tgoop.com/Enatachn_mareyam/16286
Last Update:
- ወደ ቤቱ ተመልሶም የወላጆቹን ላም "እውነትን ተናገር" ብሎ ገስጾታል:: ላሙም ሰይጣን እንዳደረበት በሰው ልሳን ተናግሮ: የቅዱሱን ወላጆች ወግቶ ገድሏቸዋል:: ቅዱስ ፊላታዎስ ግን ላሙን አስገድሎ: ወላጆቹን ከሞት አስነስቶ ከአካባ
ቢው ሰው ጋር በስመ ሥላሴ አስጠምቁዋቸዋል::
- በድንግልና ኑሮም ዘመነ ሰማዕታት ሲጀምር በርጉም ዲዮቅልጥያኖስ እጅ ብዙ ተሰቃይቷል:: በጸሎቱም ጣዖታቱን [እነ አዽሎንን] ከነ አገልጋዮቻቸው ወደ ጥልቁ አስጥሟቸዋል:: እርሱም በዚህች ቀን በሰይፍ ተከልሎ ለክብር በቅቷል:: ለእኛ ለኃጥአን የሚሆን ቃል ኪዳንንም ከጌታው ተቀብሏል::
የቅዱሳን አባቶቻችን አማናዊት ርስት ድንግል ማርያም አትለየን::
🕊
[ † ጥር ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ፊላታዎስ ሰማዕት
፪. አባ ዸላድዮስ ገዳማዊ
፫. ማር ዳንኤል ሶርያዊ
፬. አባ ዮሐንስ መሐሪ [ሊቀ ዻዻሳት]
፭. 11,004 ሰማዕታት [ የቅ/ቂርቆስ ማሕበር ]
፮. 11,503 [ የቅ/ፊላታዎስ ማሕበር ]
፯. አባ ጽሕማ [ ከተስዓቱ ቅዱሳን አንዱ ]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. በዓለ ኪዳና ለድንግል
፪. ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ
፫. ቅዱስ ገብረ ማርያም [ንጉሠ ኢትዮዽያ]
፬. ቅድስት ኤልሳቤጥ
፭. አባ ዳንኤል
፮. አባ አቡናፍር ገዳማዊ
፯. አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
" ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል:: እንደ ሊባኖስ ዝግባም ያድጋል:: በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ ተተክለዋል:: በአምላካችንም አደባባይ ውስጥ ይበቅላሉ:: ያን ጊዜ በለመለመ ሽምግልና ያፈራሉ:: ደስተኞችም ሆነው ይኖራሉ::" [ መዝ.፺፩፥፲፪ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
BY አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
Share with your friend now:
tgoop.com/Enatachn_mareyam/16286