HUETHICS Telegram 113
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ Main Campus '‘ሙስናን መታገል በተግባር’' በሚል መሪ ቃል ዓለም ዓቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በዛሬው ዕለት ተከብሯል፡፡

የምርምርና ቴ/ሽ/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ ሙስናና የስነ ምግባር ችግር ለአለምችን እና ለሰው ልጆች ፈተና ሆኖ የቆየ ሲሆን በተለይ በአፍሪካ በሚገኙ ሀገራት እጅግ በጣም ብዙ ሀብቶች እንደሚመዘበሩና በዚህ ችግር ውስጥም እየዳከሩ እንደሚገኙ በርካታ ጥናቶች እንደሚያሳዩ ጠቅሰው አለማችን ለመሰረታዊ ፍላጎት የሚሆን በቂ ሃብት ቢኖራትም ጥቂቶች በስግብግብነታቸው የተነሳ የብዙሃኖችን ሃብት በመመዝበር ያለቅጥ በማከማቸታቸው ምክንያት ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዳይኖር፣ የሰዎች የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲደፈርስና በየቦታው ግጭት እየነገሰ እንዲመጣ ሆኗዋል ብለዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስነ-ምግባርና ፀረሙስና ክበብ አስተማሪና ትምህርታዊ የሆነ ጭውውት እንዲሁም ሙስናን በተመለከተ ድንቅ የሆነ መነባነብ ለታዳሚው አቅርበዋል።

በተጨማሪም በፕሮግራሙ ላይ አቶ አባይነህ ገናሌ የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ተወካይ ዳይሬክተር ሙስናን መታገል በተግባር እንዴት ይቻላል በሚል ሃሳብ ላይ የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎችም የተለያዩ ነጥቦችን አንስተው ተወያይተዋል፡፡

በመጨረሻም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አያኖ በራሶ እንደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ከከፍተኛ አመራር ጀምሮ መምህራኖችና የአስተዳደር ሰራተኞች ለስራ የተመደበላቸውን ጊዜና ሰዓት እንዲሁም መገልገያ ቁሳቁሶችን በአግባቡ ከመጠቀም አንስቶ ሙስናን እና የስነ ምግባር ብልሽቶችን በመጋፈጥ እና ተማሪዎችም በስነ ምግባር የታነፁ ብቁ ዜጋ እንዲሆኑ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበው ፕሮግራሙ ተጠናቋል።


https://www.tgoop.com/HUethics



tgoop.com/HUethics/113
Create:
Last Update:

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ Main Campus '‘ሙስናን መታገል በተግባር’' በሚል መሪ ቃል ዓለም ዓቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በዛሬው ዕለት ተከብሯል፡፡

የምርምርና ቴ/ሽ/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ ሙስናና የስነ ምግባር ችግር ለአለምችን እና ለሰው ልጆች ፈተና ሆኖ የቆየ ሲሆን በተለይ በአፍሪካ በሚገኙ ሀገራት እጅግ በጣም ብዙ ሀብቶች እንደሚመዘበሩና በዚህ ችግር ውስጥም እየዳከሩ እንደሚገኙ በርካታ ጥናቶች እንደሚያሳዩ ጠቅሰው አለማችን ለመሰረታዊ ፍላጎት የሚሆን በቂ ሃብት ቢኖራትም ጥቂቶች በስግብግብነታቸው የተነሳ የብዙሃኖችን ሃብት በመመዝበር ያለቅጥ በማከማቸታቸው ምክንያት ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዳይኖር፣ የሰዎች የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲደፈርስና በየቦታው ግጭት እየነገሰ እንዲመጣ ሆኗዋል ብለዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስነ-ምግባርና ፀረሙስና ክበብ አስተማሪና ትምህርታዊ የሆነ ጭውውት እንዲሁም ሙስናን በተመለከተ ድንቅ የሆነ መነባነብ ለታዳሚው አቅርበዋል።

በተጨማሪም በፕሮግራሙ ላይ አቶ አባይነህ ገናሌ የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ተወካይ ዳይሬክተር ሙስናን መታገል በተግባር እንዴት ይቻላል በሚል ሃሳብ ላይ የመወያያ ሃሳብ ያቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎችም የተለያዩ ነጥቦችን አንስተው ተወያይተዋል፡፡

በመጨረሻም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አያኖ በራሶ እንደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ከከፍተኛ አመራር ጀምሮ መምህራኖችና የአስተዳደር ሰራተኞች ለስራ የተመደበላቸውን ጊዜና ሰዓት እንዲሁም መገልገያ ቁሳቁሶችን በአግባቡ ከመጠቀም አንስቶ ሙስናን እና የስነ ምግባር ብልሽቶችን በመጋፈጥ እና ተማሪዎችም በስነ ምግባር የታነፁ ብቁ ዜጋ እንዲሆኑ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበው ፕሮግራሙ ተጠናቋል።


https://www.tgoop.com/HUethics

BY የ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስነምግባር እና ፀረ ሙስና ክበብ | Hawassa University Ethics and Anti corruption Club












Share with your friend now:
tgoop.com/HUethics/113

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

It’s easy to create a Telegram channel via desktop app or mobile app (for Android and iOS): The Channel name and bio must be no more than 255 characters long With the “Bear Market Screaming Therapy Group,” we’ve now transcended language. In the next window, choose the type of your channel. If you want your channel to be public, you need to develop a link for it. In the screenshot below, it’s ”/catmarketing.” If your selected link is unavailable, you’ll need to suggest another option. Among the requests, the Brazilian electoral Court wanted to know if they could obtain data on the origins of malicious content posted on the platform. According to the TSE, this would enable the authorities to track false content and identify the user responsible for publishing it in the first place.
from us


Telegram የ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስነምግባር እና ፀረ ሙስና ክበብ | Hawassa University Ethics and Anti corruption Club
FROM American