tgoop.com/Enatachn_mareyam/17988
Last Update:
†
[ 🕊 ክብርት ሰንበት 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ ወዮ ይህች ዕለት ያረጀችዋ ያለፈችባት አዲሲቱ የጸናችባት ናት ፤ ወዮ ይህች ዕለት እስረኞች [ ነፍሳት ] የተፈቱባት ባሮች [ ደቂቀ አዳም ] ነጻ የወጡባት ናት። ወዮ ይህች ዕለት የፈረሰ የታነጸባት ሰይጣንም የጠፋባት ናት።
ዳግመኛም ይህች ዕለት በምትሠለጥንበት ጊዜ [ አመ ትሰፍን ወይም ለዘለዓለም ጸንታ በምትኖርበት ጊዜ ] አዲስ ሥራ አዲስ ነገርም ይሆናል ፤ ያን ጊዜ የፀሐይና የጨረቃ የከዋክብትም ብርሃን ፣ ወይም ፀዳል [ ማንም ዓይነት ብርሃን ] ፣ ክረምት ወይም በጋ የለም።
ክብርት የምትሆን ይህች ሰንበተ ክርስቲያን ምን ትደንቅ ! እንደ አብ የሠለጠነች እንደ ወልድ የምትገዛ እንደ መንፈስ ቅዱስ [ ለዘለዓለም ] የምትኖር ናት ፤ ይህች ቅድስት ሰንበተ ክርስቲያን ምን ትደንቅ ! ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ዘንድ ለምኝልን ፣ ስለኛም አማልጂ ለዘለዓለሙ ! ❞
[ ቅዱስ ያሬድ ]
†
❝ አንተ ግን ከሆድ አውጥተኸኛልና ፥ በእናቴ ጡት ሳለሁም በአንተ ታመንሁ። ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ። ❞
[ መዝ.፳፪፥፱ ]
[ 🕊 ክብርት ሰንበት ! 🕊 ]
† † †
💖 🕊 💖
BY አብሰራ ገብርኤል ለማርያም

Share with your friend now:
tgoop.com/Enatachn_mareyam/17988