HISCULHEROFETHIOPIA Telegram 5723
Forwarded from Bketa @¥
መዝሙርና ምሥጢራዊ ሥርዓቱ
በሶስት ክፍል ከፋፍለን እንማማራለን።
መዝሙር ምንድን ነው? የሚለውን መጠይቅ ለርዕሰ ነገራችን ሐተታዊ ፍሬ ነገር መነሻ በማድረግ መሠረታዊ ትምህርታችንን እንጀምራለን፡፡
መዝሙር የባሕርይ አምላክ ልዑል እግዚአብሔር በሰማይና በምድር የሚመሰገንበት፣ የሚቀደስበትና የሚለመንበት ዐቢይ የጸሎት ክፍል የሆነ ጣዕመ ዜማ ነው፡፡ ‹‹እግዚአብሔርን አመስግኑ መዝሙር መልካም ነውና ለአምላካችን ምስጋና ማቅረብ ያማረ ነውና››ይለናል መዝሙረኛው ዳዊት መዝ. 146፥1 በተጨማሪ ኢሳ. 6፥1-5፣ መዝ. 65፥1-5 መመልከት ሰለ መዝሙር ምንነት ያስረዳል፡፡
መዝሙር ማለት ምን ማለት ነው? ያልን እንደ ሆነ መዝሙር ዘመረ አመሰገነ ካለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ቀጥተኛ ትርጉሙም ምስጋና፣ ልመና ወይም መማፀን፣ ማስደሰት፣ መደሰት፣ ማዜም ማለት ነው፡፡ ከዚህም ሌላ እግዚአብሔርን በእጥፍ ድርብ ማመስገን ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ‹‹ኑ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን ለአምላካችንና ለመድኃኒታችን እልል እንበል . . . አምላካችን እግዚአብሔር ታላቅ ነውና›› ይለናል መዝ. 94፥1-3 ስለ ጠቅላላ ትርጉሙ መዝ. 116፥1-2፣ ኢሳ. 35፥1-6 /38፥9/ መዝ.149፥1-4፣ መዝ. 150፥1-7፣ መዝ. 80፥1-3፣ ማቴ. 26፥30፣ ማር. 14፥26፣ ቆላ. 3፥16፣ ራእ. 14፥1-5 ማቴ. 21፥9፣ ማር. 11፥9፣ ሉቃ. 19፥38 መመልከት ይጠቅማል፡፡ ከላይ እንዳልነው መዝሙር ሲባል ማዜም ማለት ነው፡፡ ዜማ ማለት ራሱ በቀጥታ ሲፈታ ጩኸት /ድምፅን ማሰማት/ ማለት ነው፡፡
ይሁን እንጂ ዜማ የምስጋና ብቻ ሳይሆን የሐዘን /የለቅሶ /የቀረርቶ /የሽለላ /የፉከራና የደስታ ስሜት መግለጫ ድምፅ ነው፡፡ ኢሳ. 6፥1-5 ማቴ. 26፥30
ከዚህ ላይ ግን ዜማ ባልን ጊዜ የምስጋና መዝሙር ድምፅ ሐሴት ማለታችን ነው፡፡ ለምን ቢሉ ዜማ ራሱን የቻለ ጥሬ ቃል ቢሆንም ዘመረ፣ አመሰገነ፣ አዜመ ካለው ቃል ጋር በጠባይና በግብር ይመሳሰላልና ነው፡፡
የመዝሙር ወይም የዜማ ጥቅሙ ምንድን ነው?
ሀ. መዝሙር ለመማሪያና ለማስተማሪያ መዝሙር እግዚአብሔርን በተመስጦ ለማመስገን
ለ. መዝሙር ወደ እግዚአብሔር ልባዊ ጸሎት ወይም ልመና ለማቅረብ
ሐ. መዝሙር ልብን ለማነፅና ነፍስን ለማስደሰት ማለትም መንፈስን ለማደስ ለምክርና ለተግሣፅ ደግሞም ለማፅናናትና ለመፅናት እጅግ አድርጎ ይጠቅማል፡፡
መዝሙር ወይም ዜማ፡- የተጀመረው በአራቱ ሰማያት ማለትም በሰማያዊት ኢየሩሳሌም፣ በኢዮር፣ በራማና በኤረር በእነዚህ ያሉ መላእክት እግዚአብሔር ፈጣሪያቸውን ያለ ዕረፍት ሲያመሰግኑት ነው፡፡ ይህንንም ሲያረጋግጥ ነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹እግዚአብሔርን በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየሁት የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት ነበር ሱራፌልም ከእርሱ በላይ ቆመው ነበር፡፡ . . . አንዱም ለአንዱ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያሉ ይጮኹ ነበር፡፡ የመድረኩም መሠረት ከጩዋኺው ድምፅ የተነሣ ተናወጠ ቤቱም ጢስ ሞላበት፡፡›› ይላል ኢሳ. 6፥1-5፣ ራእ. 4፥4 ይህም በኪሩቤልና በሱራፌል ማለት በመላእክት የተጀመረው ጣዕመ ዜማ /መዝሙር/ በእነሱ አሰሚነት ለሰው ልጆች ታድሏል፡፡ ይህም ይታወቅ ዘንድ ሊቀ ነቢያት ሙሴ በሥልጣነ እግዚአብሔር እስራኤልን ከግብፅ የባርነት አገዛዝ ነፃ ባወጣበት ጊዜ ባሕረ ኤርትራን ከፍሎ በደረቅ ምድር ሲያሻግራቸው ሙሴና ተከታዮቹ በተለይም እኅቱ ማርያምና ሙሴ እግዚአብሔርን በከበሮ ድምፅ እያጀቡ በጣዕመ ዜማ አመስግነዋል፡፡ መዝሙርም በይፋ መጀመሩ የታወቀው በዚህ ጊዜ ነው፡፡ ዘጸ. 15፥1-22 ደግሞም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ባየው ራአይ 14፥1-6 በምድር የተዋጁት 144 ሺህ ወገኖች ማንም ያልዘመረውንና ሊዘምረውም የማይቻለውን ጣዕሙ ልዩ የሆነ አዲስ መዝሙር በመድኃኒታችን ዙፋን ፊት በኪሩቤልና በሱራፌል መካከል እንደዘመሩ ይገልፃል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዜማ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዘወትር ፈጣሪዋን የምታመሰግንበት ልዩ ዜማ /መዝሙር/ ከመላእክት የተገኘ ነው፡፡ ስለዚህ መዝሙራችን እስከ አሁን በዓለም ተወዳዳሪ አልተገኘለትም የተገኘውም በኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አማካኝነት ነው፡፡
እኛም አሁን የምንዘምረው መዝሙር በቅዱስ ያሬድ ዜማ ነው፡፡ የቅዱስ ያሬድ የመጀመሪያው ዜማም አርያም ይባላል፡፡ አርያም ማለትም ልዑል ከፍተኛ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ የመጀመሪያውን ዜማ አርያም ብሎ የሰየመው ከሰማይ ካሉ መላእክት ሰምቶ መዘመር ስለጀመረ ነው፡፡ ይህም ሲታወቅ ‹‹ቀዳሚ ዜማ ተሰምአ እም ሰማይ›› እያለ ይሄድ እንደነበር ሊቃውንት ይተርካሉ፡፡ ይህ ታላቅ ሊቅ በመንፈሳዊ ተመስጦ ሰማየ ሰማያት ተነጥቆ ከመላእክት ያገኘው ዜማ ዓይነቱ ሦስት ነው፡፡
እነዚህም
1ኛ. ግእዝ
2ኛ. ዕዝል
3ኛ. አራራይ ይባላሉ፡፡
እስከ አሁን በዓለም የማናቸውም ፍጥረት ዜማ ጣዕሙ ይለያይ እንጂ በእነዚህ የዜማ ዓይነቶች ብቻ የተጠቃለለ ነው፡፡ እነዚህ ሦስቱ የዜማ ስልቶችም ምሳሌና ትርጉም አላቸው ይኸውም፡-
ግእዝ፡ - ርቱዕ ማለት ነው፡፡ አብን ርቱዕ ሎቱ ነአኰቶ ክብር ምስጋና ለእርሱ ይሁን ማለት ነው፡፡
ዕዝል፡ - ጽኑዕ ማለት ነው፡፡ ወልድ ጽኑዕ መከራ ተቀብሎ አዳምን እንዳዳነው ለማጠየቅ ነው፡፡
አራራይ፡ - ጥዑም ማለት ነው፡፡ ሀብተ መንፈስ ቅዱስን እንደተጎናጸፍን ለማስረዳት ነው፡፡
ይህም ቢሆን ታዲያ ተነጣጥለው አይቀሩም ግእዝ ከተሰኘው ዜማ ዕዝልና አራራይ ይወጣሉ፡፡ ይህም በአሐዱ አብ ዜማ ይታወቃል፡፡ ምሥጢረ ሥላሴም ከአብ እምቅድመ ዓለም ወልድ ለመወለዱ፣ መንፈስ ቅዱስ ለመስረጹ ምሳሌ ነው፡፡ ከዚህም ጋር የንባቡና የድምፁ ቃና አንድ መሆን የሥላሴን አንድነት ሲያስረዳ የዜማው ሦስት ዓይነት መሆን ደግሞ የሦስትነታቸው ምሳሌ ነው፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የያሬድ ዜማ በቂና ጥሩ ጥሩ ምሳሌ ያላቸው 8 ዐበይት ምልክቶች አሉት፡፡ እነዚህም ዜማውን ለሚማር ደቀመዝሙርና ለሚዘምረው ሁሉ ፈረንጆች ኖታ እንደሚሉት በምልክትነት ሲያገለግል ምሳሌያቸውና ምሥጢራቸው ግን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ ስለእኛ የተቀበለውን መከራ የሚያስታውሱን ናቸው፡፡
እነዚህም ኋላ ሊቃውንት ከጨመሯቸው ከድርስና ከአንብር በስተቀር ዋናዎቹ የቅዱስ ያሬድ ብቻ ሲዘረዘሩ፡-
ይዘት ( . ) ፡- በአይሁድ ጭፍሮች ለመያዙ
ሂደት ( — )፡- ታስሮ ለመጎተቱ
ጭረት ( ﺮ )፡- ለግርፋቱ ሰንበር
ድፋት (┌┐)፡- አክሊል ሾኽ ለመድፋቱ
ደረት (└┘)፡- ሲሰቅሉት በመስቀሉ ላይ አንጋለው ከደረቱ ላይ ቆመው እየረገጡት ለመቸንከሩ
ርክርክ ( ፡ )፡- ለደሙ ነጠብጣብ አወራረድና ለችንካሮች ምልክት
ቁርጥ ( ├ )፡- በጦር ተወግቶ ፈጽሞ መሞቱ ለመታወቁ
ቅንአት ( ﺭ )፡- በቅንአት አይሁድ ለመግደላቸው
ከላይ የተጠቀሱት ምልክትና መስታወሻዎች ሲሆኑ 8 መሆናቸው 8ቱ ማኅበረ አይሁድ ተባብረውና ተማክረው በብዙ መከራ ለመግደላቸው ምሳሌ ነው፡፡
እነርሱም ፡- 1. ጸሐፍት ፈሪሳውያን
2. ሰዱቃውያን
3. ረበናት /አይሁድ መምህራን/
4. መገብተ ምኵራብ /የምኵራብ ሹማምንቶች/
5. ሊቀ ካህናት
6. መላሕቅተ ሕዝብ /የሕዝብ ሽማግላች/
7. ኃጥአን
8. መጸብኃን ቀራጮች ናቸው፡፡
በሊቃውንት የተጨመሩ ምልክቶች፡-
9. አንብር ( ⊏ )
10. ድርስ ( ስ )
በቀጣይ ክፍል እስከምንገናኝ
መልካም ግዜ ለሁላችን
ሠናይ ሶቤ ለኲልነ



tgoop.com/HISCULHEROFETHIOPIA/5723
Create:
Last Update:

መዝሙርና ምሥጢራዊ ሥርዓቱ
በሶስት ክፍል ከፋፍለን እንማማራለን።
መዝሙር ምንድን ነው? የሚለውን መጠይቅ ለርዕሰ ነገራችን ሐተታዊ ፍሬ ነገር መነሻ በማድረግ መሠረታዊ ትምህርታችንን እንጀምራለን፡፡
መዝሙር የባሕርይ አምላክ ልዑል እግዚአብሔር በሰማይና በምድር የሚመሰገንበት፣ የሚቀደስበትና የሚለመንበት ዐቢይ የጸሎት ክፍል የሆነ ጣዕመ ዜማ ነው፡፡ ‹‹እግዚአብሔርን አመስግኑ መዝሙር መልካም ነውና ለአምላካችን ምስጋና ማቅረብ ያማረ ነውና››ይለናል መዝሙረኛው ዳዊት መዝ. 146፥1 በተጨማሪ ኢሳ. 6፥1-5፣ መዝ. 65፥1-5 መመልከት ሰለ መዝሙር ምንነት ያስረዳል፡፡
መዝሙር ማለት ምን ማለት ነው? ያልን እንደ ሆነ መዝሙር ዘመረ አመሰገነ ካለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ቀጥተኛ ትርጉሙም ምስጋና፣ ልመና ወይም መማፀን፣ ማስደሰት፣ መደሰት፣ ማዜም ማለት ነው፡፡ ከዚህም ሌላ እግዚአብሔርን በእጥፍ ድርብ ማመስገን ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ‹‹ኑ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን ለአምላካችንና ለመድኃኒታችን እልል እንበል . . . አምላካችን እግዚአብሔር ታላቅ ነውና›› ይለናል መዝ. 94፥1-3 ስለ ጠቅላላ ትርጉሙ መዝ. 116፥1-2፣ ኢሳ. 35፥1-6 /38፥9/ መዝ.149፥1-4፣ መዝ. 150፥1-7፣ መዝ. 80፥1-3፣ ማቴ. 26፥30፣ ማር. 14፥26፣ ቆላ. 3፥16፣ ራእ. 14፥1-5 ማቴ. 21፥9፣ ማር. 11፥9፣ ሉቃ. 19፥38 መመልከት ይጠቅማል፡፡ ከላይ እንዳልነው መዝሙር ሲባል ማዜም ማለት ነው፡፡ ዜማ ማለት ራሱ በቀጥታ ሲፈታ ጩኸት /ድምፅን ማሰማት/ ማለት ነው፡፡
ይሁን እንጂ ዜማ የምስጋና ብቻ ሳይሆን የሐዘን /የለቅሶ /የቀረርቶ /የሽለላ /የፉከራና የደስታ ስሜት መግለጫ ድምፅ ነው፡፡ ኢሳ. 6፥1-5 ማቴ. 26፥30
ከዚህ ላይ ግን ዜማ ባልን ጊዜ የምስጋና መዝሙር ድምፅ ሐሴት ማለታችን ነው፡፡ ለምን ቢሉ ዜማ ራሱን የቻለ ጥሬ ቃል ቢሆንም ዘመረ፣ አመሰገነ፣ አዜመ ካለው ቃል ጋር በጠባይና በግብር ይመሳሰላልና ነው፡፡
የመዝሙር ወይም የዜማ ጥቅሙ ምንድን ነው?
ሀ. መዝሙር ለመማሪያና ለማስተማሪያ መዝሙር እግዚአብሔርን በተመስጦ ለማመስገን
ለ. መዝሙር ወደ እግዚአብሔር ልባዊ ጸሎት ወይም ልመና ለማቅረብ
ሐ. መዝሙር ልብን ለማነፅና ነፍስን ለማስደሰት ማለትም መንፈስን ለማደስ ለምክርና ለተግሣፅ ደግሞም ለማፅናናትና ለመፅናት እጅግ አድርጎ ይጠቅማል፡፡
መዝሙር ወይም ዜማ፡- የተጀመረው በአራቱ ሰማያት ማለትም በሰማያዊት ኢየሩሳሌም፣ በኢዮር፣ በራማና በኤረር በእነዚህ ያሉ መላእክት እግዚአብሔር ፈጣሪያቸውን ያለ ዕረፍት ሲያመሰግኑት ነው፡፡ ይህንንም ሲያረጋግጥ ነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹እግዚአብሔርን በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየሁት የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት ነበር ሱራፌልም ከእርሱ በላይ ቆመው ነበር፡፡ . . . አንዱም ለአንዱ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያሉ ይጮኹ ነበር፡፡ የመድረኩም መሠረት ከጩዋኺው ድምፅ የተነሣ ተናወጠ ቤቱም ጢስ ሞላበት፡፡›› ይላል ኢሳ. 6፥1-5፣ ራእ. 4፥4 ይህም በኪሩቤልና በሱራፌል ማለት በመላእክት የተጀመረው ጣዕመ ዜማ /መዝሙር/ በእነሱ አሰሚነት ለሰው ልጆች ታድሏል፡፡ ይህም ይታወቅ ዘንድ ሊቀ ነቢያት ሙሴ በሥልጣነ እግዚአብሔር እስራኤልን ከግብፅ የባርነት አገዛዝ ነፃ ባወጣበት ጊዜ ባሕረ ኤርትራን ከፍሎ በደረቅ ምድር ሲያሻግራቸው ሙሴና ተከታዮቹ በተለይም እኅቱ ማርያምና ሙሴ እግዚአብሔርን በከበሮ ድምፅ እያጀቡ በጣዕመ ዜማ አመስግነዋል፡፡ መዝሙርም በይፋ መጀመሩ የታወቀው በዚህ ጊዜ ነው፡፡ ዘጸ. 15፥1-22 ደግሞም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ባየው ራአይ 14፥1-6 በምድር የተዋጁት 144 ሺህ ወገኖች ማንም ያልዘመረውንና ሊዘምረውም የማይቻለውን ጣዕሙ ልዩ የሆነ አዲስ መዝሙር በመድኃኒታችን ዙፋን ፊት በኪሩቤልና በሱራፌል መካከል እንደዘመሩ ይገልፃል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዜማ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዘወትር ፈጣሪዋን የምታመሰግንበት ልዩ ዜማ /መዝሙር/ ከመላእክት የተገኘ ነው፡፡ ስለዚህ መዝሙራችን እስከ አሁን በዓለም ተወዳዳሪ አልተገኘለትም የተገኘውም በኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አማካኝነት ነው፡፡
እኛም አሁን የምንዘምረው መዝሙር በቅዱስ ያሬድ ዜማ ነው፡፡ የቅዱስ ያሬድ የመጀመሪያው ዜማም አርያም ይባላል፡፡ አርያም ማለትም ልዑል ከፍተኛ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ የመጀመሪያውን ዜማ አርያም ብሎ የሰየመው ከሰማይ ካሉ መላእክት ሰምቶ መዘመር ስለጀመረ ነው፡፡ ይህም ሲታወቅ ‹‹ቀዳሚ ዜማ ተሰምአ እም ሰማይ›› እያለ ይሄድ እንደነበር ሊቃውንት ይተርካሉ፡፡ ይህ ታላቅ ሊቅ በመንፈሳዊ ተመስጦ ሰማየ ሰማያት ተነጥቆ ከመላእክት ያገኘው ዜማ ዓይነቱ ሦስት ነው፡፡
እነዚህም
1ኛ. ግእዝ
2ኛ. ዕዝል
3ኛ. አራራይ ይባላሉ፡፡
እስከ አሁን በዓለም የማናቸውም ፍጥረት ዜማ ጣዕሙ ይለያይ እንጂ በእነዚህ የዜማ ዓይነቶች ብቻ የተጠቃለለ ነው፡፡ እነዚህ ሦስቱ የዜማ ስልቶችም ምሳሌና ትርጉም አላቸው ይኸውም፡-
ግእዝ፡ - ርቱዕ ማለት ነው፡፡ አብን ርቱዕ ሎቱ ነአኰቶ ክብር ምስጋና ለእርሱ ይሁን ማለት ነው፡፡
ዕዝል፡ - ጽኑዕ ማለት ነው፡፡ ወልድ ጽኑዕ መከራ ተቀብሎ አዳምን እንዳዳነው ለማጠየቅ ነው፡፡
አራራይ፡ - ጥዑም ማለት ነው፡፡ ሀብተ መንፈስ ቅዱስን እንደተጎናጸፍን ለማስረዳት ነው፡፡
ይህም ቢሆን ታዲያ ተነጣጥለው አይቀሩም ግእዝ ከተሰኘው ዜማ ዕዝልና አራራይ ይወጣሉ፡፡ ይህም በአሐዱ አብ ዜማ ይታወቃል፡፡ ምሥጢረ ሥላሴም ከአብ እምቅድመ ዓለም ወልድ ለመወለዱ፣ መንፈስ ቅዱስ ለመስረጹ ምሳሌ ነው፡፡ ከዚህም ጋር የንባቡና የድምፁ ቃና አንድ መሆን የሥላሴን አንድነት ሲያስረዳ የዜማው ሦስት ዓይነት መሆን ደግሞ የሦስትነታቸው ምሳሌ ነው፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የያሬድ ዜማ በቂና ጥሩ ጥሩ ምሳሌ ያላቸው 8 ዐበይት ምልክቶች አሉት፡፡ እነዚህም ዜማውን ለሚማር ደቀመዝሙርና ለሚዘምረው ሁሉ ፈረንጆች ኖታ እንደሚሉት በምልክትነት ሲያገለግል ምሳሌያቸውና ምሥጢራቸው ግን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ ስለእኛ የተቀበለውን መከራ የሚያስታውሱን ናቸው፡፡
እነዚህም ኋላ ሊቃውንት ከጨመሯቸው ከድርስና ከአንብር በስተቀር ዋናዎቹ የቅዱስ ያሬድ ብቻ ሲዘረዘሩ፡-
ይዘት ( . ) ፡- በአይሁድ ጭፍሮች ለመያዙ
ሂደት ( — )፡- ታስሮ ለመጎተቱ
ጭረት ( ﺮ )፡- ለግርፋቱ ሰንበር
ድፋት (┌┐)፡- አክሊል ሾኽ ለመድፋቱ
ደረት (└┘)፡- ሲሰቅሉት በመስቀሉ ላይ አንጋለው ከደረቱ ላይ ቆመው እየረገጡት ለመቸንከሩ
ርክርክ ( ፡ )፡- ለደሙ ነጠብጣብ አወራረድና ለችንካሮች ምልክት
ቁርጥ ( ├ )፡- በጦር ተወግቶ ፈጽሞ መሞቱ ለመታወቁ
ቅንአት ( ﺭ )፡- በቅንአት አይሁድ ለመግደላቸው
ከላይ የተጠቀሱት ምልክትና መስታወሻዎች ሲሆኑ 8 መሆናቸው 8ቱ ማኅበረ አይሁድ ተባብረውና ተማክረው በብዙ መከራ ለመግደላቸው ምሳሌ ነው፡፡
እነርሱም ፡- 1. ጸሐፍት ፈሪሳውያን
2. ሰዱቃውያን
3. ረበናት /አይሁድ መምህራን/
4. መገብተ ምኵራብ /የምኵራብ ሹማምንቶች/
5. ሊቀ ካህናት
6. መላሕቅተ ሕዝብ /የሕዝብ ሽማግላች/
7. ኃጥአን
8. መጸብኃን ቀራጮች ናቸው፡፡
በሊቃውንት የተጨመሩ ምልክቶች፡-
9. አንብር ( ⊏ )
10. ድርስ ( ስ )
በቀጣይ ክፍል እስከምንገናኝ
መልካም ግዜ ለሁላችን
ሠናይ ሶቤ ለኲልነ

BY ኢትዮጵያ


Share with your friend now:
tgoop.com/HISCULHEROFETHIOPIA/5723

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

2How to set up a Telegram channel? (A step-by-step tutorial) A few years ago, you had to use a special bot to run a poll on Telegram. Now you can easily do that yourself in two clicks. Hit the Menu icon and select “Create Poll.” Write your question and add up to 10 options. Running polls is a powerful strategy for getting feedback from your audience. If you’re considering the possibility of modifying your channel in any way, be sure to ask your subscribers’ opinions first. “Hey degen, are you stressed? Just let it all out,” he wrote, along with a link to join the group. When choosing the right name for your Telegram channel, use the language of your target audience. The name must sum up the essence of your channel in 1-3 words. If you’re planning to expand your Telegram audience, it makes sense to incorporate keywords into your name. Matt Hussey, editorial director of NEAR Protocol (and former editor-in-chief of Decrypt) responded to the news of the Telegram group with “#meIRL.”
from us


Telegram ኢትዮጵያ
FROM American