Telegram Web
አይ እናት ለናት ዋጋ አነሣት

ልጇን መኪና ገጭቶባት ሁለት ቀን ካጠገቧ አልሄድም ብላ ...😭💔🙏
4
የአንድ ሀገር ውበቷ ስርዓቷ ነው። ገነትም ብትሆን ስርዓት ከሌላት ሲኦል ትናፍቀኛለች።

ሁላችሁም ከዚህ ከሃይማኖት መስኮት አሻግራችሁ ተመልከቱ። እኚህ አባት የስጋ አባቴ ቢሆን ብላችሁ አስቡት። መንገድ ላይ እንደዚህ እየሰበክን ነው ብሎ መታገል ምን አይነት መንገድ ነው።

የሀዋሳን ከተማ ጎዳናዎች ሰው በመንገድ የሚያሸማቅ ጎዳና ሆና ዛሬ ላይ በሚዲያ ውላለች። ነገ ደግሞ የቱሪስት መዲና ናት ለማለት አይከብድም?
"የ500 ቢሊየን ዶላር የተጣራ ገንዘብ ማለት በባንክ አካውንቴ 500 ቢሊየን ዶላር አለኝ ማለት አይደለም። በዚህ ሰዓት እንኳን እስከ አንድ ሚሊዮን ዶላር ጥሬ ገንዘብ የለኝም።"

"ሰዎች ስለ ሀብታሞች በተለይም ስለ ቢሊየነሮች ያላቸውን አመለካከትን ስመለከት ያናድደኛል።

ሰዎች በሀብታሞች ስኬት በጣም ስጋት ስለሚሰማቸውና ስኬቱ እነሱ ሃብታም እንዳይሆኑ እንደ ምክንያት አድርገው መቁጠር ይቀናቸዋል።

ብዙ ሰዎች የሀብት ጽንሰ-ሀሳብ ገና አልተረዱም። ይህ ሀብት ምንድን ነው? ከ500 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ አለኝ ነገር ግን 500 ቢሊየን ዶላር በባንክ አካውንቴ የጥሬ ገንዘብ ሂሳብ እንዳለኝ ያለኝ ያህል አይደለም።

በእኔ የባንክ አካውንት ያለው ቀሪ ሂሳብ በጣም በጣም ዝቅተኛ ነው። አሁን በባንክ አካውንቴ እስከ አንድ ሚሊየን ዶላር እንኳን የለኝም። የገንዘቤ ክምችት በሙሉ አክሲዮን ላይ ነው ያለው፤ አክሲዮን ስሸጥ ተጨማሪ አክሲዮን ላይ ኢንቨስት አደርጋለሁ።

ሀብቴ የእኔ ኩባንያ ነው። ቴስላ ወይም ስፔስ-ኤክስ ከሰሩ ማለት እኔም ወዲያውኑ እከስራለሁ። ነገር ግን አሁንም ደግሜ በእነዚህ የተጣራ ሃብት ብድር ወስጄ ኢንቨስት አደርጋለሁ ምክንያቱም እኔ ጥሬ ገንዘብ የለኝም።"

ኢሎን ማስክ
አድሱ ሀገር አቀፍ የተሽከርካሪ ተርጋ ...🙆‍♂
👍2👎1
ህይወት እንዲህ ናት እንግዲህ!

እሱ እንደሚለው ከሆነ ዋቢሸበሌ አካባቢ መኪና በማጠብ ነው የሚተዳደረው። የቀዳማዊ የሃይለ ሥላሴ የልጅ ልጅ ነኝ ብሏል።

ዘመዶቹን ማግኘት ይፈልጋል አገናኙት እስቲ ...😎
Dendesho...😎
"የሰዉነት ክፍሉን ፎቶ እያነሳ ይልክልኝ ነበር"

የቪኒሺየስ ጁኒየር ፍቅረኛ የነበረቺዉ ብራዚላዊቷ ሞዴል አና ሲልቫ ከቪኒሺየስ ጁኒር ጋር በነበረችበት ጊዜ ተጫዋቹን ባህሪ ተናግራለች።

ሞዴሏ"ቪኒሺየስ ጁኒየር ስለ ወ*ሲ%ብ* ብቻ ነዉ ሚያስበዉ፤እኔ ከሰዎች ጋር መነጋገር እወዳለሁ ነገር ግን ስለ ባለጌ ነገሮች ማዉራት አልፈልግም። ቪኒሺየስ ግን መነጋገር አይወድም እሱ ሁሌም ንግግሩ ስለ ወ§ ሲ*%ብ እና ስለ ወ%ሲ×ብ ብቻ ነዉ" ስትል ተናግራለች።

በተጨማሪም ሞዴሏ" የሰዉነት ክፍሉን(እርቃኑን) ፎቶ ይልክልኛ፤የኔንም እንድልክለት ይጠይቀኛል" ስትል ገልፃለች።

ተጫዋቹ በዚህ ጉዳይ በኢንስታግራም ገፁ ድሪጊቱን መፈፀሙን አምኖ ይቅርታ ጠይቋል።
1
በተለያየ የሀገሪቱ ቦታዎች (በተለይ በአዲስ አበባ) ጥብስ መጠኗ ቀንሶ ዋጋዋ ግን ጨምሯል። ምንድነው ምክንያቱ?
የዱር እንስሳት ፎቶግራፈር ከዛፍ ስር ከተኛበት ከእንቅልፉ ሲነሳ ከጎኑ እጁን ተንተርሳ ተኝታ ያገኛት ቺታ ግርምትን ፈጥሯል።

የዱር እንስሳት ፎቶግራፍ አንሺና የሥነ ሕይወት ተመራማሪ የሆኑት ዱልፍ ቮልከር በደቡብ አፍሪካ በሚገኝ አንድ የጥበቃ ማዕከል ውስጥ እጅግ ያልተለመደና አስደናቂ ተሞክሮ አጋጥሟቸዋል። ቮልከር ከዛፍ ሥር በእንቅልፍ ላይ እያሉ ሲነቁ፣ ኤደን የምትባል ቺታ አጠገባቸው ተጠግታ በሰላም ተኝታ አገኙ።

ቮልከር ይህንን ጊዜ በካሜራው መዝግቦት የነበረ ሲሆን፣ ባልተጠበቀው እንግዳ መገኘት በፍርሃት ፋንታ መተማመን እና ንጹሕ ፍቅር ተሰምቷቸዋል። ለወራት ያህል በቺታ ኤክስፒሪያንስ ማዕከል በበጎ ፈቃደኝነት ሲሠሩ የቆዩት ቮልከር፣ ከቺታዎች ጋር ትዕግሥትንና አክብሮትን መሠረት ያደረገ ጠንካራ ግንኙነት መሥርተዋል። የኤደን ረጋ ያለ ንክኪና ሰላማዊ መገኘት ጥቃትን ሳይሆን ጥልቅ ፍቅርን የሚያሳይ ነበር ተብሏል።

ቮልከር ውሻውን በሞት ካጡ በኋላ፣ ህይወታቸውን ለአደጋ የተጋለጡ የዱር እንስሳትን በተለይም ቺታዎችን ለመጠበቅ አሳልፈዋል። ቺታዎች ደግነታቸውና የማወቅ ጉጉታቸው ከሚታወቁ አዳኝ እንስሳት መካከል ተጠቃሽ ናቸው።

የቮልከርና የኤደን ታሪክ በዓለም ዙሪያ ተሰራጭቶ ከቫይራል ምስልነት ያለፈ ትርጉም አግኝቷል። ይህ ያልተለመደ ግንኙነት የዱር ፍጥረታት በሰው ልጆች ላይ እምነት ሊጥሉ፣ መውደድና በሰላም መኖር እንደሚችሉ የሚያሳይ ኃይለኛ ማሳሰቢያ ሆኗል።
የምድር #ባቡር ተሽከርካሪዎችን እና የኮንስትራክሽን መሳሪያዎችን ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ እያጓጓዘ ነው - ከ1940-ዎቹ አጋማሽ እስከ 1950-ዎቹ መጀመሪያ እንደተነሱ የሚገመቱ ፎቶግራፎች

#Flatbed #Freight #Wagons of the Franco Ethiopian #Railway Corporation bringing motor vehicles and construction equipment from the port of Djibouti to Ethiopia possibly in the 1950s/1960s. Source does not tell us the specific year/s
የሀገር ባለውለታ ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ)
ፍትህ ይፈልጋል!

ለፌዴራል እና ለአዲስ አበባ ፖሊስ የተላለፈ አሳሳቢ ጥያቄ

ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛና የኢትዮጵያ ስፖርት ሕያው ቤተ-መጻሕፍት የነበረው ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) አሟሟት ዙሪያ ተገቢው ምርመራ እንዲደረግለት ጥሪ ቀረበ።

📌 የጥያቄው ዋና ነጥብ:

የሀገር ባለውለታ፣
የብዙዎችን ትውልድ ስፖርት ያስተማረውና ስለ እግር ኳስ እድገት ያልደከመው ገነነ መኩሪያ፣ በእርግጥ ራሱን አጥፍቷል በሚል የመጀመሪያ መረጃ ዙሪያ ጥርጣሬዎች መኖራቸውን ምንጮች ይጠቁማሉ።

* የመጀመሪያ ምርመራ ማስረጃ:
በጉዳዩ ላይ የመጀመሪያ ምርመራ ያደረጉ ግለሰቦች እንዳሉት፣ የተገኘው ማስረጃ ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ ራሱን አጥፍቶ ሞቷል የሚያስብል አለመሆኑን ያሳያል።

* የህዝብ ጥያቄ:
የገነነን ጽሑፍ ያላነበበ የስፖርት አፍቃሪ በሀገሪቱ የለም። ለኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረገ ግለሰብ ትክክለኛ ፍትህ ሊያገኝ ይገባል።

🚔 ለፖሊስ የቀረበው ልባዊ ልመና:

ለፌዴራል ፖሊስ እና ለአዲስ አበባ ፖሊስ በጋራ ይህንን ጉዳይ ከስር ከመሰረቱ እንደ አዲስ እንዲይዙት እና እስከ መጨረሻው አጣርተው፣ ትክክለኛውን የሞት ምክንያት አውጥተው፣ ለኢትዮጵያ ህዝብና ቤተሰቡ ፍትህ እንዲሰጡ በትህትና እንጠይቃለን።

ገነነ መኩሪያ በህይወት እያለ ሀገሩ ባትሸልመውም፣ ቢያንስ ከሞት በኋላ ፍትህን መንፈግ የለባትም።

ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ፍትህ ይገባዋል!
2025/10/11 15:47:54
Back to Top
HTML Embed Code: