Telegram Web
የዛሬው ስምምነት የተፈረመበት ዶክመንት ተያይዟል።

ዋና ነጥቦች:
- በሚቀጥሉት 7 ቀናት ወታደራዊ ሀላፊዎቹ ለወታደሮቻቸው ኦረንቴሽን ይሰጣሉ

- ከዛም የፌደራል ባለስልጣናት በትግራይ ሀላፊነታቸውን ይረከባሉ

- የከባድ መሳርያዎች ትጥቅ አፈታት በትግራይ ክልል ያሉ የውጭ ሀይሎች እና ከመከላከያ ውጭ ያሉ ሀይሎች ከክልሉ መውጣት ጋር በአንድ ግዜ ይፈፀማል

- የቀላል መሳርያዎች ትጥቅ አፈታትን ለማሳለጥ ከሁለቱም ወገን የተውጣጣ ኮሚቴ ይቋቋማል።

Via:- ኤልያስ መሰረት
ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
አሸባሪው ሸኔ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጉንዶ መስቀል ከተማ መግባቱን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ።

ነዋሪዎቹ መንግስት በአስቸኳይ እንዲደርስላቸውም ጠይቀዋል።የሽብር ቡድኑ ከትናንት ጀምሮ በተለያዩ አቅጣጫዎች ወደ ከተማዋ እየገባ መሆኑንና ከተማዋን ሙሉ በሙሉ እንዳይቆጣጠር ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናገረዋል።

የከተማዋ ነዋሪዎች በቂ የጸጥታ ሀይል ባለመኖሩ ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ መግባታቸውን ገልጸው መንግስት በአፋጣኝ እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።

[Ethio FM]
ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
ሸዋ ደራ ጉንዶ መስቀል  ከአድስ አበባ 220 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች!

ከህዳር 03 ቀን ጀምሮ በኦነግ ሸኔ ከበባ ውስጥ ናት።

አሸባሪ ሸኔ አምሰት የደራ ቦታ ላይ ሰፍሯል
▪️1. ባቡ ድሬ
▪️2. ሀርቡ
▪️3. ራቾ አሙማ
▪️4.ጁሩ ዳዳ
▪️5. ሰለልኩላ ዙሪያ ቡርቃ የሚባል አካባቢ

በተለይ ጉንደ መስቀል ከተማ ውስጥ ገብተው ብዙ ሰው አግተዋል ሞተዋል። ከከበባ ለመውጣት እየተፋለመ ያለው ሚሊሻ ብቻ ነው ፤ እስካሁን በአካባቢው የመንግስት አካል የለም።

ትኩረት ለደራ  ሽዋ!

ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጸሙ "የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ምርመራ እንዲጀመር እና አጥፊዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ" አሜሪካ ጥሪ አቀረበች።

የኢትዮጵያ ተፋላሚ ኃይላት ግጭት ለማቆም፣ ለተቸገሩ ሁሉ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦትን ለማፋጠን፣ የሰላማዊ ሰዎችን ደሕንነት ለመጠበቅ እና መሠረታዊ አገልግሎቶችን መልሶ ለማስጀመር የደረሱበትን ስምምነት ሊያከብሩ እንደሚገባ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ ጥሪ አቅርበዋል። ኔድ ፕራስ ትላንት ቅዳሜ ባወጡት መግለጫ ጥሪውን ያቀረቡት የሁለቱ ተፋላሚ ኃይላት የጦር አዛዦች የፕሪቶሪያውን ሥምምነት ተግባራዊ የሚያደርግ ሰነድ ከፈረሙ በኋላ ነው።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ እና የትግራይ ኃይሎች አዛዥ ጄኔራል ታደሰ ወረደ ሰነዱን ከፈረሙ በኋላ የአፍሪካ ኅብረት ባወጣው መግለጫ በትግራይ እና አጎራባች ክልሎች ለተቸገሩ ሁሉ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ያለ ገደብ ለማመቻቸት ከሥምምነት መደረሱን አስታውቋል። ሁለቱ የጦር አዛዦች የተፈራረሙት ሰነድ በፕሪቶሪያ በተደረሰበት ግጭት የማቆም ሥምምነት መሠረት ለግብረ ሰናይ ሠራተኞች እና ለድርጅቶች የደህንነት ዋስትና መስጠት እንዲሁም ለሰላማዊ ሰዎች ጥበቃ ማድረግን ያካተተ ነው።

የአፍሪካ ኅብረት ያወጣው መግለጫ እንደሚያሳየው የትጥቅ አፈታት፣ አበታተን እና መልሶ ማዋሃድን የተመለከቱ ጉዳዮችን በዝርዝር የሚያብራራ የጋራ ኮሚቴ ለማቋቋም ተወስኗል። የኢትዮጵያ መንግሥት "በሰላም ሥምምነቱ በተያዘው የጊዜ ገደብ ትጥቅ የሚፈታበት እና መከላከያ ወደ መቐለ የሚገባበት ዕቅድ ላይ" ከሥምምነት መደረሱን ገልጿል። የአውሮፓ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ አኔተ ቬበር የትጥቅ አፈታትን በተመለከተ በሁለቱ ወገኖች መካከል የተደረሰው ሥምምነት "ወደ ፊት የሚወስድ አስፈላጊ እርምጃ" እንደሆነ ገልጸዋል።
 ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ከአምባሳደር ኢቶ ታካኮ ጋር ተወያዩ
**********************

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ይልቃል ከፋለ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ከሆኑት ኢቶ ታካኮ ጋር ተወያዩ።

የጃፓን ህዝብ እና መንግሥት ለክልሉ ልማት እያደረጉት ያለውን ድጋፍ እንደሚያደንቁ ዶ/ር ይልቃል ለአምባሳደሯ ገልፀውላቸዋል።

አምባሳደር ኢቶ ታካኮ በበኩላቸው በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ የሰለጠነ ብቁ የሰው ኃይል ለማውጣት ላለፉት 7 ዓመታት ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

የጃፓን ዩኒቨርሲቲዎች ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር በመስራት በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ከሚያበረክቱት አስተዋጽኦ በተጨማሪ የሀገሪቱ መንግሥት ባህርዳር ከተማን ጨምሮ በአማራ ክልል በግብርና፣ በንፁህ መጠጥ ውሃ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ላይ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

አምባሳደሯ በቆይታቸው በክልሉ የጤና ተቋማት የካይዘን ትግበራ ያለበትን ደረጃ ጨምሮ በመንግሥታቸው የሚደገፉ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችን እንደሚመለከቱ ይጠበቃል።

ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በነገው ዕለት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ  ይሰጣሉ!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በነገው ዕለት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች ማብራሪያ  እንደሚሰጡ ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ነገ ኀዳር 06 ቀን 2015 ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት 4ኛ መደበኛ ስብሰባውን እንደሚያካሂድ የምክር ቤቱ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ለኢዜአ ገልጿል፡፡

በመደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ መስከረም 30 ቀን 2015 ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በሚቀርቡ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ተመላክቷል።

በዚህም ምክር ቤቱ የመንግስትን አቋም በማዳመጥ የድጋፍ ሞሽኑን ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጿል፡፡

በዕለቱ በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙም ተገልጿል።

ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
በኮሜዲያን እሸቱ መለሰ አማካኝነት ከ1.5 ሚልዮን ዶላር በላይ ተሰበሰበ!

ኮመዲያን እሸቱ መለሰ "በሀገረ አሜሪካ ለሚቋቋመው ግዙፍ ስፋት ያለው ገዳም ቦታ መግዣ" ከ 1,500,000 የአሜሪካ ዶላር በላይ በአንድ ቀን መሰብሰብ ችሏል።

ሰሞኑን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በአሜሪካ ካሊፎርኒያ በመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ ገዳም ሥም ከ1497 ሄክታር በላይ ስፋት ያለው መሬት ልትገዛ እንደሆነ ማስታወቋ ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ ለገዳሙ መግዣ የሚሆነው ቅድመ ክፍያ ገንዘብ ለማሰባሰብ ኮሜዲያን እሸቱ በትናንትናው እለት ባዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ ከ15ሰአት በላይ በላይቭ(live) በመቆየት በአጠቃላይ ከ1.5ሚሊዮን ዶላር በላይ በማሰባሰብ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው የሆነውን ፈጣን የገቢ ማሰባሰብ ስራን አከናዉኗል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የሰሜን ካሊፎርኒያ፣ ኔቫዳ እና አሪዞና ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ቴዎፍሎስም የገቢ ማሰባሰቡን ያካሄዱትን ኮሜዲያን እሸቱን እና የዶንኪ ቲዩብ አባላቶችን ከልብ አመስግነዋል።

በዚህ ሰፊ ይዞታ ላይም የአብነት ትምህርት ቤት፣ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ዘመናዊ ዩኒቨርሲቲ፣ ሆስፒታል እንዲሁም ሌሎች በርካታ ተቋማትን ለማቋቋም እንደታቀደ የገለጹት ሊቀ ጳጳሱ፣ ለቦታው መግዣ የሚሆነውን 8 ሚሊዮን ዶላር ከምዕመናን ለማሰባሰብ እንደታሰበም ተናግረዋል።

Via:- Fidel Post
ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
ለአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የኮማንደርነት ማዕረግ ተሰጣት!

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ለአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ልዩ የኒሻን ሽልማት እና የኮማንደርነት ማዕረግ አበርክቶላታል፡፡

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በተሰማሩበት የሥራ መስክ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ 78 የኮሚሽኑ ስፖርት ክለብ አባላት የማዕረግ፣ የገንዘብና የልዩ ኒሻን ሽልማት አበርክቷል፡፡

በሽልማት ፕሮጋራሙ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ልዩ የኒሻን ሽልማት የተበረከተላት ሲሆን በኮሚሽኑ የኮማንደርነት ማዕረግም ተሰጥቷታል፡፡

ኮማንደር አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በተሰጣት ሽልማት መደሰቷን ገልጻ በማረሚያ ቤት ስፖርት ክለብ ትንሽ ልጅ ሆና በመቀጠር አሁን ለደረሰችበት ደረጃ መብቃቷንም አንስታለች፡፡

ሽልማቱ የማረሚያ ስፖርት ክለብ ወጣት አትሌቶች ጠንክረው እንዲሰሩ፣ እንዲበረታቱና የተሻለ ደረጃ እንዲደርሱ ያደርጋል ያለችው አትሌቷ በተለያዩ የውድድር መስኮች የኮሚሽኑ አትሌቶች ውጤታማ መሆናቸውን ገልፃለች፡፡

ኮሚሽኑ ለ34 ስፖርተኞች ከረዳት ሳጅን እስከ ኮማንደር ድረስ የማዕረግ ዕድገት ሲሰጥ ለ19 ስፖርተኞች ደግሞ የገንዘብ እና ለ13 ስፖርተኞች የእርከን ጭማሪና የገንዘብ ሽልማት ሰጥቷል፡፡

ለአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የተበረከተው ልዩ የሜዳሊያ ሽልማት ከረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ቀጥሎ ለ2ኛ ጊዜ መሆኑን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
ከአርባ በላይ የአማርኛ ፊልሞች ላይ የተወነው ተዋናይ ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) በድንገተኛ ህመም ዛሬ ጠዋት አርፏል ።

ተዋናዩ ካባለቤቱ የፊልም ተዋናይት
ቃልኪዳን ጥበቡ ጋር ከተለያየ በኋላ ድብርት ተደጋግሞ ያጠቃው እንደነበር ፊደል ፖስት ከቅርብ ወዳጆቹ ሰምቷል።

ዕድሜው በሰላሳዎቹ አጋማሽ የሚገኘው ተዋናይ ታሪኩ ተውልዶ ያደገው ተክለ ሐይማኖት አካባቢ ሲሆን የአንድ ልጅም አባት ነው።

በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝናን አና በብዙዎች ተወዳጅነትን ያተረፈ ተዋናይ ነው። በጉዳዬ ፊልም ላይ ደግሞ በድርሰት ፣ በዳይሬክተርነት እንዲሁም በትወና ተሳትፎበታል።

ከተወነባቸው ፊልሞች መካከል :- 300ሺ፣ የፍቅር ABCD ፣ ብላቴና፣ ቦሌ ማነቂያ ፣ እንደ ባል እና ሚስት ፣ ኢንጂነሮቹ ፣ እርቅ ይሁን ፣ ኢዮሪካ ፣ ጉዳዬ ፣ ሀገርሽ ሀገሬ ፣ ሕይወቴ ፣ ህይወት እና ሳቅ ፣ ከባድ ሚዛን ፣ ፍቅር እና ፌስቡክ ፣ ከቃል በላይ፣ላውንድሪ ቦይ ፣ ኮከባችን ፣ ማርትሬዛ ፣ ይመችሽ-የአራዳ ልጅ 2 ፣ ሞኙ የአራዳ ልጅ ፣ ትዳርን ፍለጋ ፣ አንድ ሁለት ፣ ብር ርርር ፣ ወደው አይሰርቁ፣ ወፌ ቆመች፣ ወንድሜ ያዕቆብ ፣ እንደ ቀልድ ፣ ወቶ አደር፣ አባት ሀገር፣ የሞግዚቷ ልጆች፣ ይዋጣልን ፣ ዋሻው፣ ወሬ ነጋሪ ፣ ወጣት በ97 ተጠቃሽ ናቸዉ።

#የኔቲዩብ ለአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ ወዳጅና አድናቂዎች መፅናናትን ይመኛል።

ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
Channel photo updated
Channel photo updated
Channel photo updated
Channel photo updated
2024/04/27 15:32:18
Back to Top
HTML Embed Code:


Fatal error: Uncaught Error: Call to undefined function pop() in /var/www/tgoop/chat.php:243 Stack trace: #0 /var/www/tgoop/route.php(43): include_once() #1 {main} thrown in /var/www/tgoop/chat.php on line 243