🕊
[ † እንኳን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ የተድላና የደስታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
† በዚሕች ቀን ለ፵ [ 40 ] ዓመታት በመላው ዓለም የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናት የተከፈቱበት ቀን ይታሠባል:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :- ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ልቡና ታስባ : በዓለመ መላእክት ከታየች በኋላ :-
- አበው ተስፋ ሲያደርጓት
- ነቢያት ትንቢት ሲናገሩላት
- ሱባኤ ሲቆጥሩላት
- ምሳሌም ሲመስሉላት ኑረዋል::
† ዘመኑ በደረሰ ጊዜ በአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ :-
- በመጸነሱ ተጸንሳ
- በመወለዱ ተወልዳ
- በጥበብና በሞገስ አብራው አድጋ
- በጥምቀቱ ተጠምቃ
- በትምሕርቱ ጸንታ
- በደሙ ተቀድሳ
- በትንሣኤው ከብራ
- በዕርገቱ ሰማያዊነቷን አጽንታ
- በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስ ወርዶላት በይፋ ለልጆቿ ተሰጥታለች::
† አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት በመላው ዓለም ዞረው በብዙ ድካም የሠሯት ቤተ ክርስቲያን ለ፪፻ [200] ዓመታት እጅግ የበዙ መከራዋችን አሳልፋለች:: በ፪፻፷፭ [265] ዓ/ም የመጣባት መከራ ግን በዓለም ታሪክ እስካሁን አልታየም:: የወቅቱ ኃያላን ነገሥታት [ዲዮቅልጢያኖስና መክስምያኖስ] ዓለምን ለ፪ [2] ተካፍለው ክርስቲያኖችን የማጥፋት ዘመቻ ጀመሩ::
በመጀመሪያም በዓለም ያሉ ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት እንዲቃጠሉ ካልሆነም እንዲዘጉ : በፈንታቸው ደግሞ አዽሎን: አርዳሚስ የተባሉ ጣዖቶች እንዲተኩ ትዕዛዝ ተሰጠ:: ለ፵ [40] ዓመታት ክርስቲያን ስለሆኑ ብቻ ሚሊየኖች ተገደሉ: ታሰሩ: ተሰቃዩ: ተሰደዱ:: መጻሕፍት ተቃጠሉ: አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ወደሙ::
በአባቶቻችንና እናቶቻችን ላይ ልንናገረው ከምንችለው በላይ ጭንቅና መከራ ደረሰ:: ነገር ግን ቅዱሳኑ ያን ሁሉ ችለው ጸኑ:: ፵፯ [47] ሚሊየን የሚያሕሉትን ደግሞ ሰይፍና እሳት በላቸው:: በዛ ዘመን አንድ ቤተ ክርስቲያን ለማግኘት ከአሕጉር አሕጉር መሔድን ይጠይቅ ነበር::
ከዚሕ ሁሉ በኋላ ግን እግዚአብሔር "ግፍ ይበቃል" ሲል በ፫፻፭ [305] ዓ/ም ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ነገሠ:: መክስምያኖስን በጦርነት ሲማርከው አውሬው ዲዮቅልጢያኖስ ግን አብዶ ሞተ:: ይህ ከተደረገ ከዓመታት በኋላ [በ፫፻፲፫ [313] ዓ/ም] ታላቁ ቆስጠንጢኖስ የዓለም መሪዎችን በዚሕች ቀን ጠርቶ አዋጁን በአዋጅ ሻረው:: "ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ:: በፈንታው ደግሞ ሁሉም ጣዖት ቤቶች ይዘጉ" አለ::
በሺሕ የሚቆጠሩ አብያተ ክርስቲያናትን በወርቅ አስለበጠ:: በዚሕ ምክንያት ይህች ቀን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን "ዕለተ ትፍሥሕት [የደስታ ቀን]" ተብላ ትከበራለች::
† ቸሩ አምላክ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ከመከራ ይሠውርልን:: ከበረከቷም ያድለን:: ትውልዱ ደካሞች ነንና ከማንችለው ፈተናም ይጠብቀን::
🕊
[ † ሰኔ ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
፪. ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ
፫. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት [ከታላላቆቹ ሶፍያዎች አንዷ ናት]
፬. ቅዱሳት ሰማዕታት ደባሞንና ብስጣሞን [የቅድስት ሶፍያ ልጆች]
፭. ቅዱስ አውሎጊስ ሰማዕት
፮. ቅዱስ ዋርስኖፋ ሰማዕት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፪. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
፫. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
፬. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ እልፍዮስ]
፭. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
፮. ቅዱስ ዕፀ መስቀል
† " ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሒድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ:: ኢየሩሳሌም ሆይ እግሮቻችን በአደባባይሽ ቆሙ:: ኢየሩሳሌምስ እርስ በርሷ እንደ ተገለጠች ከተማ ተሠርታለች . . . ስለ ወንድሞቼ ስለ ባልንጀሮቼም በውስጥሽ ሰላም ይሁን አልሁ:: ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት ላንቺ መልካምነትሽን ፈለግሁ:: " † [መዝ.፻፳፩፥፩-፱] (121:1-9)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ የተድላና የደስታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
† በዚሕች ቀን ለ፵ [ 40 ] ዓመታት በመላው ዓለም የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናት የተከፈቱበት ቀን ይታሠባል:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :- ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ልቡና ታስባ : በዓለመ መላእክት ከታየች በኋላ :-
- አበው ተስፋ ሲያደርጓት
- ነቢያት ትንቢት ሲናገሩላት
- ሱባኤ ሲቆጥሩላት
- ምሳሌም ሲመስሉላት ኑረዋል::
† ዘመኑ በደረሰ ጊዜ በአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ :-
- በመጸነሱ ተጸንሳ
- በመወለዱ ተወልዳ
- በጥበብና በሞገስ አብራው አድጋ
- በጥምቀቱ ተጠምቃ
- በትምሕርቱ ጸንታ
- በደሙ ተቀድሳ
- በትንሣኤው ከብራ
- በዕርገቱ ሰማያዊነቷን አጽንታ
- በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስ ወርዶላት በይፋ ለልጆቿ ተሰጥታለች::
† አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት በመላው ዓለም ዞረው በብዙ ድካም የሠሯት ቤተ ክርስቲያን ለ፪፻ [200] ዓመታት እጅግ የበዙ መከራዋችን አሳልፋለች:: በ፪፻፷፭ [265] ዓ/ም የመጣባት መከራ ግን በዓለም ታሪክ እስካሁን አልታየም:: የወቅቱ ኃያላን ነገሥታት [ዲዮቅልጢያኖስና መክስምያኖስ] ዓለምን ለ፪ [2] ተካፍለው ክርስቲያኖችን የማጥፋት ዘመቻ ጀመሩ::
በመጀመሪያም በዓለም ያሉ ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት እንዲቃጠሉ ካልሆነም እንዲዘጉ : በፈንታቸው ደግሞ አዽሎን: አርዳሚስ የተባሉ ጣዖቶች እንዲተኩ ትዕዛዝ ተሰጠ:: ለ፵ [40] ዓመታት ክርስቲያን ስለሆኑ ብቻ ሚሊየኖች ተገደሉ: ታሰሩ: ተሰቃዩ: ተሰደዱ:: መጻሕፍት ተቃጠሉ: አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ወደሙ::
በአባቶቻችንና እናቶቻችን ላይ ልንናገረው ከምንችለው በላይ ጭንቅና መከራ ደረሰ:: ነገር ግን ቅዱሳኑ ያን ሁሉ ችለው ጸኑ:: ፵፯ [47] ሚሊየን የሚያሕሉትን ደግሞ ሰይፍና እሳት በላቸው:: በዛ ዘመን አንድ ቤተ ክርስቲያን ለማግኘት ከአሕጉር አሕጉር መሔድን ይጠይቅ ነበር::
ከዚሕ ሁሉ በኋላ ግን እግዚአብሔር "ግፍ ይበቃል" ሲል በ፫፻፭ [305] ዓ/ም ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ነገሠ:: መክስምያኖስን በጦርነት ሲማርከው አውሬው ዲዮቅልጢያኖስ ግን አብዶ ሞተ:: ይህ ከተደረገ ከዓመታት በኋላ [በ፫፻፲፫ [313] ዓ/ም] ታላቁ ቆስጠንጢኖስ የዓለም መሪዎችን በዚሕች ቀን ጠርቶ አዋጁን በአዋጅ ሻረው:: "ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ:: በፈንታው ደግሞ ሁሉም ጣዖት ቤቶች ይዘጉ" አለ::
በሺሕ የሚቆጠሩ አብያተ ክርስቲያናትን በወርቅ አስለበጠ:: በዚሕ ምክንያት ይህች ቀን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን "ዕለተ ትፍሥሕት [የደስታ ቀን]" ተብላ ትከበራለች::
† ቸሩ አምላክ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ከመከራ ይሠውርልን:: ከበረከቷም ያድለን:: ትውልዱ ደካሞች ነንና ከማንችለው ፈተናም ይጠብቀን::
🕊
[ † ሰኔ ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
፪. ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ
፫. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት [ከታላላቆቹ ሶፍያዎች አንዷ ናት]
፬. ቅዱሳት ሰማዕታት ደባሞንና ብስጣሞን [የቅድስት ሶፍያ ልጆች]
፭. ቅዱስ አውሎጊስ ሰማዕት
፮. ቅዱስ ዋርስኖፋ ሰማዕት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፪. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
፫. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
፬. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ እልፍዮስ]
፭. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
፮. ቅዱስ ዕፀ መስቀል
† " ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሒድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ:: ኢየሩሳሌም ሆይ እግሮቻችን በአደባባይሽ ቆሙ:: ኢየሩሳሌምስ እርስ በርሷ እንደ ተገለጠች ከተማ ተሠርታለች . . . ስለ ወንድሞቼ ስለ ባልንጀሮቼም በውስጥሽ ሰላም ይሁን አልሁ:: ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት ላንቺ መልካምነትሽን ፈለግሁ:: " † [መዝ.፻፳፩፥፩-፱] (121:1-9)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
†
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
[ ክፍል ሠላሳ ስምንት ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ ስንወድቅ አጋንንት ፈጥነው ያጠቁናል ፣ ተገቢ ባይሆንም ቅሉ ተገቢ እንደ ሆነ በማስመሰል የተባሕትዎ ሕይወትን ይዘን እንኖር ዘንድ ያሳስቡናል፡፡ የጠላቶቻችን ዓላማ በውድቀታችን ላይ ቍስልን ለመጨመር ነው፡፡
ያለ ሐኪም የተፈወሱ ጥቂት ናቸውና ሐኪሙ ይረዳህ ዘንድ ችሎታ እንደ ሌለው ሲነግርህ ፣ ቀጥሎ ወደ ሌላው ዘንድ መሄድ ይገባሃል፡፡ እንግዲያውስ ማንኛውም መርከብ የሰለጠነ ነጂው አብሮ ሳለ የስጥመት አደጋ የሚያጋጥመው ከሆነ ነጂው [ ቋትለኛው ] ሳይኖር ሲቀር ፈጽሞ ይጠፋል ብለን ስንናገር ከእኛ ጋር በመቃረን የሚያስብ ማን ነው?
ከመታዘዝ ትሕትና ይገኛል ፣ ከትሕትናም መቲረ ፈቃድ [ ፈቃድን መተው ] ይገኛል ፤ ስለ ትሕትናችን ብሎ ጌታ የሚያስበንና ከጠላቶቻችን የሚያድነን ነውና፡፡ [ መዝ.፻፴፭ ፥፳፫ ] ስለዚህ ከመታዘዝ ፈቃድን መተው ይገኛል ብለን መናገርን የሚከለክለን የለም ፣ በዚህ የተነሣ የትሕትና ግብ ተገኝቶአልና ነው፡፡ ሙሴ የሕግ መጀመሪያ እንደ ሆነ ሁሉ ትሕትናም የመቲረ ፈቃድ መጀመሪያ ነው ፤ ማርያም ምኩራብን ፍጹም [ የተሟላ ] እንዳደረገች ሴት ልጅም እናቷን ፍጹም [ የተሟላ ] ታደርጋለች፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
[ ክፍል ሠላሳ ስምንት ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ ስንወድቅ አጋንንት ፈጥነው ያጠቁናል ፣ ተገቢ ባይሆንም ቅሉ ተገቢ እንደ ሆነ በማስመሰል የተባሕትዎ ሕይወትን ይዘን እንኖር ዘንድ ያሳስቡናል፡፡ የጠላቶቻችን ዓላማ በውድቀታችን ላይ ቍስልን ለመጨመር ነው፡፡
ያለ ሐኪም የተፈወሱ ጥቂት ናቸውና ሐኪሙ ይረዳህ ዘንድ ችሎታ እንደ ሌለው ሲነግርህ ፣ ቀጥሎ ወደ ሌላው ዘንድ መሄድ ይገባሃል፡፡ እንግዲያውስ ማንኛውም መርከብ የሰለጠነ ነጂው አብሮ ሳለ የስጥመት አደጋ የሚያጋጥመው ከሆነ ነጂው [ ቋትለኛው ] ሳይኖር ሲቀር ፈጽሞ ይጠፋል ብለን ስንናገር ከእኛ ጋር በመቃረን የሚያስብ ማን ነው?
ከመታዘዝ ትሕትና ይገኛል ፣ ከትሕትናም መቲረ ፈቃድ [ ፈቃድን መተው ] ይገኛል ፤ ስለ ትሕትናችን ብሎ ጌታ የሚያስበንና ከጠላቶቻችን የሚያድነን ነውና፡፡ [ መዝ.፻፴፭ ፥፳፫ ] ስለዚህ ከመታዘዝ ፈቃድን መተው ይገኛል ብለን መናገርን የሚከለክለን የለም ፣ በዚህ የተነሣ የትሕትና ግብ ተገኝቶአልና ነው፡፡ ሙሴ የሕግ መጀመሪያ እንደ ሆነ ሁሉ ትሕትናም የመቲረ ፈቃድ መጀመሪያ ነው ፤ ማርያም ምኩራብን ፍጹም [ የተሟላ ] እንዳደረገች ሴት ልጅም እናቷን ፍጹም [ የተሟላ ] ታደርጋለች፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊
Forwarded from ኦርቶዶክሳዊ ቻናል
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በ30 ሰከንድ ውስጥ ስለሚጠፍ ምርጥ ቻናል ነው ይቀላቀሉ 👇
ይፍጠኑ መንፈሳዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዞ የሚያሸልም 🥹
https://www.tgoop.com/addlist/isQbYInIIR0zNTc0
ይፍጠኑ መንፈሳዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዞ የሚያሸልም 🥹
https://www.tgoop.com/addlist/isQbYInIIR0zNTc0
Forwarded from 💠ኢዮራም ፕሮሞሽን💠
👉ሲያስተምር እንባ ከአይኖቹ ይቀድሙታል ተስፋ የቆረጠውን ወጣት ተስፋ ይሰጠዋል በእግዚአብሔር ቃል ተስፋውን ያለመልማል የመምህር እዮብ ይመኑ ቻናል ይቀላቀሉ 👇👇👇
የመምህር እዮብ ይመኑ ትምህርት
የመምህር እዮብ ይመኑ ትምህርት
የመምህር እዮብ ይመኑ ትምህርት
የመምህር እዮብ ይመኑ ትምህርት
የመምህር እዮብ ይመኑ ትምህርት
የመምህር እዮብ ይመኑ ትምህርት
Forwarded from ኦርቶዶክሳዊ ቻናል
የ1000 ብር ካርድ ሊለቀቅ ነው 9 ደቂቃ ብቻ ነው የቀራው። ቶሎ ከስር JOIN ሚለውን ነክታቹ JOIN REQUEST ላኩ 🏃♀️🏃♂️
20 ሰዎች ብቻ ፍጠኑኑኑኑኑ🏃♀➡️🏃♀➡️🏃♀➡️
20 ሰዎች ብቻ ፍጠኑኑኑኑኑ🏃♀➡️🏃♀➡️🏃♀➡️
Forwarded from 💠ኢዮራም ፕሮሞሽን💠
💕ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይ ፈ ል ጋ ሉ ? 🔔 💕
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧
🕊
[ † እንኳን ለታላቁ ሰማዕት ማር ገላውዴዎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት † 🕊
† ቅዱስ ገላውዴዎስ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘ በድሮው የሮም ግዛት በአንጾኪያ [አሁን ሶርያ ውስጥ] ነው:: አባቱ አብጥልዎስ የሮም ቄሣር የኑማርያኖስ ወንድም ነበር:: በዚህ ምክንያት ቅዱሱ ያደገው በቤተ መንግሥት ውስጥ ነው::
ወቅቱ መልካምም ክፉም ነገሮች ነበሩት:: መልካሙ ነገር በቤተ መንግሥት አካባቢ ይኖሩ የነበሩት ልዑላኑ አብዛኞቹ በፍቅረ ክርስቶስ የታሠሩ ነበሩ:: ከእነዚህ መካካከል "ቅዱስ ፋሲለደስ: ቅዱሳኑ :- ፊቅጦር: ቴዎድሮስ: አባዲር: አውሳብዮስ: ዮስጦስ: አቦሊ: እስጢፋኖስ . . ." ነበሩ:: ቅዱሳቱ "ማርታ: ታውክልያ: ኢራኢ: ሶፍያ. . ." ነበሩ::
አስቸጋሪው ነገር ደግሞ ነጋ መሸ ኑሯቸው ጦርነት ነበር:: የዘመኑ የፋርስና የቁዝ መሪዎች ጦረኞች ነበሩና ዕለት ዕለት ፍልሚያ ነበር:: በዚህ ምክንያት ቅዱስ ገላውዴዎስ የተመሠከረለት አርበኛና የተባረከ ንጹሕ ክርስቲያን ሆኖ አድጓል:: ከልጅነቱ ጀምሮ ቅዱሳት መጻሕፍትን በማጥናቱ ሕይወቱ በመንፈስ ቅዱስ ጨውነት ታሽቷል:: እርሱ የነገሥታቱ ቤተሰብ ነው:: ማዕዱ በየዓይነቱ ሞልቶ ካልመሸ እህል አይቀምስም:: ጸሎቱ ስሙር: ስግደቱ ከምድር: አኗኗሩ በፍቅር ሆነ:: በዚያውም ላይ በድንግልናው የጸና ኃያል ነበር::
በጊዜው የቅዱስ ገላውዴዎስን ያህል መልኩ ያማረ [ደመ ግቡ] በአካባቢው አልነበረም:: ይህ ግን ሊያታልለው አልቻለም:: ሁሉ በእጁ ቢሆንም ለእርሱ ግን ብቸኛ ምርጫው ሃይማኖተ ክርስቶስ ነበር::
ቅዱስ ገላውዴዎስ ለጦርነት ወጥቶ ሲመለስ ንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ሃይማኖቱን ክዶ: ሕዝቡን ለጣዖት ሲያሰግድ: ክርስቲያኖችን ሲገድል ደረሰ::
† ቅዱሱ ኃያል የጦር ሰው ነውና ንጉሡን መግደል ሲችል ተወው:: በዚያ ሰሞንም ለገላውዴዎስ ሁለት ምርጫዎች ቀረቡለት :-
፩. ክርስቶስን ክዶ የንጉሡ ተከታይ መሆን:
፪. በክርስትናው ደሙን ማፍሰስ::
የቅዱሳኑ ምርጫቸው የታወቀ ነውና ታስሮ ወደ ግብጽ ተጋዘ:: በዚያ ከመኮንኑ ጋር ስለ ሃይማኖት ተከራክረው መኮንኑ ስለተበሳጨ ቅዱሱን በረዥም ጦር ጐኑን ወጋው:: ዘለፍ ብሎ ነፍሱን ሰጠ:: ሕዝበ ክርስቲያኑ በድብቅ መጥተው የቅዱሱን ሥጋ ሽቱ ቀብተው: ከዝማሬ ጋር ገነዙት:: የጓደኛው እናት ቅድስት ሶፍያ መጥታ ወደ ሶርያ ወስዳዋለች::
† ተወዳጅ: ኃያል: ቡሩክና መልካም ሰው ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት በሆነባት በዚሕች ዕለት በመላው ኦርቶዶክሳውያን ይከበራል::
† አምላካችን የቅዱሱን መንኖ ጥሪት: ትዕግስት: ጸጋና በረከት ያሳድርብን:: አሜን::
🕊
[ † ሰኔ ፲፩ [ 11 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት [ሕይወቱ መላእክትን የመሰለ]
፪. አንድ ሺ ሰማንያ ስምንት ሰማዕታት [የቅዱስ ገላውዴዎስ ማኅበር]
፫. አባ ክርዳኑ ሊቀ ጳጳሳት
፬. እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ክብራ ኢትዮጵያዊት [የአቡነ በጸሎተ ሚካኤል እህት]
፭. የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዳሴ ቤቱ [ግብጽ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያሬድ ካህን
፪. ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
፫. ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና
፬. አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
† " የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ:: ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ: ፀሐይ: ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ . . . አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ: ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ:: ሰባኪው :- "ከንቱ: ከንቱ: ሁሉ ከንቱ ነው" ይላል:: " † [መክ. ፲፪፥፩-፱]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለታላቁ ሰማዕት ማር ገላውዴዎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት † 🕊
† ቅዱስ ገላውዴዎስ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘ በድሮው የሮም ግዛት በአንጾኪያ [አሁን ሶርያ ውስጥ] ነው:: አባቱ አብጥልዎስ የሮም ቄሣር የኑማርያኖስ ወንድም ነበር:: በዚህ ምክንያት ቅዱሱ ያደገው በቤተ መንግሥት ውስጥ ነው::
ወቅቱ መልካምም ክፉም ነገሮች ነበሩት:: መልካሙ ነገር በቤተ መንግሥት አካባቢ ይኖሩ የነበሩት ልዑላኑ አብዛኞቹ በፍቅረ ክርስቶስ የታሠሩ ነበሩ:: ከእነዚህ መካካከል "ቅዱስ ፋሲለደስ: ቅዱሳኑ :- ፊቅጦር: ቴዎድሮስ: አባዲር: አውሳብዮስ: ዮስጦስ: አቦሊ: እስጢፋኖስ . . ." ነበሩ:: ቅዱሳቱ "ማርታ: ታውክልያ: ኢራኢ: ሶፍያ. . ." ነበሩ::
አስቸጋሪው ነገር ደግሞ ነጋ መሸ ኑሯቸው ጦርነት ነበር:: የዘመኑ የፋርስና የቁዝ መሪዎች ጦረኞች ነበሩና ዕለት ዕለት ፍልሚያ ነበር:: በዚህ ምክንያት ቅዱስ ገላውዴዎስ የተመሠከረለት አርበኛና የተባረከ ንጹሕ ክርስቲያን ሆኖ አድጓል:: ከልጅነቱ ጀምሮ ቅዱሳት መጻሕፍትን በማጥናቱ ሕይወቱ በመንፈስ ቅዱስ ጨውነት ታሽቷል:: እርሱ የነገሥታቱ ቤተሰብ ነው:: ማዕዱ በየዓይነቱ ሞልቶ ካልመሸ እህል አይቀምስም:: ጸሎቱ ስሙር: ስግደቱ ከምድር: አኗኗሩ በፍቅር ሆነ:: በዚያውም ላይ በድንግልናው የጸና ኃያል ነበር::
በጊዜው የቅዱስ ገላውዴዎስን ያህል መልኩ ያማረ [ደመ ግቡ] በአካባቢው አልነበረም:: ይህ ግን ሊያታልለው አልቻለም:: ሁሉ በእጁ ቢሆንም ለእርሱ ግን ብቸኛ ምርጫው ሃይማኖተ ክርስቶስ ነበር::
ቅዱስ ገላውዴዎስ ለጦርነት ወጥቶ ሲመለስ ንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ሃይማኖቱን ክዶ: ሕዝቡን ለጣዖት ሲያሰግድ: ክርስቲያኖችን ሲገድል ደረሰ::
† ቅዱሱ ኃያል የጦር ሰው ነውና ንጉሡን መግደል ሲችል ተወው:: በዚያ ሰሞንም ለገላውዴዎስ ሁለት ምርጫዎች ቀረቡለት :-
፩. ክርስቶስን ክዶ የንጉሡ ተከታይ መሆን:
፪. በክርስትናው ደሙን ማፍሰስ::
የቅዱሳኑ ምርጫቸው የታወቀ ነውና ታስሮ ወደ ግብጽ ተጋዘ:: በዚያ ከመኮንኑ ጋር ስለ ሃይማኖት ተከራክረው መኮንኑ ስለተበሳጨ ቅዱሱን በረዥም ጦር ጐኑን ወጋው:: ዘለፍ ብሎ ነፍሱን ሰጠ:: ሕዝበ ክርስቲያኑ በድብቅ መጥተው የቅዱሱን ሥጋ ሽቱ ቀብተው: ከዝማሬ ጋር ገነዙት:: የጓደኛው እናት ቅድስት ሶፍያ መጥታ ወደ ሶርያ ወስዳዋለች::
† ተወዳጅ: ኃያል: ቡሩክና መልካም ሰው ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት በሆነባት በዚሕች ዕለት በመላው ኦርቶዶክሳውያን ይከበራል::
† አምላካችን የቅዱሱን መንኖ ጥሪት: ትዕግስት: ጸጋና በረከት ያሳድርብን:: አሜን::
🕊
[ † ሰኔ ፲፩ [ 11 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት [ሕይወቱ መላእክትን የመሰለ]
፪. አንድ ሺ ሰማንያ ስምንት ሰማዕታት [የቅዱስ ገላውዴዎስ ማኅበር]
፫. አባ ክርዳኑ ሊቀ ጳጳሳት
፬. እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ክብራ ኢትዮጵያዊት [የአቡነ በጸሎተ ሚካኤል እህት]
፭. የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዳሴ ቤቱ [ግብጽ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያሬድ ካህን
፪. ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
፫. ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና
፬. አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
† " የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ:: ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ: ፀሐይ: ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ . . . አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ: ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ:: ሰባኪው :- "ከንቱ: ከንቱ: ሁሉ ከንቱ ነው" ይላል:: " † [መክ. ፲፪፥፩-፱]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
🕊 † 🕊
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ከክርስቲያን ሃይማኖት የተለዩ ናቸው ! ]
🕊 💖 🕊
❝ በእግዚአብሔርነቱ ኀይል ሕያው ሲሆን ፤ ደክሞ ተሰቀለ ከሙታንም ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ዳግመኛ ሞት የለበትም ፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተነሥቶ በክብር በተገለጠ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ይህ ስለእርሱ እንደ ተጻፈ ዐውቀዋልና። [ዮሐ.፪፥፳፪ ። ፪ቆሮ.፲፫፥፬ ]
በክብር ተገለጠ የተባለ መለኮት አይደለም ኵለንታ አካሉ ፥ ኵለንታ ባሕርዩ ክብር ነው እንደምን ከበረ ይባላል? ከድንግል በነሣው ከሙታን ለይቶ በአስነሣው በሥጋ ከበረ ተባለ እንጂ። እንግዲህም በክብር ይገለጣል ተባለ እንጂ ወደ ሰማይ ዐርጓልና ከአብም በመተካከል ተቀምጧልና። [ዮሐ.፩፥፲፬ ፡ ፪፥፲፱ ፡ ፲፪፥፳፰ ፡ ፲፫፥፴፩-፴ ]
ሁሉን ይገዛ በሁሉ ይፈርድ ዘንድ በኋላ ዘመን ዳግመኛ በሥጋ ይመጣልና ፤ ለሁሉም እንደ ሥራው ይከፍለዋል ፥ በቀናች ሃይማኖት የጸኑትን ደስ ካሰኙት ከሰማዕታት ፤ ከነቢያት ከሐዋርያት ጋር ሁሉ በመንግሥተ ሰማያት በክብር ያኖረዋል ፤ ውዳሴ ከንቱን በመውደድ ከሃይማኖት የወጡትን ግን ከአይሁድና ከሕግ አፍራሾ ሁሉ ጋር በገሀነም በሥቃይ ያኖራቸዋል እሊህም ወደ ዘለዓለም ኵነኔ ይሔዳሉ። [ ማቴ.፳፭፥፴፩-፵፮ ፡ ግብ.ሐዋ.፩፥፲፩ ። መዝ. ፷፪ (፷፩)፥፲፪ ። ሮሜ.፪፥፮—፲ ]
በተራበ በተጠማ በታመመ በደከመ ጊዜ መለኮት ከትስብእት ተለየ ፤ መለኮትስ ተዋሕዶት ቢሆን ድንቅ ድንቅ ሥራ በሠራ ነበር እያሉ ባለማወቃቸው ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ ነው የሚሉ አሉ። እንዲህ ከቀናች ከክርስቲያን ሃይማኖት የተለዩ ናቸው ።
እኛ ግን ባለመለየት አንድ አካል ፤ አንድ ባሕርይ እንደሆነ እናምለን ፤ ግን በፈቃዱ ሥጋውን መከራ እንዲቀበል አደረገ። ሰዎች የተዋሐደው ሥጋ ምትሐት ነው ፤ እውነተኛ ሥጋ አይደለም እንዳይሉ ፤ ስለዚህም እንዲታመም አደረገው። [ ኢሳ.፶፫፥፪-፬ ። ዮሐ.፲፥፲፰ ። ሉቃ.፳፬፥፲፱-፳፩ ] ❞
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ከክርስቲያን ሃይማኖት የተለዩ ናቸው ! ]
🕊 💖 🕊
❝ በእግዚአብሔርነቱ ኀይል ሕያው ሲሆን ፤ ደክሞ ተሰቀለ ከሙታንም ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ዳግመኛ ሞት የለበትም ፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተነሥቶ በክብር በተገለጠ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ይህ ስለእርሱ እንደ ተጻፈ ዐውቀዋልና። [ዮሐ.፪፥፳፪ ። ፪ቆሮ.፲፫፥፬ ]
በክብር ተገለጠ የተባለ መለኮት አይደለም ኵለንታ አካሉ ፥ ኵለንታ ባሕርዩ ክብር ነው እንደምን ከበረ ይባላል? ከድንግል በነሣው ከሙታን ለይቶ በአስነሣው በሥጋ ከበረ ተባለ እንጂ። እንግዲህም በክብር ይገለጣል ተባለ እንጂ ወደ ሰማይ ዐርጓልና ከአብም በመተካከል ተቀምጧልና። [ዮሐ.፩፥፲፬ ፡ ፪፥፲፱ ፡ ፲፪፥፳፰ ፡ ፲፫፥፴፩-፴ ]
ሁሉን ይገዛ በሁሉ ይፈርድ ዘንድ በኋላ ዘመን ዳግመኛ በሥጋ ይመጣልና ፤ ለሁሉም እንደ ሥራው ይከፍለዋል ፥ በቀናች ሃይማኖት የጸኑትን ደስ ካሰኙት ከሰማዕታት ፤ ከነቢያት ከሐዋርያት ጋር ሁሉ በመንግሥተ ሰማያት በክብር ያኖረዋል ፤ ውዳሴ ከንቱን በመውደድ ከሃይማኖት የወጡትን ግን ከአይሁድና ከሕግ አፍራሾ ሁሉ ጋር በገሀነም በሥቃይ ያኖራቸዋል እሊህም ወደ ዘለዓለም ኵነኔ ይሔዳሉ። [ ማቴ.፳፭፥፴፩-፵፮ ፡ ግብ.ሐዋ.፩፥፲፩ ። መዝ. ፷፪ (፷፩)፥፲፪ ። ሮሜ.፪፥፮—፲ ]
በተራበ በተጠማ በታመመ በደከመ ጊዜ መለኮት ከትስብእት ተለየ ፤ መለኮትስ ተዋሕዶት ቢሆን ድንቅ ድንቅ ሥራ በሠራ ነበር እያሉ ባለማወቃቸው ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ ነው የሚሉ አሉ። እንዲህ ከቀናች ከክርስቲያን ሃይማኖት የተለዩ ናቸው ።
እኛ ግን ባለመለየት አንድ አካል ፤ አንድ ባሕርይ እንደሆነ እናምለን ፤ ግን በፈቃዱ ሥጋውን መከራ እንዲቀበል አደረገ። ሰዎች የተዋሐደው ሥጋ ምትሐት ነው ፤ እውነተኛ ሥጋ አይደለም እንዳይሉ ፤ ስለዚህም እንዲታመም አደረገው። [ ኢሳ.፶፫፥፪-፬ ። ዮሐ.፲፥፲፰ ። ሉቃ.፳፬፥፲፱-፳፩ ] ❞
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖