Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/Enatachn_mareyam/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tgoop/post.php on line 50
አብሰራ ገብርኤል ለማርያም@Enatachn_mareyam P.16648
ENATACHN_MAREYAM Telegram 16648
                        †                           

†    🕊         ዘ ወ ረ ደ         🕊   †


[  የጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት !   ]

💖

[   ክፍል ሁለት   ]


❝ እንኪያስ እጅግ የምወዳችሁ ምእመናን ሆይ ! ከኹሉም በፊት እነዚህን ነገሮች በስፋት እንነጋገርባቸው ዘንድ ፤ ዳግመኛም አንዳች የሚረባንን ነገር ይዘን ወደ ቤታችን እንመለስ ዘንድ ቃላችንን በታላቅ ትጋትና ጉጉት ሆናችሁ ትቀበሉት ዘንድ አሳስባችኋለሁ፡፡

ኹላችንም ወደዚህ ጉባኤ ስንመጣ እንዲሁና ያለ ዓላማ አይደለም፡፡ ወሬ ለማውራት ፣ ምን እንደተባለ እንኳን ሳንሰማ ለማጨብጨብ ፣ ከዚያም ምንም የሚረባ ነገርን ሳንይዝ ወደ ቤታችን ለመመለስ ወደዚህ ጉባኤ አልመጣንም፡፡ እኔ የመጣሁት ለነፍሳችሁ ድኅነት የሚጠቅም አንዳች ነገርን ለመናገር ነው ፤ እናንተም ስትመጡ በእኔ በባሪያው አድሮ እግዚአብሔር የሚናገረውን ነገር አድምጣችሁ ለመጠቀምና አንዳች የሚረባ ነገርን ይዛችሁ ወደ ቤታችሁ ለመመለስ ነው፡፡

ተመልከቱ ! ቤተክርስቲያን ማለት ቤተ ድኅነት ናት፡፡ ወደ እርሷ የሚመጡትም ለችግራቸው ተገቢውን መድኃኒት አግኝተው መሔድ አለባቸው፡፡ ተግባራዊ የኾነ ለውጥ ሳያመጡ ቃለ እግዚአብሔርን መማር ብቻ ምንም ጥቅም እንደሌለው ሲናገርም ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስ እንዲህ ብሏል ፦

"በእግዚአብሔር ፊት የሚጸድቁት ሕግን የሚያደርጉት እንጂ ሕግን የሚሰሙ አይደሉም፡፡" [ሮሜ.፪፥፲፫]

በቃል መነገሩ ፣ በልብ መታሰቡ ፣ በቅዱሳት መጻሕፍት መዘገቡ ከፍ ከፍ ይበልና አምላካችን ክርስቶስም ሲያስተምር ፦

"በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡" ብሏል [ማቴ.፯፥፳፩] ስለዚህ ተወዳጆች ሆይ ! ቃሉን በመስማታችን ብቻ አንዳች የምንጠቀመው ነገር ስለሌለ የሰማነውን የምናደርግ እንጂ የምንሰማ ብቻ አንሁን፡፡ እንዲህ ከሆነም እምነታችን ሕይወት ያለው እምነት ይሆናል፡፡

በመኾኑም ስለ ጾም የሚሰጠውን ስብከት ለማዳመጥ እዝነ ልቦናችሁን ክፈቱ፡፡ ከትሕትና እና ዓይናፋር ሙሽሪት ጋር ለማነጻጸር ያህል ፦ ሙሽሪቱን በሰርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች አስቀድመው ቤቱን ያስጌጡታል ፡ ይጠርጉታል፡፡ የቆሸሸ ልብስን የለበሰ ሰው ወደ ሰርጉ አዳራሽ እንዳይገባ ያደርጉታል፡፡ ወደ አዳራሹ መግባት የሚችለው የሰርግ ልብስ የለበሰ ሰው ብቻ ነው፡፡

እናንተም እንዲሁ ልታደርጉ ይገባችኋል ፦ ልቡናችሁን በማንጻት ፣ አብዝቶ ከመብላትና ራስን ካለመግዛት በመራቅ - የምግባር እናት ፣ የማስተዋልና የሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትሆን ጾምን ደጀ ልቡናችሁን በመክፈት ልትቀበሏት ይገባችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደሆነ ታላቅ ሐሴት ታደርጋላችሁ ፤ እርሷም ቁስለ ነፍሳችሁን ትፈውስላችኋለች፡፡

ሌላ ምሳሌ መስዬ ብነግራችሁ ፦ ሐኪሞች በህሙማን ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻና መርዘኛ ፈሳሽን ማስወገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ ሕሙማኑ ምግበ ሥጋን ከመውሰድ እንዲቆጠቡ ያደርጓቸዋል፡፡ ሕሙማኑ ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከሉ ግን ሐኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት የተፈለገውን ያህል ውጤት አይሰጥም፡፡ እኛም የነፍስንና የሥጋን ቁስል የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚህ በላይ ልንሆን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለሁ፡፡ ድህነትን የምንሻ ከሆነ ልቡናችንን ንጹህና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል ፤ እንዲህ ካልሆነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡ ❞

[ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]


      †                 †                †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖                    🕊                     💖
2



tgoop.com/Enatachn_mareyam/16648
Create:
Last Update:

                        †                           

†    🕊         ዘ ወ ረ ደ         🕊   †


[  የጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት !   ]

💖

[   ክፍል ሁለት   ]


❝ እንኪያስ እጅግ የምወዳችሁ ምእመናን ሆይ ! ከኹሉም በፊት እነዚህን ነገሮች በስፋት እንነጋገርባቸው ዘንድ ፤ ዳግመኛም አንዳች የሚረባንን ነገር ይዘን ወደ ቤታችን እንመለስ ዘንድ ቃላችንን በታላቅ ትጋትና ጉጉት ሆናችሁ ትቀበሉት ዘንድ አሳስባችኋለሁ፡፡

ኹላችንም ወደዚህ ጉባኤ ስንመጣ እንዲሁና ያለ ዓላማ አይደለም፡፡ ወሬ ለማውራት ፣ ምን እንደተባለ እንኳን ሳንሰማ ለማጨብጨብ ፣ ከዚያም ምንም የሚረባ ነገርን ሳንይዝ ወደ ቤታችን ለመመለስ ወደዚህ ጉባኤ አልመጣንም፡፡ እኔ የመጣሁት ለነፍሳችሁ ድኅነት የሚጠቅም አንዳች ነገርን ለመናገር ነው ፤ እናንተም ስትመጡ በእኔ በባሪያው አድሮ እግዚአብሔር የሚናገረውን ነገር አድምጣችሁ ለመጠቀምና አንዳች የሚረባ ነገርን ይዛችሁ ወደ ቤታችሁ ለመመለስ ነው፡፡

ተመልከቱ ! ቤተክርስቲያን ማለት ቤተ ድኅነት ናት፡፡ ወደ እርሷ የሚመጡትም ለችግራቸው ተገቢውን መድኃኒት አግኝተው መሔድ አለባቸው፡፡ ተግባራዊ የኾነ ለውጥ ሳያመጡ ቃለ እግዚአብሔርን መማር ብቻ ምንም ጥቅም እንደሌለው ሲናገርም ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስ እንዲህ ብሏል ፦

"በእግዚአብሔር ፊት የሚጸድቁት ሕግን የሚያደርጉት እንጂ ሕግን የሚሰሙ አይደሉም፡፡" [ሮሜ.፪፥፲፫]

በቃል መነገሩ ፣ በልብ መታሰቡ ፣ በቅዱሳት መጻሕፍት መዘገቡ ከፍ ከፍ ይበልና አምላካችን ክርስቶስም ሲያስተምር ፦

"በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡" ብሏል [ማቴ.፯፥፳፩] ስለዚህ ተወዳጆች ሆይ ! ቃሉን በመስማታችን ብቻ አንዳች የምንጠቀመው ነገር ስለሌለ የሰማነውን የምናደርግ እንጂ የምንሰማ ብቻ አንሁን፡፡ እንዲህ ከሆነም እምነታችን ሕይወት ያለው እምነት ይሆናል፡፡

በመኾኑም ስለ ጾም የሚሰጠውን ስብከት ለማዳመጥ እዝነ ልቦናችሁን ክፈቱ፡፡ ከትሕትና እና ዓይናፋር ሙሽሪት ጋር ለማነጻጸር ያህል ፦ ሙሽሪቱን በሰርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች አስቀድመው ቤቱን ያስጌጡታል ፡ ይጠርጉታል፡፡ የቆሸሸ ልብስን የለበሰ ሰው ወደ ሰርጉ አዳራሽ እንዳይገባ ያደርጉታል፡፡ ወደ አዳራሹ መግባት የሚችለው የሰርግ ልብስ የለበሰ ሰው ብቻ ነው፡፡

እናንተም እንዲሁ ልታደርጉ ይገባችኋል ፦ ልቡናችሁን በማንጻት ፣ አብዝቶ ከመብላትና ራስን ካለመግዛት በመራቅ - የምግባር እናት ፣ የማስተዋልና የሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትሆን ጾምን ደጀ ልቡናችሁን በመክፈት ልትቀበሏት ይገባችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደሆነ ታላቅ ሐሴት ታደርጋላችሁ ፤ እርሷም ቁስለ ነፍሳችሁን ትፈውስላችኋለች፡፡

ሌላ ምሳሌ መስዬ ብነግራችሁ ፦ ሐኪሞች በህሙማን ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻና መርዘኛ ፈሳሽን ማስወገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ ሕሙማኑ ምግበ ሥጋን ከመውሰድ እንዲቆጠቡ ያደርጓቸዋል፡፡ ሕሙማኑ ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከሉ ግን ሐኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት የተፈለገውን ያህል ውጤት አይሰጥም፡፡ እኛም የነፍስንና የሥጋን ቁስል የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚህ በላይ ልንሆን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለሁ፡፡ ድህነትን የምንሻ ከሆነ ልቡናችንን ንጹህና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል ፤ እንዲህ ካልሆነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡ ❞

[ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]


      †                 †                †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖                    🕊                     💖

BY አብሰራ ገብርኤል ለማርያም


Share with your friend now:
tgoop.com/Enatachn_mareyam/16648

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Choose quality over quantity. Remember that one high-quality post is better than five short publications of questionable value. You can invite up to 200 people from your contacts to join your channel as the next step. Select the users you want to add and click “Invite.” You can skip this step altogether. 6How to manage your Telegram channel? With the sharp downturn in the crypto market, yelling has become a coping mechanism for many crypto traders. This screaming therapy became popular after the surge of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May or early June. Here, holders made incoherent groaning sounds in late-night Twitter spaces. They also role-played as urine-loving Goblin creatures. How to Create a Private or Public Channel on Telegram?
from us


Telegram አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
FROM American