Telegram Web
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በጣም የምወደው መልእክት.. ከዚህ ቀደምም ለቅቄው አውቃለሁ..

በማገልገል የምንታወቅ ወንድሞች.. በዓለም ያሉ እህቶቻችን ወደ እኛ ሲመጡ ከእኛ መንፈሳዊነትን ካጡብንና ጭራሽ ዓለም ላይ ያለውን ከሰጠናቸው በአካል ከእኛው ጋር ሆነው ውስጣቸው ግን ወደ ዓለም ይመለሳል.. ይሄ ስውር ጦርነት ኢየሱስ ላይ መክፈት ስለሆነ መጠንቀቅ መልካም ነው..
776👍95🥰23👏22🤣4😢1
ዛሬ ቅዳሴ ላይ ከተነበበው የቅዱስ ወንጌል ክፍል:

የሉቃስ ወንጌል 10
21፤ በዚያን ሰዓት ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ሐሤት አደረገና፦ የሰማይና የምድር ጌታ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።

የእግዚአብሔር መገለጥ የምትገኘው በየዋህነትና በእምነት እንጂ በዓለማዊ ጥበብና እንደ ሰው በሆነ ፍልስፍና አይደለም.. ስለዚህም ከእግዚአብሔር ለመጠቀም የሚሻ ሰው ራሱን በእግዚአብሔር ፊት እንደ ሕጻነት ሊያደርግ ይገባል.. የዋህዎች ከተንኮል የራቅን በንጹህ ልብ የምንቀርብና ጌታ የሚለንን አሜን ብለን የምንቀበል ልንሆን ይገባል።

መልካም የጌታ ቀን

@Apostolic_Answers
1.11K🙏124👏21👍14🔥13🥰13
ወንድሞች ኧረ በእህቶች በጣም እየተበለጥን ነው መሰለኝ🙄🙄 አንዷ ገና ጩጬ የሆነች እህት(in her early 20s) ምን ጠቅሳ ብታወራ..?? ፊሎካሊያ(philokalia).. በእኛ ዜና አበው እንደሚባለው በጣም በርካታ የተለያዩ አጫጭር የቅዱሳን አባቶች ሕይወታዊ ምክር እና ንግግሮችን የያዘ መጽሐፍ ነው.. ከምነግራችሁ በላይ ጠቃሚ ነው..

ወንድሞች ኧረ አንሰማቸው አይበልጡንም ሎል.. ዜና አበውን እና መጽሐፈ ሲራክን ለሕይወታችን በጣም ልናነባቸው ይገባል..

እዚሁ አብረን ማንበብ እንጀምር እንዴ በየቀኑ..??
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍1.29K331👏36🔥19🤣17
አንዴ የዳነ ሰው ድኅነቱን አያጣውምን..??

ካልቪኒዝም vs ሉተራኒዝም

ካልቪኒስት ፕሮቴስታንቶች በ PS ትምህርታቸው መሠረት እግዚአብሔር አስቀድሞ የመረጣቸውና ከዚያም ያዳናቸው ሰዎች ሊጠፉ አይችሉም።

ሉተራን ፕሮቴስታንቶችም እግዚአብሔር አስቀድሞ የመረጣቸውና ያዳናቸው ሰዎች ኩነኔ የለባቸውም ያው ድካም ውስጥ ቢገቡም አይቆጠርባቸውም ስለተመረጡ ይሉናል😁😁 (ትንሽ ለየት የሚለው የእነዚ ሳይመረጡ ሾልከው የሚድኑ ይኖራሉ እና እነርሱ ሊጠፉ ይችላሉ ማለታቸው ነው ሎል)

ሉተራኒዝም 🤝 ካልቪኒዝም [የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ ሎል]

ከመጽሐፍ ቅዱሱና ከታሪካዊው እውነት በሚሊየን ማይል ርቀት ላይ ናቸው😁😁
338🤣122👍37🙈15🔥6🤔2
ከላይ ካለው ጽሑፍ ጋር በተያያዘ.. እንደው አክሊል ስለ መምረጥ መመረጥ ጽፈሃል እና እግዚአብሔር ሲመርጣቸው በምን መስፈርት ነው..?? ያሉ ሰዎችን አየሁ.. ዌል ያለምንም መሥፈርት ሰዎችን ለማዳን ይመርጣል.. ያው ሰዎቹ ሳይፈልጉ ሳያምኑ ሳይፈቅዱ.. unconditional election ይሉታል ይህንን..

ታድያ ነጻ ፈቃድስ..?? ዌል ሉተርና ካልቪን በውድቀት ውስጥ ያለ ሰው ነጻ ፈቃድ የለውም፣ እግዚአብሔርን መፈለግም ሆነ ማመንም አይችልም ብለው ነው የሚያምኑት.. ስለዚህ ያለፍላጎታቸው እግዚአብሔር በቃ ዝም ብሎ በራሱ ፈቃድ ይመርጥና ያድናቸዋል ነው የሚሉት..

ላለፉት ጥቂት ዓመታት ጴንጤ ላይ ሄደንበታል እና አሁን ላይ ብዙ ልጆችም እየሄዱበት ነው.. በዚህ ዓመት ደግሞ ፕሮቴስታንቲዝም ላይ ከሰራሁ ሉተራኒዝም እና ካልቪኒዝም ላይ ብቻ ይሆናል..
👏304132👍44😁3😱2
ሉተራኖች ተቀበሉ.. ከእምነት መግለጫችሁ አንድ ነገር ላስቀምጥና እሱ ላይ ተመስርቼ ጥቂት አሳቦችን ላስቀምጥ፡

"በመጀመሪያ ወላጆቻችን(በአዳም እና ሔዋን) ውድቀት ምክንያት ሰው ክፉኛ በመበከሉ ከመለወጣችንና ከነፍሳችን መዳን ጋር በተያያዘ ለመለኮታዊው ነገር በተፈጥሮው እውር ነው፤ ይህም የእግዚአብሔር ቃል በሚሰበክበት ጊዜ አይረዳውም(አይገባውም) ሊረዳውም አይችልም፤ ይልቁንም እንደ ሞኝነት ይቆጥረዋል። በራሱ ወደ እግዚአብሔር ሊቀርብም አይችልም፤ ይልቁንም በሚሰበከው እና በሚሰማው ቃል በኩል በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከንጹሕ ጸጋ የተነሣ ያለ ሰውዬው ምንም ዓይነት የፈቃድ ትብብር እስኪለወጥ፣ አማኝ እስኪሆን(እምነት እስኪሰጠው)፣ ዳግም እስኪወለድና እስኪታደስ ድረስ የእግዚአብሔር ጠላት እንደሆነ ይቆያል።"
[Formula of concord - Solid declaration, II:5]

1. በውድቀት ውስጥ ያለ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል መቀበል አይችልም ይልቁንም እንደ ሞኝነት ነው የሚያየው ለእግዚአብሔርም ጠላት ነው

2. ይህንን ሰው እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በሚሰበከውና በሚሰማው የእግዚአብሔር ቃል በኩል ሰውዬው ምንም እንኳን የሚሰማውን ባይቀበልም ግን ደግሞ ያለ ሰውዬው ምንም ዓይነት የፈቃድ ትብብር ዳግም ይወልደዋል ያድሰዋል ይለውጠዋል እምነትን ይሰጠዋል

የኔ reflection

3. ሰውዬው የእግዚአብሔርን ነገር እምቢ በሚልበት ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ይህ ቀዳሚ ጸጋ(prevenient grace) ሲሰጠው መቃወም ይችል ነበር ወይ? አዎ መቃወም ይችላል የምትሉ ከሆነ በዛ በሞት ውስጥ ሆኖ የመለኮትን ነገር የማይቃወም ስለማይኖር ይህንን ጸጋ ማንም ሳያገኝ ይቀራል ስለዚህም አንድም ሰው አይድንም ወደ ሚለው ያመራል። መቃወም ይችላል የምትሉት ከዚህ ከቀዳሚው ጸጋ በኋላ ከሆነ ይህ የመጀሪያው ጸጋ(grace) እንደ ካልቪኒስቶቹ irresistible grace ነው ያስብላል.. ስለዚህም deep down ብዙ ነገራችሁ ካልቪኒስት ነው።

4. ሲቀጥል እግዚአብሔር ቃሉን በሚሰሙት ሰዎች ላይ ይህንን የመፈወስ ሥራ ሲሰራ ከሰውዬው ምንም አይቶ ካልሆነ አንዳንዶችን ሲያድን ሌሎቹን ራሱ ነው የተዋቸውም ያስብላል። ምክንያቱም የተፈወሱትም የተፈወሱት ከእነርሱ ምንም ታይቶ አይደለምና።

5. የመጨረሻ ለመጨመር ያህል ዳግም ልደታችሁም በእምነት ላይ የሚመሠረት ሳይሆን በእግዚአብሔር ፈቃድ ላይ ብቻ(በመሣሪያዎቹ በኩል) የሚመሠረት ነው። ስለዚህም regeneration precedes faith(ዳግም ልደት እምነትን ይቀድማል) የሚለው የካልቪኒስቶች አገላለጽ በ temporal order ሳይሆን በ logical order that means putting regeneration as a cause of faith ይህ ነገር የእናንተም ትምህርት ይሆናል ማለት ነው።

@Apostolic_Answers
318👏28👍9🔥9🙏5
እስከ ትናንት ድረስማ ያው በጉራጌ ጓደኞች ተከብቤ ነበር እኮ..

ዛሬ የበአላቹ ቀን ያበደ ክትፎዋችሁን ስትይዙ ካዳችሁኝ እንጂ😁😁

እንኳን አደረሳችሁ ለማንኛውም
😁774277🤣104👍14🔥13🤩2
ጌታ ቢፈቅድና ቢረዳን እኛም ብንኖር.. ከነገ ጀምሮ መጽሐፈ ሲራክን ማንበብ እንጀምራለን.. ሁላችሁም መጽሐፍ ቅዱሳችሁን የ2000ውን እትም አዘጋጁ.. የሌላችሁ ግን በየቀኑ የምናነበውን ክፍል ወይ ፎቶውን እንለጥፍላችኋለን..

እግዚአብሔር መልካሙን የሕይወት ጉዞ ይግለጥልን.. መንፈስ ቅዱስ በዚህ መጽሐፍ በኩል ይመርምረን ይምከረን ይገስጸንም
1.44K🙏185👍72🔥25😁15🥰8🤩5
እንኳን አደረሳችሁ.. ያው ከመሸ😁😁

https://vm.tiktok.com/ZMAPXeGF3/
392🔥21👍8👏6🙏5🤔1
ዮው ጋይስ ባለፈው ያልኳችህ "ዜና አበው" የተወሰኑትን ምክሮች ዲያቆን ያረጋል ተርጉሟቸዋል እና በቃ ከነገ ጀምሮ እሱን ይሆናል ጠዋት ጠዋት የምናነበው.. መጽሐፈ ሲራክን ቀጣይ..
422👍31🔥15👏13😁3
ቅዱስ አባ እንጦስ በገዳም ውስጥ በሚኖርበት ጊዜ ብዛት ባላቸው የኃጢአት አሳቦች ይጠቃ ነበር። ስለሆነም በአንድ ወቅት ጥያቄውን ለእግዚአብሔር እንዲህ በማለት ያቀርባል፦

"ጌታዬ ሆይ! እኔ ልድን እወዳለሁ፤ ይሁን እንጂ እነዚህ ክፉ አሳቦች ብቻዬን ሊተዉኝ አልቻሉም። በዚህ መከራ ውስጥ ስሆን ምን ባደርግ ይሻለኛል?"

ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ተነሥቶ ወደ ውጪ ሊወጣ ሲል አንድ እርሱን የሚመስል ሰው ቁጭ ብሎ ሥጋጃ(እንደ ምንጣፍ ያለ ነገር?) ሲሰራ ይመለከታል። ያ ሰው ጥቂት ከሠራ በኋላ ሥራውን አቋርጦ ይነሣና መጸለይ ይጀምራል። ጸሎቱን እንደጨረሰም ተመልሶ ሰሌን መስፋቱን ይቀጥላል። እንደገና ተነሥቶ ደግሞ ይጸልያል። በዚያን ወቅት ይህንን ሁሉ ያደረገው የእግዚአብሔር መልአክ ሲሆን ይህንንም ያደረገው አባ እንጦንስን ሊያርመውና ሊያስተምረው ፈልጎ ነው።

በመጨረሻም መልአኩ "እንደዚህ ካደረግህ ትድናለህ" ይለዋል። አባ እንጦንስም እነዚህን ቃላት ሲሰማ እጅግ ከመደሰቱ በላይ ድፍረትንም ተጎናጸፈ። ከዚህ በኋላ አድርግ የተባለውን ስላደረገ ዳነ።
———————————-

እንጦንስ በኃጢአት አሳብ አብዝቶ ይፈተን የነበረው ከጸሎት ሰዓቱ በኋላ እንዲሁ ቁጭ ይል ስለነበር ነው። እኛም በኃጢአት አብዝተን እንዳንፈተንና እንዳንወድቅ ሥራ ፈተን አንቀመጥ.. ምንም ቢሆን ቤት ውስጥም ውጪም በሆነ ሥራ ራሳችንን ቢዚ እናድርግ

መልካም ውሎ
1.45K🙏168👍34👏19🔥17😢6😁3🤣1
ስለ እግዚአብሔር ፍርድ አባ እንጦስ ሲያሰላስል ከቆየ በኋላ አምላኩን እንዲህ በማለት መጠየቅ ይጀምራል፦

"ጌታዬ ሆይ! አንዳንድ ሰዎች ገና ልጅ እንዳሉ የሚሞቱትና ሌሎች ደግሞ ከመጠን በላይ እስኪያረጁ ድረስ የሚቆዩት ለምንድን ነው? አንዱ ደሃ ሌላ ደግሞ ባለ ጠጋ የሚሆነውስ ስለ ምን ነው? ኃጢአተኞች የሚበለጽጉበትና እውነተኞች የሚያጡበት ምክንያትስ ምንድን ነው?"

ከዚህ በኋላ አንድ ድምጽ "እንጦንስ ሆይ! ትኩረትህን ወደ ራስህ አድርግ! እነዚህ ሁሉ ሊሆኑ የቻሉት እንደ እግዚአብሔር የፍርድ አሠራር ነው። ስለ እነርሱ ታውቅ ዘንድ ለአንተ የተሠጠህ ነገር የለም!" በማለት ሲናገረው አደመጠ።
——————————--

አንዳንዴ በሕይወታችን ውስጥ የማንረዳቸው የእግዚአብሔር አሠራሮች ይኖራሉ.. ይህም ከእኛ አቅም አንጻር ነው.. ልክ ለአንድ ሕጻን ልጅ ሁሉም ነገር እንደማይነገረውና ሲያድግ እንደሚደርስበት ሁሉ እግዚአብሔር አባታችንም በብዙ ነገር ሕጻናት ለምንሆን ለእኛ ልጆቹ በትንሳኤ ሰዓት ወይም ወደ እርሱ እስክንሄድ ድረስ ብዙ ነገሮችን ከማወቅ ሊሸፍን ይችላል ነው። ስለዚህም ለድኅነት የተሰጠንና የራሳችን ጉዳይ ላይ እናተኩር በቀረው ግን በእግዚአብሔር እንመን..

መልካም የጌታ ቀን
1.02K🙏135👍21🔥15🥰3👏3🤣3
ነጻ ፈቃድ ባይኖረንስ ግን..??

"አብ ከሰባው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም።" [ዮሐ 6 44]

ይህንን ቃል ይዘው ፕሮቴስታንቶች[ሉተራኖችና ካልቪኒስቶች] ሰው ሙሉ በሙሉ በውድቀት ውስጥ ስለገባ ነጻ ፈቃዱን እንዳጣውና ስለዚህም በፈቃዱ ወደ ጌታ መምጣት ስለማይችል አብ በፈቃዱ በምርጫው ይስበዋል ይላሉ.. የት ላይ ብለዋል..?? ለምሳሌ በእምነት መግለጫ ደረጃ ብቻ፡ [formula of concord – solid declaration, concerning free will, 26; Belgic confession: article 14; Westminster confession, chap 9:3]

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ግን ይህንን የመጽሐፍ ክፍል ሲተረጉም እንዲህ ይላል፡

-ማኒኪያኖች(የማኒ ተከታይ ኖስቲኮች - መነናውያን) ከዚህ ቃል(ከዮሐ 6፡ 44) በመነሣት “በራሳችችን ሥልጣን የሚሆን ምንም ነገር የለም” ይላሉ፤ ነገር ግን ገለጻው የሚያሳያው የፈቃዳችን መሪ(አለቃ) ራሳችን እንደሆንን ነው። አንድ ሰው እንዲህ ሊል ይችላል፡ “ሰው ወደ እርሱ መምጣት የሚችል ከሆነ ታድያ መሳቡ ለምን አስፈለገው".. ነገር ግን ቃላቱ የእኛን ነጻ ፈቃድ የሚያስወግዱ አይደሉም፤ ይልቁንም ድጋፍን ወይም እርዳትን እንደምንፈልግ የሚያሳይ ብቻ ነው። [Homilies on John, hom. XLVI]

ከዚህ ምን እንረዳለን..?? ፕሮቴስታንቲዝም በተለይ "ጸጋ ብቻ" በሚለው ትምህርቱ የ16ኛው ክ/ዘመን [ግ]ኖስቲሲዝም እንደሆነ ነው..

@apostolic_Answers
399👍47🔥16🤣8😱4🙏4👏2
ከፕሮቴስታንት መሥራች ማርቲን ሉተር በጣም የሚደብረኝ ነገሩ እብሪተኝነቱ ነው..

እሱን በሚቃወም መልኩ አባቶች እንደማስረጃ ሲጠቀሱበት አባቶችን የሚያጣጥልበት መንገድ እንዴት እንደሚደብር.. ከመንፈስ ቅዱስ እንዳልሆነ በጣም ግልጽ የሚያደርገው አንዱ ከአባቶች ትምህርት ጋር ሲጋጭ የሚያሳየው ካራክተር ነው..

በዚሁ በነጻ ፈቃድ ጉዳይ ላይ ለኤራስመስ መልስ ሲመልስ ኤራስመስን በኃይለ ቃል አጠፋፋትና አባቶችን ደግሞ ጭራሽ ቅዱስ ይሁኑ አይሁኑም አይታወቅም እኛ ካለን ፍቅር አንጻር እንደዛ እንላለን እንጂ በእምነት ደረጃ አናውቅም.. ይልና ጄሮምን ተመልከት እያለ ከርእሱ ጋር ማይገናኝ ነገር እያነሳ መሳደብ ይጀምራል..

ሉተር የተሻለ ነገር ቢኖረውም.. ምንም እንኳን ደጋሚ ቢሆንም(ያው ጸሎተ ሃይማኖትን እና አቡነ ዘበሰማያትን ድገሙ(repeat) ስለሚል😁😁) በዛው ልክ ግን ከነ ትእቢቱ ከክርስትና ርቆ የወደቀበት ነገርም ብዙ ነው

@Apostolic_Answers
435👍59😁17🤣13🙈12🔥9
ያው የግል የቴሌግራም አካውንት በመደለት ነው የምታወቀው😁😁 እና በውስጥ ምናልባት አውርታችሁኝ ያልመለስኩላችሁ ልጆች ምናምን በጣም ይቅርታ አድርጉልኝ ያው ሰው በጣም በዝቶብኝ ስለነበር ነው ለተለያዩ ጉዳዮች.. አሁን ደግሞ ያው አካውንቴን ላጠፋው ነውና ያው ይቅርታ ግሩፑ ላይ ግን ስላለሁ እየመጣችሁ ጠይቁ በቻልኩት መልሳለሁ ሌሎችም ልጆች ይመልሳሉ
319😢49👍29🤣25😁7😱1
አባ ፓመቦ እንጦስን እንዲህ ሲል ይጠይቃቸዋል.. “ምን ማድረግ ይገባኛል?”

አባ እንጦንስም ሲመልስ:- “በራስህ ጽድቅ አትታመን፣ ባለፈው አትጨነቅ፣ አንደበትህንና ሆድህን ግዛ”
———————————

ይሄ ለብዙዎቻችን ትምህርት ነው.. በተለይ አንደበትን መግዛት.. በውሎዋችን ምናምን በጣም ከምንቀርባቸው ወዳጆቻችን ጋር ቀላል ስለሚሆንብን በጣም ያልተገባ ነገርን እናወራለን.. ይሄ ደግሞ ቀስ እያለ ልቅነትና ግድ የለሽነትን ያመጣል.. ስለዚህ በተቻለ አቅም ቀስ በቀስ አንደበታችንም ቁጥብ መሆን አለበት..

መዝሙረኛውም “አቤቱ፥ ለአፌ ጠባቂ አኑር፥ የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ። “[መዝ 141: 3] እንደሚለው ነው..

መታመናችንም ሁሉ በእግዚአብሔር ይሁን ረዳታችን እርሱ ነውና.. ያለ እርሱም ምንም ልናደርግ አንችልምና.. በራሳችን ጽድቅ መታመን የጀመርን ቀን እግዚአብሔር ሊተወን ይችላልና..

መልካም ውሎ

@Apostolic_Answers
855🙏83👍37🥰24🔥5🤣3
ኧረ የሆኑ ልጆች በአብ እና በወልድ መካከል አስገኚና ተገኚ የለም እያሉ ኡኡ ሲሉ ሰማሁ😁😁

“ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ እውነተኛ አምላክ” የሚለውን የኒቀ‍ያ እምነት መግለጫን(ጸሎተ ሃይማኖትን) ሳያምኑበት ነው እንዴ ቆይ ሚጸልዩት ሎል.. በአስገኚና በተገኚ መካከል ምንም ዓይነት መቀዳደም እና የባህሪ ልዩነት እንዲሁም በውልደት እንጂ በፍጥረት ያልሆነ እንላለን እንጂ ጭራሽ ወልድ ከአብ አልተገኘም የሚል ምንፍቅና ላይም ደርሰናል..?? በጣም ብዙ አባቶች እኮ ናቸው ይሄንን ያስተማሩት ደግሞ😁😁

ለቤተ ክርስቲያን የተቆረቆረ እንደሚመስል ለቤተ ክርስቲያናችን አደገኛ ሰው የለም.. ለማንኛውም እንደው እንደተማረ ሰው ማስመሰሉን ትተን ብናነብ.. ያው ቪዲዮውን አላጋራኋችሁም ብዙም ስለማይጠቅም😁😁
493👍65🤔14🤣12😢5🔥4
አንዱ እስላም መምህር ምን ቢል..?? “መምህር በረከትን ለውይይት መርጠናል..”

በጌታ ስም ጀለስ በአንድ ስክሪቢቶ 4 ትንንሽ መጽሐፍት ሲጽፍ ጀግና የሆነ መሰለው እንዴ😁😁 (ስክሪቢቶው ገና ሌላ 2 ያስጽፈኛል እያለ ነው ኧረ እንደውም ሎል) በጌታ ከእንደነዚህ ዓይነት ignorant ልጆች ጋር ሲጀመር እኔ ራሱ ከዚህ በፊት እንወያይ በማለቴ ይሄንን ልጅ እንዴት እንደማፍር.. ፊት አትስጧቸው የምር.. ቤታችሁን እየከፈታችሁ ብቻ መስራት ያለባችሁን ሥሩ.. ከፈለጉ መጥተው ገስት ላይ ጥያቄ ይጠይቋችሁ..
🤣343102👍67😁20🔥4🙈3😢1
አባ እንጦንስ በአንድ ወቅት እንዲህ ሲል ተናግሯል:

በአንድ ወቅት ጠላት በዓለሙ ሁሉ ላይ ያጠመዳቸውን ወጥመዶች ተመለከትሁና “ከእነዚህ ማን ሊያመልጥ ይችላል?” በማለት በሃዘን ውስጥ ሆኜ ስጠይቅ: “ትሁት ሰው ያመልጣል” የሚል ድምጽ አደመጥሁ..
——————————————

ትህትና በክርስትና ውስጥ ትልቁን ቦታ ይይዛል ከፍቅር ጋር.. ጌታ ኢየሱስ ራሱ ከእኔ ተማሩ በማለት “እኔ የዋሕ በልቤም ትሑት ነኝ” ብሏል.. አምላክ ሲሆን ሰው በመሆኑም ትልቁን ትህትና አሳይቶናል.. ስለዚህም ጌታ በልቡ ትሑት ከሆነ የክርስቶስ ልብ ያለው እርሱ ትሑት ነው.. ያለ ትሕትና የክርስቶስ ልብ አይኖረንም.. የክርስቶስ ልብ ካለን ግን ወደ ሰማይ ከፍ ብለናል.. ስለዚህ አውግስቲንም : “ትእቢት መላእክትን ከሰማይ ወደ ምድር ጣለ፤ ትሕትና ደግሞ ሰዎችን ከምድር ወደ ሰማይ ያወጣል” ይላል.. በአንደበት ያልሆነ በልብ የሆነ ትሕትናን ጌታ ይስጠን(በነገራችን ላይ ከልብ ትሑት ለመሆን እርዳኝ ተብሎ ይጸለያል)

መልካም ውሎ

@Apostolic_Answers
841🙏98👍29🔥12🥰8👏8😱2
አንድ የተወደዱ መምህር "ጌታችን የተሰቀለው እንጨት ላይ ነው እንጨት ባይኖር ድኅነት የለም" እና መሰል ነገርም የተናገሩበትን ቪዲዮ ይዘው አንዳንዶች ሲተቹ አየሁ..

ለምን ተቻችሁ? ልል አይደለም.. መተቸት ያለበት ሁሉ በእውቀትና በፍቅር ይሁን እንጂ ይተቻል.. ግን እንደ አንድ ክርስቲያን ይህንን ንግግራቸውን ያው ጌታ እኛን ለማዳን እነዚህን ነገሮች ሁሉ ተጠቅሟቸዋል ለማለት ነው ብዬ ነው የምረዳው እንጂ መቼስ ጌታ በፈቃዱ መርጦ የተጠቀመውን ነገር ለምሳሌ እርሳቸው እንዳሉት እንጨቱን አይተን እንጨት ባይኖር ጭራሽ ድኅነት ሊኖር አይችልም ወደሚል ድምዳሜ አያደርስም። በቃ እግዚአብሔር ባወቀ እንጨትን ተጠቅሟል ከዛ ውጪ ለጥጠነው እንጨት ባይኖር መዳን የለም ስንዴ ባይኖር መዳን የለም ውኃ ባይኖር መዳን የለም ብለን መደምደም የምንችል አይመስለኝም ይሄ የእግዚአብሔርንም ኃይል በእነዚህ ነገሮች ላይ ወደ መገደቡ ሊወስድ ስለሚችል ማለት ነው።

መምህራችን የተናገሩት ግን እኔ እንደተረዳሁት እንደው በቃ እግዚአብሔር እነዚህን ነገሮች ሁሉ ተጠቅሞባቸዋል ለማለት ያህል ብቻ ነው
454👍61👏21🤣2
2025/10/01 22:16:39
Back to Top
HTML Embed Code: