COVID_19_IN_ETHIOPIA Telegram 2743
ኢንሹራንስ ኩባንያዎች ለተሽከርካሪዎች ዋስትና የሚያስከፍሉት የዓረቦን መጠን ጨመረ።

የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ከወቅታዊ #የዋጋ_ንረት ጋር በተያያዘ የዋስትና ሽፋን ለሚሰጧቸው ንብረቶች የሚያስከፍሉትን የዓረቦን መጠን እየጨመሩ መሆኑን ሪፖርተር አስነብቧል።

ኩባንያዎቹ በተለይ በሞተር ኢንሹራንስ ዘርፍ ለተሽከርካሪዎች የመድን ሽፋን ይጠይቁ የነበረውን የዓረቦን መጠን ከመቼውም ጊዜ በላይ መጨመራቸው ታውቋል ብሏል ጋዜጣው።

ኩባንያዎቹ ለሚሰጡት የመድን ሽፋን ይጠይቁ ከነበረው ዋጋ እስከ እጥፍ ጭማሪ እየጠየቁ መሆኑን የኩባንያዎቹ ደንበኞች እየገለጹም ነው፡፡

ደንበኞቹ የተሽከርካሪ የመድን ሽፋን ሲያሳድሱ በወቅቱ የተሽከርካሪዎች ዋጋ መሠረት ዓመታዊ የዓረቦን ክፍያቸውን እንዲፈጽሙ እየተደረገ ነው፡፡

የኩባንያዎቹ ደንበኞች እንደሚገልጹት ከሆነ ፣ የተሽከርካሪዎቻቸውን የኢንሹራንስ ሽፋን ለማሳደስ ሲቀርቡ ከዚህ ቀደም ሲከፍሉ ከነበረው የዓረቦን ዋጋ በላይ እየተጠየቁ ነው፡፡ ከኩባንያዎቹ የተገኘው መረጃም ፣ ጭማሪ ሳይሆን ወቅቱን ያገናዘበ ማስተካከያ እየተገረገ ነው፡፡

ይህ የተለመደ አሠራር ሲሆን፣ የአሁኑን የሚለየው ከሌላው ጊዜ በተለየ የተሽከርካሪዎች ዓረቦን ዋጋ ጭማሪ ከፍተኛ መሆኑ ነው፡፡ 

አንዳንድ ደንበኞችም አደጋ ደርሶባቸው የጉዳት ካሳ በሚጠይቁበት ወቅት የኢንሹራንስ ሽፋናቸው በወቅታዊው ተሽከርካሪዎች ዋጋ መሠረት ገቢ እንዲያደርጉ መጠየቃቸውንም እያመለከቱ ነው፡፡

የሪፖርተርን ዘገባ ያንብቡ : telegra.ph/Reporter-08-22



tgoop.com/COVID_19_IN_ETHIOPIA/2743
Create:
Last Update:

ኢንሹራንስ ኩባንያዎች ለተሽከርካሪዎች ዋስትና የሚያስከፍሉት የዓረቦን መጠን ጨመረ።

የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ከወቅታዊ #የዋጋ_ንረት ጋር በተያያዘ የዋስትና ሽፋን ለሚሰጧቸው ንብረቶች የሚያስከፍሉትን የዓረቦን መጠን እየጨመሩ መሆኑን ሪፖርተር አስነብቧል።

ኩባንያዎቹ በተለይ በሞተር ኢንሹራንስ ዘርፍ ለተሽከርካሪዎች የመድን ሽፋን ይጠይቁ የነበረውን የዓረቦን መጠን ከመቼውም ጊዜ በላይ መጨመራቸው ታውቋል ብሏል ጋዜጣው።

ኩባንያዎቹ ለሚሰጡት የመድን ሽፋን ይጠይቁ ከነበረው ዋጋ እስከ እጥፍ ጭማሪ እየጠየቁ መሆኑን የኩባንያዎቹ ደንበኞች እየገለጹም ነው፡፡

ደንበኞቹ የተሽከርካሪ የመድን ሽፋን ሲያሳድሱ በወቅቱ የተሽከርካሪዎች ዋጋ መሠረት ዓመታዊ የዓረቦን ክፍያቸውን እንዲፈጽሙ እየተደረገ ነው፡፡

የኩባንያዎቹ ደንበኞች እንደሚገልጹት ከሆነ ፣ የተሽከርካሪዎቻቸውን የኢንሹራንስ ሽፋን ለማሳደስ ሲቀርቡ ከዚህ ቀደም ሲከፍሉ ከነበረው የዓረቦን ዋጋ በላይ እየተጠየቁ ነው፡፡ ከኩባንያዎቹ የተገኘው መረጃም ፣ ጭማሪ ሳይሆን ወቅቱን ያገናዘበ ማስተካከያ እየተገረገ ነው፡፡

ይህ የተለመደ አሠራር ሲሆን፣ የአሁኑን የሚለየው ከሌላው ጊዜ በተለየ የተሽከርካሪዎች ዓረቦን ዋጋ ጭማሪ ከፍተኛ መሆኑ ነው፡፡ 

አንዳንድ ደንበኞችም አደጋ ደርሶባቸው የጉዳት ካሳ በሚጠይቁበት ወቅት የኢንሹራንስ ሽፋናቸው በወቅታዊው ተሽከርካሪዎች ዋጋ መሠረት ገቢ እንዲያደርጉ መጠየቃቸውንም እያመለከቱ ነው፡፡

የሪፖርተርን ዘገባ ያንብቡ : telegra.ph/Reporter-08-22

BY ዜና





Share with your friend now:
tgoop.com/COVID_19_IN_ETHIOPIA/2743

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

ZDNET RECOMMENDS The imprisonment came as Telegram said it was "surprised" by claims that privacy commissioner Ada Chung Lai-ling is seeking to block the messaging app due to doxxing content targeting police and politicians. The visual aspect of channels is very critical. In fact, design is the first thing that a potential subscriber pays attention to, even though unconsciously. 4How to customize a Telegram channel? On Tuesday, some local media outlets included Sing Tao Daily cited sources as saying the Hong Kong government was considering restricting access to Telegram. Privacy Commissioner for Personal Data Ada Chung told to the Legislative Council on Monday that government officials, police and lawmakers remain the targets of “doxxing” despite a privacy law amendment last year that criminalised the malicious disclosure of personal information.
from us


Telegram ዜና
FROM American