tgoop.com/Enatachn_mareyam/16222
Last Update:
🕊 † ኃያል ቴዎድሮስ በናድሌዎስ † 🕊
- በ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን በምሥራቅ [በአንጾኪያ] ያበራ:
- ድንግልናውን በንጹሕ የጠበቀ:
- ቅዱሳን መላእክት የሚያነጋግሩት:
- የአንጾኪያ ሠራዊት ሁሉ አለቃ የነበረ:
- በጦርነት ተሸንፎ የማያውቅ:
- አሕዛብ ስሙን ሲሰሙ የሚንቀጠቀጡለት:
- ከአማልክት ወን ነው እያሉ የሚፈሩት
- እግዚአብሔርን በፍጹም ልቡ የሚያመልክ የወቅቱ ወጣት ክርስቲያን ነው::
- ዲዮቅልጢያኖስ በካደ ጊዜም ጌታ ከባልንጀሮቹ ለውንድዮስና ኒቆሮስ ጋር መላእክት ወደ ሰማይ አሳርገውታል:: በዚያም መድኃኒታችን ክርስቶስን ፊት ለፊት አይቶ: በእሳት ባሕርም ተጠምቁዋል:: በዚህች ቀንም ከቅዱሳን ለውንድዮስና ኒቆሮስ: እንዲሁ ከ፪.፭ ሚሊየን ሰራዊቱ ጋር ለመከራ ተሰጥቷል:: እርሱንም በ፻፶፫ ችንካር ወግተው ገድለውታል::
አምላከ ቅዱሳን ወይነ ቃና ፍቅሩን ያሳድርብን::
ከድንግል እናቱ ምልጃና ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን::
🕊
[ † ጥር ፲፪ [ 12 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት † ]
፩. ቃና ዘገሊላ
፪. ቅዱስ ያዕቆብ እሥራኤል
፫. ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ
፬. ቅዱሳን ለውንድዮስ እና ኒቆሮስ
፭. "፪.፭ ሚሊየን" ሰማዕታት [ የቅዱስ ቴዎድሮስ ማሕበር ]
[ † ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
፪. ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
፫. ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
፬. ቅዱስ ድሜጥሮስ
፭. ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
፮. ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ [ ሰማዕት ]
፯. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፰. አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
" አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ አደነቀ:: ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም:: ውሃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር:: አሳዳሪውም ሙሽራውን ጠርቶ :- 'ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል:: ከሰከሩም በኋላ መናኛውን:: አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል' አለው:: " [ዮሐ.፪፥፱]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
BY አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
Share with your friend now:
tgoop.com/Enatachn_mareyam/16222