tgoop.com/Enatachn_mareyam/16258
Last Update:
†
[ 🕊 ገ ድ ለ ቅ ዱ ሳ ን 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ቅዱስ መቃርዮስ ካስተማረው ትምህርት ]
[ ክፍል ሰባ ሁለት ]
🕊
[ ለመኖር ምን እንደሚያስፈልግ አስተማረ ! ]
🕊
❝ አባ መቃርዮስ ታላቁ እንዲህ አለ ፦ “ ለአንተ መነቀፍ እንደ መከበር ፣ ድህነት እንደ ሀብት ፣ ገንዘብ መክሰርና ማጣት እንደ ትርፍ ፣ የተጣበቡና የተጨናነቁ ሁኔታዎች ልክ እንደ ሰፊ ጎዳናዎችና ነጻ ቦታዎች ፣ የሥጋ ነገሮችም እንደ እንግዳ ነገሮች ናቸውና ትኖራለህ እንጂ አትሞትም፡፡ ከባልንጀሮችህ ጋር ሕሊናህን ተከተል ፣ ዕብሪተኛ ከሆነ ከማንኛውም ሰው ራቅ፡፡ ❞
[ መዳንን ስለ መሻትና መናፈቅ አስተማረ ]
❝ ታላቁ አባ መቃርዮስ እንዲህ አለ ፦ “ ወንድሞቼ ሆይ ፦ የምትመኟቸውና የምትናፍቋቸው ነገሮች ሁሉ ወደ መዳን የሚመሩ ፣ ነፍሳችሁንም የሚጠብቁና የሚያጸኑ ነገሮች እንዲሆኑ እማልዳችኋለሁ ፣ በዚህም ዛሬ ማድረግ የሚገባንን ነገር ለነገ እንዳንቀጥርና እንዳናሳድር ፣ በእግዚአብሔር መልካም ነገሮችም ሁለት ቀናትን እንግዶች ሆነን እንዳናሳልፍ አደራ እላችኋለሁ፡፡ ❞
🕊
የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡
ይቆየን !
💖 🕊 💖
BY አብሰራ ገብርኤል ለማርያም

Share with your friend now:
tgoop.com/Enatachn_mareyam/16258