨረሻም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አያኖ በራሶ እንደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ከከፍተኛ አመራር ጀምሮ መምህራኖችና የአስተዳደር ሰራተኞች ለስራ የተመደበላቸውን ጊዜና ሰዓት እንዲሁም መገልገያ ቁሳቁሶችን በአግባቡ ከመጠቀም አንስቶ ሙስናን እና የስነ ምግባር ብልሽቶችን በመጋፈጥ እና ተማሪዎችም በስነ ምግባር የታነፁ ብቁ ዜጋ እንዲሆኑ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበው ፕሮግራሙ ተጠናቋል።


https://www.tgoop.com/HUethics

BY የ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስነምግባር እና ፀረ ሙስና ክበብ | Hawassa University Ethics and Anti corruption Club












Share with your friend now:
tgoop.com/HUethics/115

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

4How to customize a Telegram channel? Although some crypto traders have moved toward screaming as a coping mechanism, several mental health experts call this therapy a pseudoscience. The crypto community finds its way to engage in one or the other way and share its feelings with other fellow members. "Doxxing content is forbidden on Telegram and our moderators routinely remove such content from around the world," said a spokesman for the messaging app, Remi Vaughn. Polls With the sharp downturn in the crypto market, yelling has become a coping mechanism for many crypto traders. This screaming therapy became popular after the surge of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May or early June. Here, holders made incoherent groaning sounds in late-night Twitter spaces. They also role-played as urine-loving Goblin creatures.
from us


Telegram የ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስነምግባር እና ፀረ ሙስና ክበብ | Hawassa University Ethics and Anti corruption Club
FROM American