†
[ 🕊 ድምፀ ተዋሕዶ 🕊 ]
🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒
[ ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ። ]
[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]
🕊
❝ ጕልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል ? ቃልህን በመጠበቅ ነው። ❞ [ መዝ . ፻፲፱ ፥ ፱ ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ሕይወተ ወራዙት [ የወጣቶች ሕይወት ! ]
[ ክፍል - ዘጠኝ - ]
💖 ድንቅ ትምህርት 💖
[ በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ክፉ የጎልማሳነት ምኞት ]
❝ የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]
🕊 💖 🕊
👇
[ 🕊 ድምፀ ተዋሕዶ 🕊 ]
🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒
[ ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ። ]
[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]
🕊
❝ ጕልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል ? ቃልህን በመጠበቅ ነው። ❞ [ መዝ . ፻፲፱ ፥ ፱ ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ሕይወተ ወራዙት [ የወጣቶች ሕይወት ! ]
[ ክፍል - ዘጠኝ - ]
💖 ድንቅ ትምህርት 💖
[ በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ክፉ የጎልማሳነት ምኞት ]
❝ የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]
🕊 💖 🕊
👇
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
[የምስራቅ ኦርቶዶክስ ምንፍቅና ! ]
🔔
❝ እንደ ስሕተት ሽንገላ ባለ ተንኮል በሰዎችም ማታለል ምክንያት በትምህርት ነፋስ ሁሉ እየተፍገመገምን ወዲያና ወዲህም እየተንሳፈፍን ሕፃናት መሆን ወደ ፊት አይገባንም ፥
ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን በነገር ሁሉ ወደ እርሱ ራስ ወደሚሆን ወደ ክርስቶስ እንደግ ፤ ❞ [ ኤፌ.፬ ፥ ፲፬ ]
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
- ምስራቃውያን ከኦሬንታል ኦርቶዶክስ የሚለዩባቸው የአስተምህሮና የመንፈሳዊ ሕይወት አቅጣጫዎች ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመንፈሳዊ ኮሌጆቻችን ውስጥ እየተስፋፋ ስለመጣው የሐራጥቃ ተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴና የማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻቸው !
🔔
- በዲ/ን መጥምቅ እና
- በዲ/ን ቸርነት
[ ማክሰኞ በምሽቱ መርሐ-ግብር ይጠብቁ ! ]
🕊 💖 🕊
[
🔔
❝ እንደ ስሕተት ሽንገላ ባለ ተንኮል በሰዎችም ማታለል ምክንያት በትምህርት ነፋስ ሁሉ እየተፍገመገምን ወዲያና ወዲህም እየተንሳፈፍን ሕፃናት መሆን ወደ ፊት አይገባንም ፥
ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን በነገር ሁሉ ወደ እርሱ ራስ ወደሚሆን ወደ ክርስቶስ እንደግ ፤ ❞ [ ኤፌ.፬ ፥ ፲፬ ]
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
- ምስራቃውያን ከኦሬንታል ኦርቶዶክስ የሚለዩባቸው የአስተምህሮና የመንፈሳዊ ሕይወት አቅጣጫዎች ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመንፈሳዊ ኮሌጆቻችን ውስጥ እየተስፋፋ ስለመጣው የሐራጥቃ ተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴና የማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻቸው !
🔔
- በዲ/ን መጥምቅ እና
- በዲ/ን ቸርነት
[ ማክሰኞ በምሽቱ መርሐ-ግብር ይጠብቁ ! ]
🕊 💖 🕊
🕊
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
❖ ጥቅምት ፲ [ 10 ] ❖
[ ✞ እንኩዋን ለቅዱሳን ሰማዕታት "ባኮስ ወሰርጊስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ ]
† 🕊 ቅዱሳን ባኮስ ወሰርጊስ 🕊 †
ሰማዕትነት በክርስትና ለሃይማኖት የሚከፈል የመጨረሻው ዋጋ [መስዋዕትነት] ነው:: ሰው ለፈጣሪው ሰውነቱን ሊያስገዛ: ሃብት ንብረቱን ሊሰጥ ይችላል:: ከስጦታ በላይ ታላቅ ስጦታ ግን ራስን አሳልፎ መስጠት ነው::
ራስን መስጠት በትዳርም ሆነ በምናኔ ውስጥ ይቻላል:: የመጨረሻ ደረጃው ግን ሰማዕትነት ነው:: "አማን መነኑ ሰማዕት ጣዕማ ለዝ ዓለም: ወተዓገሡ ሞተ መሪረ በእንተ መንግስተ ሰማያት" እንዳለው ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ሰማዕትነት ማለት መራራውን ሞት ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ሲሉ መታገስ ነው::
እርሱ ቅሉ መድኃኒታችን ክርስቶስ የሰማይና የምድር ጌታ ሲሆን ኃፍረተ መስቀልን ታግሦ ሙቶልን የለ! በዓለም ያሉ ብዙ እምነቶች ስለ መግደል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስተምራሉ:: ክርስትና ግን መሞትን እንጂ መግደልን የሚመለከት ሕግ የለውም::
እርሱ ባለቤቱ "ጠላቶቻችሁን ውደዱ: የሚረግሟችሁን መርቁ: ስለሚያሳድዷችሁ ጸልዩ" ብሎናልና:: [ማቴ.፭፥፵፬] ነገር ግን ዕለት ዕለት ራሳችንን በሃይማኖትና በምግባር ካልኮተኮትነው ክርስትና በአንድ ጀምበር ፍጹም የሚኮንበት እምነት አይደለምና በፈተና መውደቅ ይመጣል::
በተለይ የዘመኑ ክርስቲያን ወጣቶች ልናስተውል ይገባናል:: የቀደሙ ወጣት ሰማዕታት ዜና የሚነገረን እንድንጸና ነውና::
እስኪ ለዛሬ ደግሞ በአጭሩ የቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስን ዜና እንካፈል::
እነዚህ ቅዱሳን የዘመነ ሰማዕታት ፍሬዎች ናቸው:: ባኮስ እና ሰርጊስ [ሰርግዮስ] ከልጅነት ጀምሮ ባልንጀሮች ናቸው:: በ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን በሮም ግዛት ሥር መክስምያኖስና ዲዮቅልጢያኖስ እስከ ነገሡበት ዘመን ድረስ በአንጻሩም ቢሆን ሰላም ነበር::
ታዲያ በዚህ የሰላም ጊዜ ፪ቱ ቅዱሳን ሥራ አልፈቱም:: ጾምን: ጸሎትንና በጐ ምግባራትን ሁሉ ይከተሉ ነበር:: ለመከራ ዘመን ስንቅ የሚሆነን በሰላሙ ዘመን የተያዘ ስንቅ ነውና::
በዚያው አንጻር ደግሞ ሠርቶ መብላት ይገባልና ሥራ ሲፈልጉ መክስምያኖስ ሠራዊት መሰብሰብ ጀመረ:: እነርሱም ከሠራዊቱ ዘንድ ተቆጥረው የምድራዊ ንጉሥ ጭፍሮች ሆኑ:: በእርግጥ በዘመናችን ለክርስትና አይመቹም ከሚባልላቸው ሥራዎች አንዱ ውትድርና ነው::
ነገር ግን ብዙ ቅዱሳንን ስትመለከቷቸው ሙያቸው ይሔው ነበር:: ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ ጊዜው የሰላምም ይሁን የጦርነት ይጾማሉ: ይጸልያሉ: ይመጸውታሉ:: እንዲህ እንዲህ እያሉም ዘመናት አለፉ::
ከቆይታ በሁዋላ ግን ሰይጣን ያደረበት ንጉሡ መክስምያኖስ ጣዖት አመለከ:: አዋጅም አውጥቶ ክርስቲያኖችን ያሰቃይ: ይገድልም ያዘ:: ቅዱሳኑ ይህንን ሲሰሙ አዘኑ::
ቁጭ ብለውም ተወያዩ:: በልባቸው ፍቅረ ክርስቶስ ይነድ ነበርና ወጣትነታቸው: መልካቸው: ተወዳጅነታቸው ሁሉ ሊያታልላቸው አልቻለም:: እንደ አንድ ልብ መካሪ: እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ስለ ሃይማኖት ሊሰው ወሰኑ::
በማግስቱም ንጉሡ ወደ ሾመው የቅርብ አለቃቸው ቀረቡና "የምንነግርህ ነገር አለን" አሉት:: "እሺ" ሲላቸው በወገባቸው ያለውን የክብር መታጠቀያና የክብር ልብሳቸውን በፊቱ ወረወሩለትና "እኛ የክርስቶስ ጭፍሮች ነንና ከዚህ በሁዋላ ላንተ: ለጣዖት አምላኪው አንታዘዝም" አሉት::
መኮንኑ ነዶታልና አስገረፋቸው: አሳሰራቸው:: በረሃብና በጥም: በብዙ መክፈልተ ኩነኔም አሰቃያቸው:: እነርሱ ግን ጽኑዓን ነበሩና አልቻሏቸውም:: ጥቅምት ፬ ቀን በሆነ ጊዜ ግን ፪ቱን ለያዩዋቸው::
ቅዱስ ባኮስን ለብቻው ወስደው ትልቅ ድንጋይ በአንገቱ ላይ አሠሩበትና ባሕር ውስጥ አሰጠሙት::
ነፍሱም ከስጋው ስትለይ ባሕር ወደ ዳር አስወጣችው:: በአካባባቢውም "ባባ" እና "ማማ" የሚባሉ ባሕታውያን ነበሩና እግዚአብሔር እንዲገንዙት አዘዛቸው:: ሲሔዱም ቅዱስ ሥጋውን አንበሳና ተኩላ ሲጠብቁት አግኝተው: በታላቅ ዝማሬ ገንዘው: በራሳቸው ተሸክመው ወስደው: በበዓታቸው ውስጥ ቀበሩት::
ቅዱስ ሰርጊስን ደግሞ ለ፮ ቀናት ካሠሩት በሁዋላ በዚህች ቀን እጁንና እግሩን በእንጨት ላይ ቸንክረው: በእንስሳት ጭራ ላይ አስረው ሲጐትቱት ውለዋል:: አንገቱን በሰየፉት ጊዜም አንዲት ወጣት ደሙን ተቀብላ በረከትን አግኝታለች:: የመከራ ዘመን ካለፈ በሁዋላም ለቅዱሳኑ ቤተ ክርስቲያን ታንጾ በዚህች ቀን ተቀድሷል:: ተአምራትም ታይተዋል::
አምላከ ሰማዕታት ጽንዓት: ትእግስታቸውን አሳድሮ ከበረከታቸው ይክፈለን::
🕊
[ † ጥቅምት ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ [ሰማዕታት]
፪. ቅዱስ ዮሐንስ መስተጋድል
፫. አባ አውማንዮስ ሊቀ ዻዻሳት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፪. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
፫. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
፬. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ እልፍዮስ]
፭. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
፮. ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ
፯. ቅዱስ እፀ መስቀል
" ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ: ወይስ ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ ራቁትነት: ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን? 'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች ተቈጠርን' ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው:: በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::" [ሮሜ.፰፥፴፭-፴፰]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
❖ ጥቅምት ፲ [ 10 ] ❖
[ ✞ እንኩዋን ለቅዱሳን ሰማዕታት "ባኮስ ወሰርጊስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ ]
† 🕊 ቅዱሳን ባኮስ ወሰርጊስ 🕊 †
ሰማዕትነት በክርስትና ለሃይማኖት የሚከፈል የመጨረሻው ዋጋ [መስዋዕትነት] ነው:: ሰው ለፈጣሪው ሰውነቱን ሊያስገዛ: ሃብት ንብረቱን ሊሰጥ ይችላል:: ከስጦታ በላይ ታላቅ ስጦታ ግን ራስን አሳልፎ መስጠት ነው::
ራስን መስጠት በትዳርም ሆነ በምናኔ ውስጥ ይቻላል:: የመጨረሻ ደረጃው ግን ሰማዕትነት ነው:: "አማን መነኑ ሰማዕት ጣዕማ ለዝ ዓለም: ወተዓገሡ ሞተ መሪረ በእንተ መንግስተ ሰማያት" እንዳለው ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ሰማዕትነት ማለት መራራውን ሞት ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ሲሉ መታገስ ነው::
እርሱ ቅሉ መድኃኒታችን ክርስቶስ የሰማይና የምድር ጌታ ሲሆን ኃፍረተ መስቀልን ታግሦ ሙቶልን የለ! በዓለም ያሉ ብዙ እምነቶች ስለ መግደል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስተምራሉ:: ክርስትና ግን መሞትን እንጂ መግደልን የሚመለከት ሕግ የለውም::
እርሱ ባለቤቱ "ጠላቶቻችሁን ውደዱ: የሚረግሟችሁን መርቁ: ስለሚያሳድዷችሁ ጸልዩ" ብሎናልና:: [ማቴ.፭፥፵፬] ነገር ግን ዕለት ዕለት ራሳችንን በሃይማኖትና በምግባር ካልኮተኮትነው ክርስትና በአንድ ጀምበር ፍጹም የሚኮንበት እምነት አይደለምና በፈተና መውደቅ ይመጣል::
በተለይ የዘመኑ ክርስቲያን ወጣቶች ልናስተውል ይገባናል:: የቀደሙ ወጣት ሰማዕታት ዜና የሚነገረን እንድንጸና ነውና::
እስኪ ለዛሬ ደግሞ በአጭሩ የቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስን ዜና እንካፈል::
እነዚህ ቅዱሳን የዘመነ ሰማዕታት ፍሬዎች ናቸው:: ባኮስ እና ሰርጊስ [ሰርግዮስ] ከልጅነት ጀምሮ ባልንጀሮች ናቸው:: በ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን በሮም ግዛት ሥር መክስምያኖስና ዲዮቅልጢያኖስ እስከ ነገሡበት ዘመን ድረስ በአንጻሩም ቢሆን ሰላም ነበር::
ታዲያ በዚህ የሰላም ጊዜ ፪ቱ ቅዱሳን ሥራ አልፈቱም:: ጾምን: ጸሎትንና በጐ ምግባራትን ሁሉ ይከተሉ ነበር:: ለመከራ ዘመን ስንቅ የሚሆነን በሰላሙ ዘመን የተያዘ ስንቅ ነውና::
በዚያው አንጻር ደግሞ ሠርቶ መብላት ይገባልና ሥራ ሲፈልጉ መክስምያኖስ ሠራዊት መሰብሰብ ጀመረ:: እነርሱም ከሠራዊቱ ዘንድ ተቆጥረው የምድራዊ ንጉሥ ጭፍሮች ሆኑ:: በእርግጥ በዘመናችን ለክርስትና አይመቹም ከሚባልላቸው ሥራዎች አንዱ ውትድርና ነው::
ነገር ግን ብዙ ቅዱሳንን ስትመለከቷቸው ሙያቸው ይሔው ነበር:: ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ ጊዜው የሰላምም ይሁን የጦርነት ይጾማሉ: ይጸልያሉ: ይመጸውታሉ:: እንዲህ እንዲህ እያሉም ዘመናት አለፉ::
ከቆይታ በሁዋላ ግን ሰይጣን ያደረበት ንጉሡ መክስምያኖስ ጣዖት አመለከ:: አዋጅም አውጥቶ ክርስቲያኖችን ያሰቃይ: ይገድልም ያዘ:: ቅዱሳኑ ይህንን ሲሰሙ አዘኑ::
ቁጭ ብለውም ተወያዩ:: በልባቸው ፍቅረ ክርስቶስ ይነድ ነበርና ወጣትነታቸው: መልካቸው: ተወዳጅነታቸው ሁሉ ሊያታልላቸው አልቻለም:: እንደ አንድ ልብ መካሪ: እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ስለ ሃይማኖት ሊሰው ወሰኑ::
በማግስቱም ንጉሡ ወደ ሾመው የቅርብ አለቃቸው ቀረቡና "የምንነግርህ ነገር አለን" አሉት:: "እሺ" ሲላቸው በወገባቸው ያለውን የክብር መታጠቀያና የክብር ልብሳቸውን በፊቱ ወረወሩለትና "እኛ የክርስቶስ ጭፍሮች ነንና ከዚህ በሁዋላ ላንተ: ለጣዖት አምላኪው አንታዘዝም" አሉት::
መኮንኑ ነዶታልና አስገረፋቸው: አሳሰራቸው:: በረሃብና በጥም: በብዙ መክፈልተ ኩነኔም አሰቃያቸው:: እነርሱ ግን ጽኑዓን ነበሩና አልቻሏቸውም:: ጥቅምት ፬ ቀን በሆነ ጊዜ ግን ፪ቱን ለያዩዋቸው::
ቅዱስ ባኮስን ለብቻው ወስደው ትልቅ ድንጋይ በአንገቱ ላይ አሠሩበትና ባሕር ውስጥ አሰጠሙት::
ነፍሱም ከስጋው ስትለይ ባሕር ወደ ዳር አስወጣችው:: በአካባባቢውም "ባባ" እና "ማማ" የሚባሉ ባሕታውያን ነበሩና እግዚአብሔር እንዲገንዙት አዘዛቸው:: ሲሔዱም ቅዱስ ሥጋውን አንበሳና ተኩላ ሲጠብቁት አግኝተው: በታላቅ ዝማሬ ገንዘው: በራሳቸው ተሸክመው ወስደው: በበዓታቸው ውስጥ ቀበሩት::
ቅዱስ ሰርጊስን ደግሞ ለ፮ ቀናት ካሠሩት በሁዋላ በዚህች ቀን እጁንና እግሩን በእንጨት ላይ ቸንክረው: በእንስሳት ጭራ ላይ አስረው ሲጐትቱት ውለዋል:: አንገቱን በሰየፉት ጊዜም አንዲት ወጣት ደሙን ተቀብላ በረከትን አግኝታለች:: የመከራ ዘመን ካለፈ በሁዋላም ለቅዱሳኑ ቤተ ክርስቲያን ታንጾ በዚህች ቀን ተቀድሷል:: ተአምራትም ታይተዋል::
አምላከ ሰማዕታት ጽንዓት: ትእግስታቸውን አሳድሮ ከበረከታቸው ይክፈለን::
🕊
[ † ጥቅምት ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ [ሰማዕታት]
፪. ቅዱስ ዮሐንስ መስተጋድል
፫. አባ አውማንዮስ ሊቀ ዻዻሳት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፪. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
፫. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
፬. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ እልፍዮስ]
፭. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
፮. ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ
፯. ቅዱስ እፀ መስቀል
" ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ: ወይስ ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ ራቁትነት: ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን? 'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች ተቈጠርን' ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው:: በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::" [ሮሜ.፰፥፴፭-፴፰]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
Forwarded from 💠ኢዮራም ፕሮሞሽን💠
💕ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይ ፈ ል ጋ ሉ ? 🔔 💕
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧
🕊 💖 🕊
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ❝ በዕፀ መስቀል ላይ የተቸነከርክ አንተ ነህ ❞ ]
🕊
❝ ጌታዬ ፈጣሪዬ አንተ ነህ። ቅድመ ዓለም የነበርክ አንተ ነህ ፤ ዛሬም ያለህ አንተ ነህ። ሰማያዊ አንተ ነህ። ምድራዊም አንተ ነህ። [ዮሐ.፩፥፳፬–፴።
በሰማይ በአብ ህልው የምትሆን አንተ ነህ። ስለእኛ በመስቀል የተሰቀልክ አንተ ነህ። ዓለም ሳይፈጠር ዠምሮ በጌትነት ዙፋንህ ያለህ አንተ ነህ። አሁንም በዕፀ መስቀል ላይ የተቸነከርክ አንተ ነህ።
በመለኮት ሕማም ሞት የሌለብህ አንተ ነህ ፤ በሥጋ መከራ የተቀበልከ አንተ ነህ። ከአብ ጋር አንድ እንደ መሆንህ ሞት የሌለብህ አንተ ነህ። ከእኛ ጋር አንድ እንደ መሆንህ በፈቃድህ የሞትክ አንተ ነህ። [ዮሐ.፲፥፲፬–፴]
በመቃብር ያደርህ አንተ ነህ። በኪሩቤል ላይ ያለህ አንተ ነህ። ከሙታን ጋር በመቃብር የነበርክ አንተ ነህ። በአንተ ሕማምና ሞትም ድኅነት ተሰጠ። ከሙታን ጋር የተቈጠርክ አንተ ነህ።
ለሙታንም ትንሣኤን የምትሰጥ አንተ ነህ። ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በመቃብር ያደርክ አንተ ነህ። በዘመኑ ሁሉ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የምትኖር አንተ ነህ። በመለኮት ሕማም ሳይኖርብህ በሥጋ የታመምክ አካላዊ እግዚአብሔር ቃል አንተ ነህ። ❞
[ ቅዱስ ኤራቅሊስ ]
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ❝ በዕፀ መስቀል ላይ የተቸነከርክ አንተ ነህ ❞ ]
🕊
❝ ጌታዬ ፈጣሪዬ አንተ ነህ። ቅድመ ዓለም የነበርክ አንተ ነህ ፤ ዛሬም ያለህ አንተ ነህ። ሰማያዊ አንተ ነህ። ምድራዊም አንተ ነህ። [ዮሐ.፩፥፳፬–፴።
በሰማይ በአብ ህልው የምትሆን አንተ ነህ። ስለእኛ በመስቀል የተሰቀልክ አንተ ነህ። ዓለም ሳይፈጠር ዠምሮ በጌትነት ዙፋንህ ያለህ አንተ ነህ። አሁንም በዕፀ መስቀል ላይ የተቸነከርክ አንተ ነህ።
በመለኮት ሕማም ሞት የሌለብህ አንተ ነህ ፤ በሥጋ መከራ የተቀበልከ አንተ ነህ። ከአብ ጋር አንድ እንደ መሆንህ ሞት የሌለብህ አንተ ነህ። ከእኛ ጋር አንድ እንደ መሆንህ በፈቃድህ የሞትክ አንተ ነህ። [ዮሐ.፲፥፲፬–፴]
በመቃብር ያደርህ አንተ ነህ። በኪሩቤል ላይ ያለህ አንተ ነህ። ከሙታን ጋር በመቃብር የነበርክ አንተ ነህ። በአንተ ሕማምና ሞትም ድኅነት ተሰጠ። ከሙታን ጋር የተቈጠርክ አንተ ነህ።
ለሙታንም ትንሣኤን የምትሰጥ አንተ ነህ። ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በመቃብር ያደርክ አንተ ነህ። በዘመኑ ሁሉ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የምትኖር አንተ ነህ። በመለኮት ሕማም ሳይኖርብህ በሥጋ የታመምክ አካላዊ እግዚአብሔር ቃል አንተ ነህ። ❞
[ ቅዱስ ኤራቅሊስ ]
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
†
💖 [ የትሕርምት ሕይወት ! ] 💖
🕊 💖 🕊
[ “ አገልግሎትን በተመለከተ ! " ]
[ ሥራን አስመልክቶ የሰጠው ትምህርት ! ]
--------------
❝ ወደጄ ሆይ ! በምትሠራው ሥራ ምክንያት አትዘን፡፡
በምትሠራው ሥራ ላይ በፍጹም ስኬታማ ልሆን አልቻልኩም፡፡ እኔ ስንፍናን የተሞላሁ ፣ የደነዘዝሁ ነኝና በፍጹም ይህን ተግባር ልፈጸም አልችልም፡፡ እጆቼ ያለ ፍሬ ከሥራው ብዛት የተነሣ ዝለዋል፡፡ ሥራውን ለመሥራት አሁን አቅሙ የለኝም ስለዚህ ወደመጣሁበት እመለሳለሁ ... የሚል ሐሳብ በአእምሮህ ውስጥ ከቶ አይመላለስ::
እንደ አንድ አማኝ በእግዚአብሔር ታመን ፥ እንዲህ ባለ ነገርም ተስፋ አትቁርጥ፡፡ ነገር ግን ወደ መንግሥቱና ወደ እርሱ ደስታ ስለጠራህ ስለ ጌታችን ስለ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብለህ መከራውን ሁሉ ታግሠህ ኑር፡፡ እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ ፦ “እውነት እላችኋለሁ ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ ፥ ይህን ተራራ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል ፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም፡፡” [ማቴ.፲፯፥፳]
ስለዚህ ተወዳጆች ! ሆይ እምነት ይኑረን ፤ እኛ ተስፋ ያደረግናቸው ከቶ ሊያድኑን የማይችሉ ሰዎችን ሳይሆን እግዚአብሔርን ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ ፦ “በእግዚአብሔር የታመኑ እንደማይታወክ ለዘላለም እንደሚኖር እንደ ጽዮን ተራራ ናቸው::” [መዝ.፻፳፬፥፩] የኃያላን ጌታ ሆይ በአንተ ተስፋ የሚያደርጉ ብፁዓን ናቸው፡፡ ❞
[ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ]
🕊 💖 🕊
💖 [ የትሕርምት ሕይወት ! ] 💖
🕊 💖 🕊
[ “ አገልግሎትን በተመለከተ ! " ]
[ ሥራን አስመልክቶ የሰጠው ትምህርት ! ]
--------------
❝ ወደጄ ሆይ ! በምትሠራው ሥራ ምክንያት አትዘን፡፡
በምትሠራው ሥራ ላይ በፍጹም ስኬታማ ልሆን አልቻልኩም፡፡ እኔ ስንፍናን የተሞላሁ ፣ የደነዘዝሁ ነኝና በፍጹም ይህን ተግባር ልፈጸም አልችልም፡፡ እጆቼ ያለ ፍሬ ከሥራው ብዛት የተነሣ ዝለዋል፡፡ ሥራውን ለመሥራት አሁን አቅሙ የለኝም ስለዚህ ወደመጣሁበት እመለሳለሁ ... የሚል ሐሳብ በአእምሮህ ውስጥ ከቶ አይመላለስ::
እንደ አንድ አማኝ በእግዚአብሔር ታመን ፥ እንዲህ ባለ ነገርም ተስፋ አትቁርጥ፡፡ ነገር ግን ወደ መንግሥቱና ወደ እርሱ ደስታ ስለጠራህ ስለ ጌታችን ስለ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብለህ መከራውን ሁሉ ታግሠህ ኑር፡፡ እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ ፦ “እውነት እላችኋለሁ ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ ፥ ይህን ተራራ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል ፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም፡፡” [ማቴ.፲፯፥፳]
ስለዚህ ተወዳጆች ! ሆይ እምነት ይኑረን ፤ እኛ ተስፋ ያደረግናቸው ከቶ ሊያድኑን የማይችሉ ሰዎችን ሳይሆን እግዚአብሔርን ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ ፦ “በእግዚአብሔር የታመኑ እንደማይታወክ ለዘላለም እንደሚኖር እንደ ጽዮን ተራራ ናቸው::” [መዝ.፻፳፬፥፩] የኃያላን ጌታ ሆይ በአንተ ተስፋ የሚያደርጉ ብፁዓን ናቸው፡፡ ❞
[ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ]
🕊 💖 🕊
†
[ 🕊 በመገዛት አመሰግንሻለሁ 🕊 ]
🌼▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🌼
❝ እመቤቴ ማርያም ሆይ በመገዛት አመሰግንሻለሁ:: በመማጸንም አገንሻለሁ። አንቺ የሊቀ ካህናቱ መሠውያ ሁነሻልና ልጅሽም በእውነት ለሚመገበው የሕይወት ምግብ ነው::
ሕፃንሽ ከልብ ለሚያዳምጠው ምክሩ ጣፋጭ ነው። ቁጣ የሌለብሽ ርኅሩኅ ሆይ ወደ አንቺ እጸልያለሁ ፤ በመማለድም ወደ አንቺ እለምናለሁ:: በኵርሽ /ልጅሽ ክርስቶስ/ አካሔዴን ወደ ጽድቅ መንገድ ያቅና ስምሽን በማስታወስ በጠራሁት ጊዜም በእውነት ይነጋግረኝ።
አንቺም ለዚህ ለአገልጋይ የሚጠቅመውን ስጠው በሥልጣንህ እርዳው ፤ በእጅህም አጽናው ፤ ከሚያስፈራው የሕይወት ጠላቱም መፈራትን አጐናጽፈው በይው:: ለዘለዓለሙ አሜን:: ❞
🕊
[ እንዚራ ስብሐት ]
💖 🕊 💖
[ 🕊 በመገዛት አመሰግንሻለሁ 🕊 ]
🌼▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🌼
❝ እመቤቴ ማርያም ሆይ በመገዛት አመሰግንሻለሁ:: በመማጸንም አገንሻለሁ። አንቺ የሊቀ ካህናቱ መሠውያ ሁነሻልና ልጅሽም በእውነት ለሚመገበው የሕይወት ምግብ ነው::
ሕፃንሽ ከልብ ለሚያዳምጠው ምክሩ ጣፋጭ ነው። ቁጣ የሌለብሽ ርኅሩኅ ሆይ ወደ አንቺ እጸልያለሁ ፤ በመማለድም ወደ አንቺ እለምናለሁ:: በኵርሽ /ልጅሽ ክርስቶስ/ አካሔዴን ወደ ጽድቅ መንገድ ያቅና ስምሽን በማስታወስ በጠራሁት ጊዜም በእውነት ይነጋግረኝ።
አንቺም ለዚህ ለአገልጋይ የሚጠቅመውን ስጠው በሥልጣንህ እርዳው ፤ በእጅህም አጽናው ፤ ከሚያስፈራው የሕይወት ጠላቱም መፈራትን አጐናጽፈው በይው:: ለዘለዓለሙ አሜን:: ❞
🕊
[ እንዚራ ስብሐት ]
💖 🕊 💖
🕊
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
❖ ጥቅምት ፲፩ [ 11 ] ❖
[ ✞ እንኩዋን ለአባ "ያዕቆብ ስዱድ" እና ለእናታችን "ቅድስት ዺላግያ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ ]
† 🕊 አባ ያዕቆብ ስዱድ 🕊 †
"ዻዻስ" ማለት "አባት - መሪ - እረኛ" ማለት ነው:: በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ በሐዲስ ኪዳን የመንፈሳዊ ስልጣን ደረጃዎች በጥቅሉ ፫ [3] ናቸው:: እነሱም ዲቁና: ቅስና: ዽዽስና ሲሆኑ በሥራቸው ወደ ፱ [9] ያህል ክፍሎች አላቸው:: ከእነዚህም ከፍተኛው ስልጣን ዽዽስና ነው::
ዽዽስና ማለት የክርስቶስን መንጋ እንደ ባለቤቱ አድርጐ መጠበቅ ማለት ነው:: ሥልጣኑ በምድር "ሸክም: ዕዳ" ሲሆን በሰማይ ግን "ክብር" ነው:: ማንም በሥጋው ላይ ካልጨከነ በቀር ዽዽስናን አይመኝም::
ቅዱስ ዻውሎስ "ሠናየ ግብረ ፈተወ - ማንም ዽዽስናን ቢመኝ መልካም ሥራን ተመኘ" [፩ጢሞ.፫፥፩] (3:1) ማለቱን ይዞ "ሹሙኝ" ማለት ወደ ማይጠፋ እሳት የሚያስጥል ከባድ ውሳኔ ነው:: ምክንያቱም አንድ ክርስቲያን የሚጠየቅ በራሱ ኃጢአት ሲሆን አንድ ካህን ደግሞ ስለ ልጆቹ ይጠየቃል:: የከፋው ግን የዻዻሱ ነው::
አንድ ዻዻስ ቢጾም ቢጸልይም እንኩዋ ለድኅነቱ በቂ አይደለም:: ምክንያቱም በመንበሩ ላይ ያስቀመጠው መንጋውን እንጂ ራሱን እንዲያድን አይደለምና:: ጌታ እንዳለ መልካም እረኛ "ይሜጡ ነፍሶ ቤዛ አባግኢሁ - መልካሙ እረኛ ስለ በጐቹ ቤዛ ራሱን አሳልፎ የሚሰጥ ነው::" [ዮሐ.፲] (10) ስለዚህም ክህነት [ዽዽስና] ሐዋርያዊ አገልግሎት ከባድም ኃላፊነት ነው::
አባቶቻችን ሐዋርያትና ተከታዮቻቸው ሐዋርያውያን ታላላቅ የዽዽስና መንበሮችን መሥርተው: ትምሕርቱን ከነ ወንበሩ አስተላልፈዋል:: ከእነዚህ መንበረ ዽዽስናዎች ፬ [4] ቱ የበላይ ናቸው::
እነዚህም የቅዱስ ዼጥሮሱ የሮም: የቅዱስ ዮሐንሱ የአንጾኪያ: የቅዱስ ማርቆሱ የእስክንድርያና የቅዱስ ዻውሎሱ የኤፌሶን መናብርት ናቸው::
እነዚህ መንበሮችም ከክርስቶስ ዕርገት እስከ ፬፻፵፫ [443] (451) ዓ/ም: ጉባኤ ኬልቄዶን ድረስ በአንድነት ቆይተው ተለያይተዋል:: ከእነዚህ መናብርት መካከል የእስክንድርያው [የግብጹ] እና የአንጾኪያው [የሶርያው] ዛሬም ድረስ በተዋሕዶ እምነት የጸኑ ናቸው::
የእኛ ቤተ ክርስቲያንም ሐዋርያዊት እንደ መሆኗ ሐዋርያትን መስለው: ሐዋርያትን አህለው የተነሱ አበው ዻዻሳትን በየጊዜው በበዓላት ታስባለች: ታከብራለች::
በተለይ ደግሞ የእስክንድርያና የአንጾኪያ በርካታ አባቶችን እናከብራለን:: እነርሱ ለቀናች ሃይማኖትና ለመንጋው ሲሉ ብዙ መከራን በአኮቴት ተቀብለዋልና:: ከእነዚህም መካከል አንዱ አባ ያዕቆብ ሲባሉ በ፭ [5]ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ የአንጾኪያ መንበር ፓትርያርክ ነበሩ::
ቅዱሱ በገዳማዊ ሕይወት የተመሠከረላቸው: በትምሕርት የበሰሉና ለመንጋው የሚራሩ በመሆናቸው በምዕመናን ይወደዱ ነበር:: ነገር ግን ተረፈ አርዮሳውያንና መለካውያን ከነገሥታቱ ጋር አብረው ብዙ አሰቃዩዋቸው:: በመጨረሻም ከመንበራቸው አፈናቅለው ወደ በርሃ አሳድደዋቸዋል:: ከስደት በሁዋላም አባ ያዕቆብ በዚህች ቀን ዐርፈዋል::
† 🕊 ቅድስት ዺላግያ ገዳማዊት 🕊 †
ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚል እግዚአብሔር የኃጥኡን መመለስ እንጂ ሞቱን አይፈልግም:: በጠፋው በግ መገኘት ደስ ይለዋል:: በእግርህ ሒድ እንኩዋ አይለውም:: ይልቁኑ በትከሻው ተሸክሞ ከጐረቤቶቹ ጋር ደስ ይለዋል እንጂ::
ቤተ ክርስቲያን ካፈራቻቸው ቅዱሳን አንዳንዶቹ ጭንቅ ከሆነ የኃጢአት ሕይወት የተመለሱ ናቸው::
ግን ድንቅ በሆነ ንስሃቸው "ቅዱሳን" ከመባል ደርሰዋል:: ከእነዚህም አንዷ ቅድስት ዺላግያ ናት::
ይህቺ ቅድስት እናት በልጅነቷ በመልኩዋ ምክንያት ስሕተት ያገኛት ናት:: አምላክ የፈጠረውን መልክና ገላ እንዴት መጠቀም እንዳለብን እየተማርን አይደለምና በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረውን ገላችን ለዲያብሎስ ሰጥተነዋል::
ይህቺ እናትም ችግሯ ይኼው ነበር:: ስለ ገጽታዋና ገላዋ የነበራት የተሳሳተ አመለካከት መጀመሪያ ወደ ትውዝፍት [ምንዝር ጌጥ]: ቀጥሎም ወደ ዝሙት ከተታት:: ለዘመናትም የሰይጣን ወጥመድ ሆና ኑራለች::
ፈጣሪ ግን ለሁላችንም የመዳን ቀን ጥሪ አለውና እሷንም ጠራት:: ምናልባትም በዘመኗ የብዙ ሰባክያንን ትምሕርት ሰምታለች:: አንዱም ግን ወደ ልቧ አልገባም::
ምክንያቱም መንፈስ ቅዱስ ያላደረበት አስተማሪ በጥሩ አማርኛ ልባችን ደስ ያሰኝ ይሆናል እንጂ ሊለውጠን አይችልም::
በዘመኑም የሚታየው ትልቁ ችግር ይኼው ይመስለኛል:: እግዚአብሔር የሾማቸው አባቶቻችን ተቀምጠው ወጣቶች መድረኩን የሙጥኝ ብለነዋል::
ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ዺላግያ አንድ ቀን የሰማችው የደጉ ዻዻስ ትምሕርት ግን ፈጽሞ ዘልቆ ተሰማት:: ተጸጸተች: አለቀሰች:: ወደ ዻዻሱ ሔዳ "ማረኝ" አለች: ንስሃ ሰጣት:: እርሷም ንብረቷን ሁሉ መጽውታ በርሃ ገባች::
አንገቷን ደፍታ በጾምና በጸሎት ሰይጣንን ድል ነሳችው:: ከሃገሯ ሶርያ ወደ ቀራንዮ ደርሳ ተመልሳ ለ፴ [30] ዓመታት ዘጋች:: ተባሕትዎዋን ስትፈጽም በጸጋ እግዚአብሔር ተአምራትን ሠርታ: ለኃጥአን መንገድ ጧፍ ሆና አብርታ በዚህች ቀን ዐርፋለች::
አምላከ ቅዱሳን የሚያስተውለውን የንስሃ አእምሮን ያድለን:: ከወዳጆቹ በረከትም አያርቀን::
[ † ጥቅምት ፲፩ [ 11 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ አባ ያዕቆብ [ስደተኛው ሊቀ ዻዻሳት]
፪. ቅድስት ዺላግያ ገዳማዊት
፫. ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
፬. ቅዱስ አርማሚ ሰማዕት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያሬድ ካህን
፪. ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት
፫. ብፁዐን ኢያቄምና ሐና
፬. አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
" መቶ በግ ያለው ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ ዘጠና ዘጠኙን በበርሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሔድ ከእናንተ ማን ነው? ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል:: ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ 'የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ' ይላቸዋል:: እላችሁአለሁ: እንዲሁ ንስሃ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሃ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል:: " [ሉቃ.፲፭፥3-፯] (15:3-7)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
❖ ጥቅምት ፲፩ [ 11 ] ❖
[ ✞ እንኩዋን ለአባ "ያዕቆብ ስዱድ" እና ለእናታችን "ቅድስት ዺላግያ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ ]
† 🕊 አባ ያዕቆብ ስዱድ 🕊 †
"ዻዻስ" ማለት "አባት - መሪ - እረኛ" ማለት ነው:: በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ በሐዲስ ኪዳን የመንፈሳዊ ስልጣን ደረጃዎች በጥቅሉ ፫ [3] ናቸው:: እነሱም ዲቁና: ቅስና: ዽዽስና ሲሆኑ በሥራቸው ወደ ፱ [9] ያህል ክፍሎች አላቸው:: ከእነዚህም ከፍተኛው ስልጣን ዽዽስና ነው::
ዽዽስና ማለት የክርስቶስን መንጋ እንደ ባለቤቱ አድርጐ መጠበቅ ማለት ነው:: ሥልጣኑ በምድር "ሸክም: ዕዳ" ሲሆን በሰማይ ግን "ክብር" ነው:: ማንም በሥጋው ላይ ካልጨከነ በቀር ዽዽስናን አይመኝም::
ቅዱስ ዻውሎስ "ሠናየ ግብረ ፈተወ - ማንም ዽዽስናን ቢመኝ መልካም ሥራን ተመኘ" [፩ጢሞ.፫፥፩] (3:1) ማለቱን ይዞ "ሹሙኝ" ማለት ወደ ማይጠፋ እሳት የሚያስጥል ከባድ ውሳኔ ነው:: ምክንያቱም አንድ ክርስቲያን የሚጠየቅ በራሱ ኃጢአት ሲሆን አንድ ካህን ደግሞ ስለ ልጆቹ ይጠየቃል:: የከፋው ግን የዻዻሱ ነው::
አንድ ዻዻስ ቢጾም ቢጸልይም እንኩዋ ለድኅነቱ በቂ አይደለም:: ምክንያቱም በመንበሩ ላይ ያስቀመጠው መንጋውን እንጂ ራሱን እንዲያድን አይደለምና:: ጌታ እንዳለ መልካም እረኛ "ይሜጡ ነፍሶ ቤዛ አባግኢሁ - መልካሙ እረኛ ስለ በጐቹ ቤዛ ራሱን አሳልፎ የሚሰጥ ነው::" [ዮሐ.፲] (10) ስለዚህም ክህነት [ዽዽስና] ሐዋርያዊ አገልግሎት ከባድም ኃላፊነት ነው::
አባቶቻችን ሐዋርያትና ተከታዮቻቸው ሐዋርያውያን ታላላቅ የዽዽስና መንበሮችን መሥርተው: ትምሕርቱን ከነ ወንበሩ አስተላልፈዋል:: ከእነዚህ መንበረ ዽዽስናዎች ፬ [4] ቱ የበላይ ናቸው::
እነዚህም የቅዱስ ዼጥሮሱ የሮም: የቅዱስ ዮሐንሱ የአንጾኪያ: የቅዱስ ማርቆሱ የእስክንድርያና የቅዱስ ዻውሎሱ የኤፌሶን መናብርት ናቸው::
እነዚህ መንበሮችም ከክርስቶስ ዕርገት እስከ ፬፻፵፫ [443] (451) ዓ/ም: ጉባኤ ኬልቄዶን ድረስ በአንድነት ቆይተው ተለያይተዋል:: ከእነዚህ መናብርት መካከል የእስክንድርያው [የግብጹ] እና የአንጾኪያው [የሶርያው] ዛሬም ድረስ በተዋሕዶ እምነት የጸኑ ናቸው::
የእኛ ቤተ ክርስቲያንም ሐዋርያዊት እንደ መሆኗ ሐዋርያትን መስለው: ሐዋርያትን አህለው የተነሱ አበው ዻዻሳትን በየጊዜው በበዓላት ታስባለች: ታከብራለች::
በተለይ ደግሞ የእስክንድርያና የአንጾኪያ በርካታ አባቶችን እናከብራለን:: እነርሱ ለቀናች ሃይማኖትና ለመንጋው ሲሉ ብዙ መከራን በአኮቴት ተቀብለዋልና:: ከእነዚህም መካከል አንዱ አባ ያዕቆብ ሲባሉ በ፭ [5]ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ የአንጾኪያ መንበር ፓትርያርክ ነበሩ::
ቅዱሱ በገዳማዊ ሕይወት የተመሠከረላቸው: በትምሕርት የበሰሉና ለመንጋው የሚራሩ በመሆናቸው በምዕመናን ይወደዱ ነበር:: ነገር ግን ተረፈ አርዮሳውያንና መለካውያን ከነገሥታቱ ጋር አብረው ብዙ አሰቃዩዋቸው:: በመጨረሻም ከመንበራቸው አፈናቅለው ወደ በርሃ አሳድደዋቸዋል:: ከስደት በሁዋላም አባ ያዕቆብ በዚህች ቀን ዐርፈዋል::
† 🕊 ቅድስት ዺላግያ ገዳማዊት 🕊 †
ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚል እግዚአብሔር የኃጥኡን መመለስ እንጂ ሞቱን አይፈልግም:: በጠፋው በግ መገኘት ደስ ይለዋል:: በእግርህ ሒድ እንኩዋ አይለውም:: ይልቁኑ በትከሻው ተሸክሞ ከጐረቤቶቹ ጋር ደስ ይለዋል እንጂ::
ቤተ ክርስቲያን ካፈራቻቸው ቅዱሳን አንዳንዶቹ ጭንቅ ከሆነ የኃጢአት ሕይወት የተመለሱ ናቸው::
ግን ድንቅ በሆነ ንስሃቸው "ቅዱሳን" ከመባል ደርሰዋል:: ከእነዚህም አንዷ ቅድስት ዺላግያ ናት::
ይህቺ ቅድስት እናት በልጅነቷ በመልኩዋ ምክንያት ስሕተት ያገኛት ናት:: አምላክ የፈጠረውን መልክና ገላ እንዴት መጠቀም እንዳለብን እየተማርን አይደለምና በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረውን ገላችን ለዲያብሎስ ሰጥተነዋል::
ይህቺ እናትም ችግሯ ይኼው ነበር:: ስለ ገጽታዋና ገላዋ የነበራት የተሳሳተ አመለካከት መጀመሪያ ወደ ትውዝፍት [ምንዝር ጌጥ]: ቀጥሎም ወደ ዝሙት ከተታት:: ለዘመናትም የሰይጣን ወጥመድ ሆና ኑራለች::
ፈጣሪ ግን ለሁላችንም የመዳን ቀን ጥሪ አለውና እሷንም ጠራት:: ምናልባትም በዘመኗ የብዙ ሰባክያንን ትምሕርት ሰምታለች:: አንዱም ግን ወደ ልቧ አልገባም::
ምክንያቱም መንፈስ ቅዱስ ያላደረበት አስተማሪ በጥሩ አማርኛ ልባችን ደስ ያሰኝ ይሆናል እንጂ ሊለውጠን አይችልም::
በዘመኑም የሚታየው ትልቁ ችግር ይኼው ይመስለኛል:: እግዚአብሔር የሾማቸው አባቶቻችን ተቀምጠው ወጣቶች መድረኩን የሙጥኝ ብለነዋል::
ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ዺላግያ አንድ ቀን የሰማችው የደጉ ዻዻስ ትምሕርት ግን ፈጽሞ ዘልቆ ተሰማት:: ተጸጸተች: አለቀሰች:: ወደ ዻዻሱ ሔዳ "ማረኝ" አለች: ንስሃ ሰጣት:: እርሷም ንብረቷን ሁሉ መጽውታ በርሃ ገባች::
አንገቷን ደፍታ በጾምና በጸሎት ሰይጣንን ድል ነሳችው:: ከሃገሯ ሶርያ ወደ ቀራንዮ ደርሳ ተመልሳ ለ፴ [30] ዓመታት ዘጋች:: ተባሕትዎዋን ስትፈጽም በጸጋ እግዚአብሔር ተአምራትን ሠርታ: ለኃጥአን መንገድ ጧፍ ሆና አብርታ በዚህች ቀን ዐርፋለች::
አምላከ ቅዱሳን የሚያስተውለውን የንስሃ አእምሮን ያድለን:: ከወዳጆቹ በረከትም አያርቀን::
[ † ጥቅምት ፲፩ [ 11 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ አባ ያዕቆብ [ስደተኛው ሊቀ ዻዻሳት]
፪. ቅድስት ዺላግያ ገዳማዊት
፫. ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
፬. ቅዱስ አርማሚ ሰማዕት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያሬድ ካህን
፪. ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት
፫. ብፁዐን ኢያቄምና ሐና
፬. አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
" መቶ በግ ያለው ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ ዘጠና ዘጠኙን በበርሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሔድ ከእናንተ ማን ነው? ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል:: ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ 'የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ' ይላቸዋል:: እላችሁአለሁ: እንዲሁ ንስሃ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሃ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል:: " [ሉቃ.፲፭፥3-፯] (15:3-7)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖