tgoop.com/Ametemarym/3645
Last Update:
✥የዓብይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት✥
✥ቅድስት✥
በመባል የታወቃል ።
በዚህ ቀን እግዚያአብሔር አምላክ ቅዱስ ነውና እኛም ቅዱስ እንድንሆን ይፈልጋል ሁሉም የተቀደሰ ህይወት እንዲኖረው ይሻል። እኛም እርሱን መስለን በሮሜ 8÷28 የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቅድሞ ወሰነ ይላልና። እግዚያአብሔር አምላክ በቅድስና እንዲመራን የርሱ መልካም ፍቃድ ይህውንልን።
ሌላው ግን በዚህ ጊዜ ቅድስት ተብሎ በሚታወቀው ሳምንት ውስጥ የምናስበው ምንድነው? ስንል ሰንበትን ነው። እግዚያአብሔር አምላክ ሰንበትን እንደቀደሳት ሰንበትን ቀድሶ ለኛ ቅድስት አድርጎ እንደሰጠን የሚያሳይ ነው።
ሰንበት ስናከብር ሁለት ሰንበት እናከብራለን።
በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን።
1ኛ ቀዳሚ ሰንበት
2ኛ ሰንበተ ክርስቲያን
የክርስቲያን ሰንበት ቀዳሚ ሰንበት የተባለቺው #ቅዳሜ ነው። ለምሳሌ ውዳሴ ማርያም በንደግምበት ሰዓት ውዳሴሃ ለእግዝተነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ ዘይትነበብ በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት ። ይላል።
የቀደመች ሰንበት የአይውድ ሰንበት ወይም በብሉይ ዘመን የምትከበር ሰንበት ሁሉም ሰው ሊያከብራት የምትገባ ሰንበት። ዘፍጥረት 2÷3 እግዚያአብሔር አምላክ ሁሉን በስድስት ቀን ከፈጠረ በዋላ በሰባተኛው ቀን አረፈ የሰባተኛው ቀንም ቀደሰው።
አከበረው ሰንበት አለው። ዘጸአት 20 ላይ ስንመለከት ከአስርቱ ትዛዛት አንዱ ሰንበቴን አክብር ነው። ወይም ሰንበትን አክብር ነው።
እዚህ ሰንበት ቅዳሜ ላይ ጌታ ከፈጠረው ፍጥረት ሁሉ አረፈ ። ለምን አረፈ?
ደክሞት በፍፁም አይስማማውም።
ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባው።
ከምንሰራው ስራ አርፈን እግዚያአብሔርን እናመሰግነው ዘንድ ነው።
ስለዚህ ቅዳሜ የስጋ እረፍት ነው።
2ኛ ሰንበት እውድ ነው።
እውድን ሰንበት እንደውም የቀኖች ሁሉ ንግስት ነው የሚላት አትናቲዮስ ሲጠራት ። የእለታት ሁሉ ንግስት አባይ ታላቅ እለት ይላታል።
ለምን ?
በዚህ ቀን ደሞ ነብሳችን አርፋለች።
እንዴት ? አለምን በስድስተኛው ቀን ፈጥሮ በሰባተኛው ቀን ያረፈው የሁሉ ፈጣሪ እግዚያአብሔር አለምን ለማዳን በጀመሪያውስንመለከት ትምህርት ዘወረደ እንደተመለከትነው ወርዶ ወደዚህ መቶ ነብሳችን በህለተ ሰንበት እውድ አሳረፋት። ማቴ 28÷1 ዮሐ 20÷1 በመቃብሩ ስፍራ በህለተ ሰንበት ወይም ደግሞ የሰንበቱ መጨረሻ በመጀመሪያው የሰንበት ቀንእነሆ ወደ መቃብሩ ስፍራ ኤዶ መቃብሩ ግን ባዶ ነበር። ነብሳችን ያረፈችበት ሰንበት እለተ ሰንበት እውድ ነበር ። እውድ ደግሞ ሰንበት ተብሎ ይጠራል።
1 ቀዳሚት ሰንበት ።
2 እውድ ሰንበት ።
ይኤንን እነሆ ሰንበታቴን አክብሩ ብሎ እንደተናገረ እነዚህን እናከብራለን ።
ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በፍጥሞ ደሴት ሳለው ይላል ። ራይ 1÷10 ላይ በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርኹ አለ። የጌታ ቀን የሚላት እውድነው። ሐዋሪያት የጌታ ቀን ብለው ይጠርዋታል ።
ቅዳሜ ሥጋችን ያረፈበት የሚያርፍበት
እውድ ደግሞ ነፍሳችን የሚያርፍበት ልዩ ቀን ነው። ቅድስት ሲል እግዚያአብሔር ቅዳሜን እግዚያአብሔር እውድን ለውላችን ቅድሶ ሰጠን ።
በዚህ ቀን አርፈን የታመመን እንድንጠይቅ ድውያን እድንጠይቅ እግዚያአብሔር ይፈልጋል።
ለስጋ ብቻ መሮጥ አይደለም ወገኖቼ ለዓለማዊ ነገር ብቻ መክነፍ አይደለም።
እግዚያአብሔር ዛሬ ይጠይቀናል ።
በዚህ ቀን ችግረኞችን እንድንጠይቅ እግዚያአብሔር ይሻል።
✥
የህለተ ሰንበ በረከት እረድኤት ከኛጋር ይኑር።
ሼር በማድረግ ቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ።
👇👇👇👇👇👇👇
╔═✟✞════🇨🇬 ════✟✞═╗
@dmse_tewado @orthodoxswi_eywet
╚═✟✞════🇨🇬 ════✟✞═╝
BY የማርያም አገልጋይ
Share with your friend now:
tgoop.com/Ametemarym/3645