Telegram Web
አደራ ጠርጥሪኝ

ስምሽን ስሰማ እንባ አይኔን ካሞቀኝ
ስላንቺ ሳወራ ሳግ ደርሶ ካነቀኝ
ፀሀይ ከበረደኝ ሳቅ ከኔ ከራቀ
መከፋት ደስታየን ከእኔ ከሰረቀ

አደራ ጠርጥሪኝ
ናፍቀሽኝ ይሆናል ሰው ልከሽ አስጠሪኝ

በእብዶች መካከል ደህና ከተሰኘሁ
በዝናብ ሲርሱ ደርቄ ከታየሁ
በትልቅ ሰው ለቅሶ ሳቄ ካመለጠኝ
ሀገር ባሳቀ ቀልድ እንባ ካጠመቀኝ

አደራ ጠርጥሪኝ
ናፍቀሽኝ ይሆናል ሰው ልከሽ አስጠሪኝ

ከጨረቃ ጋራ ሳወጋ ካመሸሁ
ከሚያውቁሽ ከሚያውቁኝ ከራሴ ከሸሸሁ
አለም ከደበተኝ ከከረፋኝ ሀገር
በሆነ ባልሆነው ካለኝ ነገር ነገር

አደራ ጠርጥሪኝ
ናፍቀሽኝ ይሆናል ሰው ልከሽ አስጠሪኝ

ይሄው አሁን እንኳ
ስላንቺ እየፃፍኩኝ ላብ ሞልቷል ግንባሬ
ቁጭ ብየ ራሱ ልሩጥ ይላል እግሬ

እኔ እወድሻለሁ ማለቱን ትቻለሁ
በስምሽ መማሉን ረስቼዋለሁ
ለምን ለምን ለምን
ለምን አንቺን ብቻ ለምን ከሰው መርጦ
የሚያርበተብተኝ
የሚያብሰከስከኝ ከሌላው አብልጦ
....ማለቱን ካበዛሁ

አደራ ጠርጥሪኝ
ናፍቀሽኝ ይሆናል ሰው ልከሽ አስጠሪኝ

አወ ናፍቀሽኛል አልክድም ወድቄ
ዝም ብለሽ ነይልኝ አታብዢ ጥያቄ
መልሴ ሁኝኝና
ከወደቅኩበት ጥግ ነይ ፈልገሽ አንሺኝ
መራቅሽ አሞኛል በመቅረብ ፈውሺኝ


አደራ......
https://www.tgoop.com/yebezigetmoch
የግጥም መንደር pinned «አደራ ጠርጥሪኝ ስምሽን ስሰማ እንባ አይኔን ካሞቀኝ ስላንቺ ሳወራ ሳግ ደርሶ ካነቀኝ ፀሀይ ከበረደኝ ሳቅ ከኔ ከራቀ መከፋት ደስታየን ከእኔ ከሰረቀ አደራ ጠርጥሪኝ ናፍቀሽኝ ይሆናል ሰው ልከሽ አስጠሪኝ በእብዶች መካከል ደህና ከተሰኘሁ በዝናብ ሲርሱ ደርቄ ከታየሁ በትልቅ ሰው ለቅሶ ሳቄ ካመለጠኝ ሀገር ባሳቀ ቀልድ እንባ ካጠመቀኝ አደራ ጠርጥሪኝ ናፍቀሽኝ…»
አለሌ ነበርኩ ። ከህንድ እስከ እብድ የቀረኝ የለም የምል አለሌ። የተኛኋቸው ሴቶች ጠቢቡ ሰለሞን ከተኛቸው የሚያንስ አይደለም አልቆጠርኳቸውም እንጂ።

ጀንጅኜ መዳረሻዬ ማራኪ ሆቴል ነው ።ሆቴሏ ሸጎጥ ያለች ሰዋራ ስፍራ ነች ፤ ከመኖርያዬም እሩቅ ነች ።

አስተናጋጆቹም ምቹ ናቸው። በእርግጥ ጉርሻ ምቹ የማያደርገው የለም ። ፈረንጁ እና መስኪ የሚባሉ አስተናጋጆችን የበለጠ አውቃቸዋለሁ ።

ጠብ እርግፍ ብለው ያስተናግዱኛል ፤ በእርግጥ መስኪ የምትባለው ትንሽ ተለቅ ትላለች ።
ፊት ከሰጠሁት ይጎነትለኛል ብላ ይሆን ፣ ተፈጥሮዋ ሆኖ ይሆን ፣ ነፍፍ ቺክ ስለማመላልስ ይሆን ፣ ስለማጨስ ወይም ስለምጠጣ ይሆን እኔ'ንጃ ብቻ
አትስቅልኝም አትኮሳተርብኝም ።

ፊቷ አልሰጥም።።ን ቢሸኝም ውበቷ ግን እንዳለ ነው። መስኪ ምንም ያህል ቲፕ ብሰጣት አመሰጋገኗ ሆነ አስተያየቷ አይለይም ተመሳሳይ ነው ።

ክላሴ ውስጥ አጭሼ ፣ ጠጥቼ ፣ ባልጌ ሹልክ ብለን በጓሮ እንሄዳለን ። በሌላ ቀን ሌላ ቺክ ይዤ እመጣለሁ ፣ ካልጠረረብኝ ቺክ አልገርብም ።

ሁሉንም እንደሙዳቸው እና እንደፍላጎታቸው እሰክሳቸዋለሁ ።
ላጤነቴ በነፃነት ታየው አልታየው ብዬ ሳልሳቀቅ ለመባለግ አግዞኛል።

ጓደኞቼ ሁሉ ሲያገቡ ፤ ቤተሰቦቼ የአታገባም ውትወታ የበረታ ወቅት ሶልያና የምትባል ልጅ ተዋወቅኩ ።

ባገኘኋት በሁለተኛ ቀን ለመቾመስ በት በት አልኩ አልተሳካልኝም ።
በውስጤ ስንቷ እንደ አንቺ አካብዳ ጭኗን ሳትከፍት የቀረች የለችም ብዬ ፈገግ ስል ምነው አለቺኝ

እርጋታሽ ደስ ይላል አልኳት

ውስጤ እንደላዬ የተረጋጋ እንዳይመስልህ አለቺኝ ። ይሆናል ግን ውስጥም ላይም አንድ ላይ ከመንቀዥቀዥ ይሻላል አልኳት ከንፈሯን ገለጥ አድርጋ ሳቅኩኝ አይነት አለቺኝ

በነገራችን ላይ

አንተም ረጋ ያልክ ነክ አለቺኝ... ስስቅ ። ውስጥህ ወዲ ወዲያ ስለሚል ነው እርጋታህ ያልታወቀህ አለችኝ ።

ይሆናል አልኳት

ሶልያና የበዛ እርጋታ አላት ፥ እርጋታዋ ይረብሸኛል ከደስታ ይልቅ ለድብርት አጋልጦ ነው የሚሰጠኝ።

አብሪያት የምሆነው እስከምደክላት ብቻ ነበር።

ትፈልጋለች ብዬ የማስበውን እነግራታለሁ ። ሲኒማ እጋብዛታለሁ ፤ ትያትር ትጋብዘኛለች ከንፈሯ ጋ ሳልደርስ ቀናቶች ነጎዱ

በጭራሽ የወሲብ ወሬ ለማውራት አታመችም ። ወሲብ ነክ ከተወራ ለመቀጠል ፊቷ አይጋብዝም።ወሲብ ነክ ወሬ ካወራሁ ለይሉኝታ እንኳን ፈገግ አትልም።

መንፈሳዊ ጉባኤ ትጋብዘኛለች። ለእሷ ደስ እንዲላት አንዳንድ አሰልቺ ፣ አንዳንድ ማራኪ ስብከቶችን እሰማለሁ ።

ቀልቧን ለመግዛት መንፈሳዊ መፅሃፍ እያነበብኩ ፤ በጉዳዩ ላይ ሰፊ እውቀት አለኝ ወሬ ሳወራት ቀልቧ ሲሳብ ወሬው ሲጥማት አያለው።

ሳይታወቀኝ የኔን መንገድ እየተውኩ በእሷ መንገድ መመላለስ ቀጠልኩ ።

ከሌሎች ስለተለየች ይሆን ፣ እንደምፈልገው
አለመሆኗ ይሆን ፣ የምፈልገውን ስላልሰጠቺኝ ይሆን ብቻ ቀልቤን ገዝታዋለች።

ውሎዋን ስራዬ ብዬ እከታተላለሁ ። ካልተደዋወልን ይታወቀኛል ። እንቅስቃሴዋ እየገቡኝ መጡ ። ሳላገኛት የት እና ምን እያረገች እንደሆነ መገመት ቻልኩ ።

ከደወለችልኝ ስግብግብ ብዬ አነሳለሁ ። በሂደት መንገዷ ምቾት ሰጠኝ ። ከተመላለስኩበት መንገድ በተሻለ ይሄኛው መንገድ ጣፈጠኝ

የድሮ አመሌ ውል ሲለኝ የምቀመጭላቸው ቺኮች ውልብ ብዬባቸው ሲደውሉ ሳላቅማማ የድሮ ስልክ ቁጥሬን ቀየርኩ ።

የትላንት የውድቀት መንገዳችንን ካልቀየርነው ለለውጣችን ሳንካ ይሆናል ።

አሁን ፈልጌ መፅሃፍ ቅዱስ አነባለሁ፤ እፆማለሁ ጉባኤ እከታተላለሁ ።መንፈሳዊ ጉዞ እሄዳለሁ ። ከሶሊያና ጋ እንፋቀራለን። የትላንት መንገዴን አልተረኩላትም ለዛሬው ማንነቴ ግን ማሃንዲሷ እሷው ናት ።

ለአምላኬ ስንቴ በእሷ ምክንያት ምስጋና እንዳቀረብኩለት። የትላንት ህይወቴን እንዴት አሁን እንደማልወደው ። ስለ ሴት አውልነት ሲነሳ ምንም ሃሳብ አልሰጥም ያ ዘመን ያሳፍረኛል።

ሶልያና አንድ እለት ስትፍነቀነቅ መጣች ምነው ስላት እቴቴ ስራ አገኘች አለቺኝ የት ስላት ባንክ

በቀላሉ ፍንክንክ የምትል አይደለችም የእናቷ ጉዳይ ግን ስስ ጎኗ ነው። ብቻዋን ስላሳደገቻት ይሆን ሁሉ ነገሯ ስለሆነች ይሆን ብቻ ስፍስፍ ትልላታለች።

ምን እንደምትሰራ አላውቅም ። በትምህርት ብዙ ያልገፋች ስለሆነች የት እና ምን ትሰራለች ብዬ አልጠየኩም ፤ እሷም ስራ ነች አልመጣችም ፣ ስራ ቀረች ነው እንጂ የት እና ምን እንደምትሰራ ነግራኝ አታውቅም ።

በጥንጡም በግዙፉም ወሬዎቾ መሃል እቴት ሳትል አትውልም ።

የድሮ ስራዋስ ስላት ። ውይ የድሮ ስራዋን እኮ አትወደውም ግድ ሆኖባት እንጂ አለቺኝ።

ስለ እኔ እንደነገራቻት እና እንደወደደቺኝ የነገረቺኝ እለት እንዴት ደስ እንዳለኝ ።

ባሻዬ ብላ ቴክስት አደረገችልኝ ። ደስ ስላት እና ስትቀልድ ባሻዬ ነው የምትለኝ ። ከእቴት ጋ እንደምንመሳሰል ነግሬህ አውቃለሁ ኣ ስትለኝ ሁሌ ብዬ የሳቅ ስቲከር ላኩላት ።

እንደ እሷ ቆንጀ ነኝ ግን ብላ ፎቶዋን ላከችልኝ ።

ማመን አልቻልኩም

ክው

ድርቅ አልኩ

የላከችልኝ ፎቶውን አገላብጬ አየሁት ፤ አልቀየር አለ ። የማራኪ ሆቴል አስተናጋጅ መስኪ የሶሊያና እናት ናት ፤ ሁለት አብረው ሆነው እና አንድ የመስኪን ማራኪ እንግዳ መቀበያ ጋ የተነሳችውን ፎቶ ላከችልኝ ።

ውስጤ ታወከ ።

ያ ሴት አውል አብርሃም ፤ ያ በየጊዜው ለቁጥር ስፍር የሌላቸውን ሴቶችን የሚያጋድመው ፣ የሚያጨሰው አብራሃም ፤ ያ በጥሩ አይን አይታው የማታውቀው አብራሃም ፤ የአንድ ልጇ ሶሊያና እጮኛ ነኝ ብሎ ፊቷ እንዴት ይቆማል??

ትላንቴ ተከተለኝ። እግዜር በተፀፀትንበት ትላንታችን ይቀጣናል እንዴ? ስንቴ ያመሰገንኩበት ጉዳይ መጨረሻው እንዴት እንደዚህ ሆነ ??

የማደርገው ጠፋኝ ። ጠፋሁ ። አንዳንድ ትላንት ትላንት ላይ ብቻ አይቆምም።
© Adhanom Mitiku
ወጣሁኝ ከቤታችን ወደ ተለመደው ቦታችን አብረን ወደታየንበት ሳቅሽ ሳቄ ከሆነበት ሰውን ረስተን በፍቅር የሰከርንበት ህልም ያለምንበት ተኳርፈን ከታረቅንበት ከቦታችን ደረስኩኝ😒ቁጭ አልኩኝ......
ማኩረፊያዬ 💋 ቦታው ልክ እንደ እኛ ተለውጧል እኔ ልሙት! ብታይው ትገረሚያለሽ❤️🤌.....

ቤዛዊት የሴት ልጅ

💬💬💬💬
💬🐷🐷🐷💬
💬 በመጥፋታችን ይቅርታ 💬
💬💬💬💬
😳
🙏
👖
👟👟
Join 👏 👌👌🌹🌹🌹
💔 መቆየት ለፈለገው ልብህን
መሄድ ለፈለገው ደግሞ መንገዱን
ዘርጋለት‥
🌹💋😍
Forwarded from ✥💕⛪
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
@yebezigetmoch 💔
💋🙈🥺

😞 ትዝታዬ😞
Forwarded from ✥💕⛪
የፍቅር ደብዳቤ

👩‍❤️‍💋‍👨.... ፍፁም አይቼ የማላውቀው ዓለም የማላውቀው ስሜት ካንቺ ጋር በመሆኔ የሚሰማኝ ብቻ መንፈሴ ትረካለች ፍፁም ደስተኛ እሆናለሁ.....
@yebezigetmoch
• ጥቂት አዉራ፡፡ ስታወራ ቀስ ብትል መልካም ነዉ

• አንድ ቦታ ላይ ብዙ አትታይ፡፡ ስራህ ላይ አተኩር

• ምርጥ የሰዉነት አቋም ይኑርህ

• ተግባቢና የተረጋጋ ሰዉ ሁን

• ማንም ትክክል ነህ እንዲልህ አትጠብቅ፡፡ ማንም ደጋፊህ እንዲሆን አትጎትጉት

• ስላለህ ነገር ደጋግመህ እየተናገርክ የመጎረር ስሜትን አስወግድ

• ፀዳ በል፡፡ በደንም ልበስ፣ ፏ በል!

• ምርጥ አዳማጭና መፍትሄ አምጪ ሁን

• አደርገዋለሁ ያልከዉን ነገር አድርገዉ

• በጣም ደስ ሲልህ ወይም በጣም ስታዝን ዉሳኔ አትወስን

• ሴቶችን በአስተሳሰባቸዉ መዝናቸዉ

• የግል ጉዳይህን ላገኘኸዉ ሰዉ አትናር

• ሰዉ ስላንተ የፈለገዉን ቢያስብ ከማንነትህ ጋር አታገናኘዉ

• ሃላፊነት መዉሰድን አትፍራ

• ማንንም ለመጉዳት ብለህ ጉድጓድ ከመቆፈርም ይሁን ከማስቆፈር ራስህን አሽሽ

• የጎዱህንና ‘ምንም የለዉም!’ ብለዉ የራቁህን ሰዎች ስኬታማ በመሆን አሳያቸዉ

• ሃሳብህን ለማሳመን የሰዎችን ማንነት አትጉዳ፡፡ ትክክክል ብትሆን እንኳን ካመኑ ይመኑህ ካላመኑህ ጊዜዉ ያሳምናቸዋል

🌹 በቸር ያውላችሁ 🌹

@yebezigetmoch
" የናፈከኝ ለታ"

ብዙ አለም ኣላውቅም
ብዙ አለም ኣልኖርኩም
ጊዜን ካንተ ጋራ
ቁጥር ኣልሰፈርኩም
ግን......የናፈከኝ ለታ
አይንህ ከአይኔ ሲያርፍ
አቅሜን እንዳሳጣኝ
በከንፈርህ መሳም
ልቤ እንደከዳኝ
በእቅፍህ አለም
ሚወስደኝ አታሎ
ደስታ እንደ ሞት ነው ወይ
እራሴን አስጥሎ
እኔ አላውቅም.......
ነብስ ድረስ ሚዘልቅ
ፍቅር ይሰማኛል
የናፈከኝ ለታ
ሰከንድ ያድርብኛል
ትዝታን እየካበ
አንተን አንተን እያለ
እኔን ይንደኛል
ማሰቤስ የታለ
ሸመትከው በፍቅርህ
ሸከፍከው በጀርባ
ልቁረጥ ያሉት ፍቅር
ለምለም ነው ሚረባ
የናፈከኝ ለታ........
አንተ አደርስበት
ጥልቅ ነው ስሜቱ
በሌለህበት
እልፍ ነው ፍሰቱ
ናፍቆትህ ትንግርቱ
.
.
.
💋💋💋🌹🌹🌹❤️❤️❤️🤌🤌🤌
@yebezigetmoch
ፅናት ወዳንቺ የሚወስደኝ ከሆነ እስኪበቃሽ ድረስ ፀንቼ ጠብቅሻለው ።💔😔
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በስህተት የ5ብር ካርድ ወደ ስልኬ ልከው
ማንም ሳይጠይቀኝ ለባለቤቱ መልሻለሁ 😁😋
ህይወት ሁሉ ጊዜ ሁለት አማራጭ አላት አንዱ
ምን አባሽ ብሎ ጥሎሽ ሲሄድ አንዱ ደሞ ምን
አባቴ ልሆንልሽ ምን ጎደለብሽ ብሎ ይመጣል ..
"ደስታ በዙሪያህ የምትጠብቀው ነገር አይደለም,
አንተ ራስህ የምትፈጥረው ነገር ነው."
@yebezigetmoch 😍
join 💗
?❤️‍🩹 መድኃኒት❤️‍🩹🥹

ክፍል ፩

በቤዛዊት የሴት ልጅ

የስልኩ ጩኸት ከእንቅልፌ አባነነኝ ተናደድኩ...... ያቋረጡኝ ምን ከመሰለ ህልም ነበር። የህይወቴ የመጨረሻዋ ስኬቴ ናት አምላኬ እሷን የሰጠኝ ዕለት እውነት በዓለም ላይ ሾሞኛል ማለት ነው። "ባሮክ ባሮክ" ጩኸቷማ እህቴ ነበረች ወደ ቆጡ መውጫ መሰላል ላይ ሆና የምትጠራኝ። "ተነስ ኧረ እንዳትበቅል" አለችኝ። ብበቅል ደስ ባለኝ እሷን እያሰብኩ ጥርሴ ቢረግፍ ጸጉሬ ቢሸብት አልኮነንም ነበር።

እንደ ምንም ተነስቼ ወረድኩኝ። ምሳ ቀርቧል የእህቴ ቆንጆ ሽሮ እንጀራው ላይ ራስ ሆኖ ይታያል ተጣጥቤ ከማዕዱ ተቋድሼ ወደ ጓደኛዬጋር ሄድኩኝ።
ባሮክ እባላለሁ በኤሌክትሪክ ኢንጅነሪንግ ከተመረኩኝ ሁለት ዓመት ሆኖኛል እንደማንኛውም ወጣት የመንግስት ስራ ባይኖርኝም ለራሴ ባመስነፍ ከአንድ ሞል ላይ አንዲት ልጅ ቀጥሬ ቡና ጠጡ እየሰራሁ ነው። አብሮ አደጌም ሳሚም የራሱ የስፖርት ቤት ከፍቶ እየሰራ የሚገኝ የቅባት ልጅ ነው። ከሁለተኛ ክፍል ጀምሮ አብረን ተምረን ያደግን ልጆች ነን። አሁንም ወደ እሱ ነው የምሄደው። ገና ስደርስ ሽሮ በልቶ የሚያድረው ህዝቤ ይሄን ብረት እየገፋ ነበር የተጨማደደ ፊቴን ፈገግ አድርጌ ወደ ሳሚ ቢሮ ገባሁ።
"እ ብሮ ቆየህ እኮ" ገና እንዳየኝ ሳሚ ተናገረ።
"ምን ከመሰለ ህልም ላይ እንደተነሳሁ ብታውቅ እንዲህ ባላልክ" አልኩት ሰላም ብዬው እየተቀመጥኩ።
"ቅዠታም ደግሞ አገረሸብህ" አለኝ ፋይሉን እየከተተ።
"የምሬን ሳም በአሁኑ እኮ ሳገባት ነው ያየኋት" አልኩት ውስጤ ያለውን ደስታ ከፊቴ እያስነበብኩት።
"ቆይ ለምን ሱባኤ አትይዝላትም እንዴ ተቆጣጠረችህ እኮ" አለኝ የባከንኩ የመሰለው አብሮ አደጌ።
"ሳምዬ ብትቆጣጠረኝማ እየበተነ ያለው በረከቴ በሰበሰብኩት የተዘጋው በሬ በተከፈተልኝ እውነት እንዴት ውብ ሆና ስታየኝ እንደነበር በተለይ የምወደው ጥርሷ ብልጭ አድርጋ ስታሳየኝ እኮ....." አቋረጠኝ።
"ተነስ ባክህ እንሂድ" አለኝ። ተናደድኩ ተኮሳትሬ ቀድሜው ወጣሁኝ። መኪና ውስጥ እየሄድን ዝም አልኩኝ ዕቃቃውን እንደተቀማ ህፃን እጄን አጣምሬ በመስኮቱ ወደ ውጪ እያየሁ ነበር እንደማላወራው የተረዳው ሳሚ ሙዚቃውን ከፈተው።

🎧🎧🎧🎧🎧
ኤፍሬም እኔን የጠየቀኝ ይመስል ስለ ውበቷ የዘፈነልኝ የሚመስለኝን የምወደውን ሙዚቃ ነበር
🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶

ዞሬ አየሁት እና ፈገግታዬን ሰጠሁት። "ኧረ ወንድሜ ለአንተ ብዬ ነው አልነገርካት ነገር ልጅቷ በየት ትወቀው ሁሌ እየተያዩ መሳቅ በአይን መሸኛኘት ይጎዳሃል። በህልምህ አትቃዥ ንገራት" አለኝ አፍ ሆኖ የሚነግርልኝ ይመስል። እኔም ሌላ ክርክር ውስጥ ላለመግባት የወሬውን ርዕስ አስቀይሬ ስለ ምንሄድበት ስራ ማውራት ጀመርኩ። ከደቂቃዎች በኋላም የምንገባበት ህንጻ ጋር ደርሰን መኪናውን ፓርክ እያደረግን እኔም ሳሚም የደነገጥነው። ህልሜ ናት......

ክፍል ፪ይቀጥላል

❤️‍🩹🥹መድኃኒት አዲስ ተከታታይ ታሪክ ❤️‍🩹🥹

በማንበብ አስተያየት ስጡ ወዳጆቻችሁን ጋብዙ!
https://www.tgoop.com/yebezigetmoch
መስዋዕት ሁኚ


ሴት አይደለሽ ነይ ወደ ወደፊት
ትማሪ ዘንድ ስለ መስዋዕት
መላሽ ጆሮ አድርገሽ በልብሽ ከትቢ
ለመስዋዕት ተዘጋጅተሽ አበቢ።

ትኩስ ነው ውበት እሳተ ነበልባል
አላፊ አግዳሚ የሚበላ ዳግም የሚያባብል
አይራ'ቅም ከእሳት መድኃኒት ለክረምት
አይተው ደግሞ ተፈርቶ መፈጀት

ይህ ውበት እንዳው ከረገፈ
ከጊዜው ጎዳና ካለፈ
ጸጸት ነው ጸሀይ ስትዘቀዝቅ
ነፍስ ካላገኘች ሃቅ!

የሴትነትሽ ሃቅሽ መስዋዕት መሆን ነው
በአንቺ ነውና አዳም የሚበረታው
ስህተቱ ብትሆኚ ድኅነትም ሆነሻል
የእልፍ ዘመን መከራ በሴት ተፈጽሟል።

ለአዳምሽ ተሸሸጊ ለሁሉ አትታይ
በዘመን አትለኪ በሴት ልኬት ብቻ ታ'ይ
ለመወደድ ውደጂ ልብሽን ገብሪ
በአዳምሽ ጎን ፍቅር ዝሪ
በዕድሜሽ ከውበት በላይ ምግባርን ዘክሪ።

ያከብርሽ ዘንድ የልባምነት ዘውድ እንድትደፊ
የስጋ ሃሳብሽን በነፍስሽ በልጠሽ እለፊ
ጌጥሽ ይሁን ትህትና
እንግዳ ይመላለስ ከእልፍኝሽ ጓዳ።
ፋሲካ ሁኚ ደስታሽን ይትረፍ ለሌላ
ትንሳኤ ሁኚ ለድሃ ከለላ።

ራስሽን ተይ ከመታበይ ውጪ
መስዋዕት ሁኚ ለሴትነትሽ ከስጋ ድካም አምልጪ
ለክብር ልዕልና በራስ ዜግነት በሴትነት ታጪ።

🥰

ሴትነትሽ ከዓለም ለይቶ ይፈትንሻል የማትወጪው የመሰለሽ ነገር ሁሉ የሚታለፍ መሆኑን አስበሽ ከመልክሽ ይልቅ በልቦናሽ ላይ ስሪ። በፈጣሪሽ ቤት የምታበሪው መብራት ምግባር መሆኑን አስበሽ ስጋሽን ሰቅለሽ ለነፍስሽ ድከሚ ለአዳምሽ ታዘዢ ለቤትሽ መልካም ፍሬ ሁኚ ለልጆች እናት ለሰራተኞችሽ ሰብሳቢ ለወዳጆችሽ መጽናኛ ሁኚ።

✍️ ቤዛዊት የሴትልጅ

ሚያዝያ 14/2017 ዓመተ ምህረት
አደራ ጠርጥሪኝ

ስምሽን ስሰማ እንባ አይኔን ካሞቀኝ
ስላንቺ ሳወራ ሳግ ደርሶ ካነቀኝ
ፀሀይ ከበረደኝ ሳቅ ከኔ ከራቀ
መከፋት ደስታየን ከእኔ ከሰረቀ

አደራ ጠርጥሪኝ
ናፍቀሽኝ ይሆናል ሰው ልከሽ አስጠሪኝ

በእብዶች መካከል ደህና ከተሰኘሁ
በዝናብ ሲርሱ ደርቄ ከታየሁ
በትልቅ ሰው ለቅሶ ሳቄ ካመለጠኝ
ሀገር ባሳቀ ቀልድ እንባ ካጠመቀኝ

አደራ ጠርጥሪኝ
ናፍቀሽኝ ይሆናል ሰው ልከሽ አስጠሪኝ

ከጨረቃ ጋራ ሳወጋ ካመሸሁ
ከሚያውቁሽ ከሚያውቁኝ ከራሴ ከሸሸሁ
አለም ከደበተኝ ከከረፋኝ ሀገር
በሆነ ባልሆነው ካለኝ ነገር ነገር

አደራ ጠርጥሪኝ
ናፍቀሽኝ ይሆናል ሰው ልከሽ አስጠሪኝ

ይሄው አሁን እንኳ
ስላንቺ እየፃፍኩኝ ላብ ሞልቷል ግንባሬ
ቁጭ ብየ ራሱ ልሩጥ ይላል እግሬ

እኔ እወድሻለሁ ማለቱን ትቻለሁ
በስምሽ መማሉን ረስቼዋለሁ
ለምን ለምን ለምን
ለምን አንቺን ብቻ ለምን ከሰው መርጦ
የሚያርበተብተኝ
የሚያብሰከስከኝ ከሌላው አብልጦ
....ማለቱን ካበዛሁ

አደራ ጠርጥሪኝ
ናፍቀሽኝ ይሆናል ሰው ልከሽ አስጠሪኝ

አወ ናፍቀሽኛል አልክድም ወድቄ
ዝም ብለሽ ነይልኝ አታብዢ ጥያቄ
መልሴ ሁኝኝና
ከወደቅኩበት ጥግ ነይ ፈልገሽ አንሺኝ
መራቅሽ አሞኛል በመቅረብ ፈውሺኝ


አደራ......
https://www.tgoop.com/yebezigetmoch
.......... ''ኪሎ ስንት ነው?'' እንድታየኝ ነበር የጠየኳት። እሷ ግን ስራዋ ላይ እየተዋከበች ''65'' ብላ ለሚያጣድፋት ደንበኞቿ ትመዝናለች። የትላንት ውበቷ እና መኮሳተሯ ዛሬም ደምቆ ይታያል። አንዴ እንኳን አታየኝም እንዴ እያልኩ ሰርቃ አየችኝ። የምገዛትን መጠኑንን እንደነግራት ይመስላል። ''በቃ ሁሉንም ልውሰድ '' አልኩኝ። ከልቤ! ሁሉም አፈጠጠ የእሷ ደግሞ ግልምጫም አለው። '' ዞር በል በናትህ '' ብላ አመናጭቃ ማስተናገዷን ቀጠለች። የቀሩት አንድ ያረጁ እናት ነበሩና 5ኪሎ እንድትመዝን አድርጌ ቅድሚያ ብሩን ሰጠኋት። ቡናማ ሻሽ ያሰሩት እናትም መረቁኝ ና ተቀብለው ከፊቷ ዘወር አሉ።

እኔ ግን ከመሸጫዋ ቦታ አልተንቀሳቀስኩም። '' ሌላውን ትመዝኚልኝ?'' አልኳት። እኔን አለማወቋ እየደነቀኝ። በምደነግጥለት ግልምጫዋ እምቢታዋን አሳየችኝ። ፈገግ ብዬ '' አላወቅሽኝም?'' መነጽሬን እያወጣሁ ጠየኳት። አየችኝ ውስጥ ድረስ መረመረችኝ። '' ስራ የፈቱትን አላውቅም '' አለች። የተናደውን እየደረደረች። ''የምርሽን ነው ጹጹ'' አልኩ። ጣረ ሞት ከፊቷ የቆመ ይመስል አፈጠጠች። መላ አካሏ ደረቋላ ከግንባሯ ላይ ችፍ ያለው ላብ ድንጋጤዋን አልደበቀም። '' ጹጹ'' ደገምኩላት። ሀሞት የቀመሰች ይመስል ተርገፈገፈች። '' ምን አይነት ቅሌታም እና ደፋር ነህ ከፊቴ የቆምከው'' ብላ ተነሳች።

ያልጠበኩት ነው የተፈጠረው። እታቀፋለሁ ብዬ ልቀጸፍ መሆኑ ቢገባኝ ወደኋላ ፈቅ አልኩ። ''ተረጋጊ እንጂ ጽዮን '' አልኩ በመታወቂያ ስሟ። '' ውረደት ሳላከናንብህ ከዚህ ጥፋ'' አለች። '' ቆ...ይ...እ....'' አላስጨረሰችኝም። ''ዞር በል አንተ ሰውዬ ሬሳህ እንዳይጎተት'' አለች እንደ ነጎድጓድ በሚያስገመግም ድምጿ። ዙሪያዋ ያሉት የሆነው ባይገባቸውም ከተቀመጡበት ተነስተዋል። አንድ ወጣት ጎረቤቷ ከሱቁ ዘሎ ወጥቶ ወደ እኔ መጣ። እጄን እየጎተተ መንገዱን እየመራኝ '' ይቅርብህ ከጹጹ ጋር ሙግት። ከተነሳባት ለእኛም ይተርፋልና ፍንጣሪው ሌላ ቀን ተመለስ። '' አለኝ። ዞር ብዬ ሳያት ወደ ስራዋ ተመልሳለች። የትላንት እልኋ ዛሬም ነበልባል ነው። ወጣቱ ትንሽ ሸኝቶኝ አሰናበተኝ። እኔም ያቆምኩትን መኪናዬን አስነስቼ ወደ ቤቴ መንገድ ጀመረኩ።

ጽዮን እልኸኛ ጽዮን ጣይቱ ዛሬም በኑሮ ስብራትም አልደቀቀችም። እንደትላንት በሚያውቋት ፊት ክቡር ናት። እሳተ ነበልባሏ ያስፈራል። ዘንድሮም ትፈጃለች። በመስኮቴ የሚገባው ንፋስ ትላንትን እየጎተት ያሳየኛል። ሰው እንዴት እንዲህ ይኖራል ከዕድሜ ብዛት አይበርድም አይደክምም። ጽዮን ያው ጽዮን ናት። መልኬን መርሳቷስ የዚህን ያህል ምን ጋር ተቀይሬ ትላንት የምትወደው የታመነችለት ፍስሃ ነኝ። እንዴት ረሳችኝ። እሳቷ ራሷን ፈጃት እንዴ። ...............ነገ አገኛታለሁ።


✍️ርዕስ የለውም❤️‍🩹
🥀🌿🌱ክፍል 1🍁🍁🍁🍁

🖋️የቤዛዊት ሃሳብ

@yebezigetmoch
#story #time
2025/06/25 17:42:37
Back to Top
HTML Embed Code: