Forwarded from ሔኖክ ጥበብ👌 Henok Design👗
👏ጥሩውን ለናተ 👌ሔኖክ ጥበብ
የሃገር ባህል ልብስ ለመግዛት አስበዋል🤔
እንግዲያውስ አይጨነቁ telegram ቻናላችንን ጆይን በማድረግ የፈለጉትን የባህል ልብስ ይምረጡ
ከሃገር ውጭ ያላቹ ደንበኞቻችን
በ DHL, እና POSTA በኩል አድርገን እንልክልዎታለን
አድራሻችን: ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ሽሮ ሜዳ
🔘0913612714
0939165393
👉https://www.tgoop.com/Hfekrawi16
👉inbox @Heni_tebeb
የሃገር ባህል ልብስ ለመግዛት አስበዋል🤔
እንግዲያውስ አይጨነቁ telegram ቻናላችንን ጆይን በማድረግ የፈለጉትን የባህል ልብስ ይምረጡ
ከሃገር ውጭ ያላቹ ደንበኞቻችን
በ DHL, እና POSTA በኩል አድርገን እንልክልዎታለን
አድራሻችን: ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ሽሮ ሜዳ
🔘0913612714
0939165393
👉https://www.tgoop.com/Hfekrawi16
👉inbox @Heni_tebeb
Forwarded from ቁምነገር
ህይወትህ ያንተ ነው!
ለትውስታ፦ አውቀህ ፈልገህ እራስህን እየፈተንከው ነውን? ሁን ብለህ እራስህን ጫና ውስጥ ከተሃልን? ወደህ ወዳጆችህን ለይተሃልን? ፈቅደህ እራስህን የለውጥ ሂደት፣ የእድገት ጉዞ ውስጥ ከተሃልን? ውሃ ያጠጣሀው ተክል መሬት ይይዛል፣ ያድጋል፣ ፍሬም ያፈራል። የሰራህበት ማንነት፣ ለአዲስ ክስተት ያጋለጥከው፣ የፈተንከውና ለከባድ ሁነት ያጋለጥከው አንተነትህም የተሻለ ሰው ሆኖ ታገኘዋለህ፣ ጠንካራና ብርቱ ሰው ሆኖ ታገኘዋለህ። በህይወትህ እጅግ ወሳኝ የሆነውን ጉዳይ ውሃ አጠጣው፣ አጥብቀህ ስራበት፣ ዋጋ ክፈልበት፣ የሚገባውን ትኩረት ስጠው። ህይወትን እየቀለድክ አታሸንፈውም፤ ህይወትን ችላ እያልክ፣ ትኩረት እየነፈከው አታሻሽለውም። የህይወት ፈተናህ ሲያንስ፣ ጭንቀት ሲርቅህ፣ ከጫናዎች ውጪ ስትሆን በእርግጥ እያደክ እንዳልሆነ አስተውል።
አዎ! ጀግናዬ..! ህይወትህ ያንተ ነው አትቀልድበት፤ የግል ጉዳይ የእራስህ ነው፤ የሚመጣብህ እያንዳንዱ ፈተና ያንተን ጥንካሬ ይጠይቃል፤ ያንተን ብርታት ይፈልጋል። እላይ ታች፣ ወዲህ ወዲያ ማለትን በምትፈልግ አለም ውስጥ እየኖርክ ቁብነገር በሆነው ህይወትህ ብትቀልድ በተራው ህይወት በእራሱ ሲቀልድብህ መመልከትህ አይቀርልህም። አሁን አሁን ብዙዎቻችን ፋታ አጥተናል፣ ማረፍ አቅቶናል፣ ነገሮችን መረዳትና ማስተዋል ከብዶናል፣ ለማን ትኩረት መስጠት እንዳለብን፣ ምንንስ ማስቀደም እንደሚገባን ዘንግተናል። እዚም እዛም ጫወታ ያታልለናል፣ ቀልድ ማየቱ፣ ሌሎች በህይወታችን ሲያፌዙ አብሮ መሳቅን መርጠናል። በዚህ መንገድ ግን እራሳችንን ልናሸንፍ አንችልም። አንዳንዴም ቢሆን ለእራሳችን ብለን ቆምጠጥ ማለት ይኖርብናል። እየቀለድክ የምታድግበት የስራ ዘርፍ የለም፤ እያሾፍክ የሚለውጥህ ተግባርም አይኖርም።
አዎ! ቀልድም ይሁን ቁብነገር ያማረ ፍሬን ሊያፈራ የሚችለው ስራዬ ብለህ ወገብህን ታጥቀህ ስትይዘው ብቻ ነው። አንዳንዱ አንተን አይቶ፣ ሁኔታህን አንብቦ የስራህን ጥራት ያውቀዋል፤ አንዳንዱ ከጅማሬህ ተነስቶ የት እንደምትደርስ ይገነዘባል፣ ሌላው ደግሞ ተግባርህን ብቻ ተመልክቶ ለምን እንዳደረከው ይረዳል። ዘመንህን ሁሉ እየቀለድክ ብትኖር የቀልድህን ክፍያ በአመሻሹ የህይወትህ ክፍል ታገኘዋለህ፤ ዕድሜህን በሙሉ ወሬ በማመላለስና የሰዎችን ስራ በማደማመቅ ብቻ ብታሳልፍ የወጣችልህ ጀምበር በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደምትጠልቅብህ አትጠራጠር። ህይወት በጫወታ ቢቻ የሚመራ፣ በቁብነገር ብቻም የታጠረ ጉዞ አይደለም። ሁለቱንም በማጣጣም ጎን ለጎን ማስኬድ የግድ ነው፤ ከሁሉም ከሁሉም ግን ቁብነገር በሆነው የህይወታችን ክፍል ላይ ማሾፍና መቀለድ የከፋ ዋጋ እንደሚያስከፍለን መረዳት ተገቢ ነው።
═════════❁✿❁ ═════════
ለንጋታችን
@btina21
@enkopaweyan
@enkopaweyan
ለትውስታ፦ አውቀህ ፈልገህ እራስህን እየፈተንከው ነውን? ሁን ብለህ እራስህን ጫና ውስጥ ከተሃልን? ወደህ ወዳጆችህን ለይተሃልን? ፈቅደህ እራስህን የለውጥ ሂደት፣ የእድገት ጉዞ ውስጥ ከተሃልን? ውሃ ያጠጣሀው ተክል መሬት ይይዛል፣ ያድጋል፣ ፍሬም ያፈራል። የሰራህበት ማንነት፣ ለአዲስ ክስተት ያጋለጥከው፣ የፈተንከውና ለከባድ ሁነት ያጋለጥከው አንተነትህም የተሻለ ሰው ሆኖ ታገኘዋለህ፣ ጠንካራና ብርቱ ሰው ሆኖ ታገኘዋለህ። በህይወትህ እጅግ ወሳኝ የሆነውን ጉዳይ ውሃ አጠጣው፣ አጥብቀህ ስራበት፣ ዋጋ ክፈልበት፣ የሚገባውን ትኩረት ስጠው። ህይወትን እየቀለድክ አታሸንፈውም፤ ህይወትን ችላ እያልክ፣ ትኩረት እየነፈከው አታሻሽለውም። የህይወት ፈተናህ ሲያንስ፣ ጭንቀት ሲርቅህ፣ ከጫናዎች ውጪ ስትሆን በእርግጥ እያደክ እንዳልሆነ አስተውል።
አዎ! ጀግናዬ..! ህይወትህ ያንተ ነው አትቀልድበት፤ የግል ጉዳይ የእራስህ ነው፤ የሚመጣብህ እያንዳንዱ ፈተና ያንተን ጥንካሬ ይጠይቃል፤ ያንተን ብርታት ይፈልጋል። እላይ ታች፣ ወዲህ ወዲያ ማለትን በምትፈልግ አለም ውስጥ እየኖርክ ቁብነገር በሆነው ህይወትህ ብትቀልድ በተራው ህይወት በእራሱ ሲቀልድብህ መመልከትህ አይቀርልህም። አሁን አሁን ብዙዎቻችን ፋታ አጥተናል፣ ማረፍ አቅቶናል፣ ነገሮችን መረዳትና ማስተዋል ከብዶናል፣ ለማን ትኩረት መስጠት እንዳለብን፣ ምንንስ ማስቀደም እንደሚገባን ዘንግተናል። እዚም እዛም ጫወታ ያታልለናል፣ ቀልድ ማየቱ፣ ሌሎች በህይወታችን ሲያፌዙ አብሮ መሳቅን መርጠናል። በዚህ መንገድ ግን እራሳችንን ልናሸንፍ አንችልም። አንዳንዴም ቢሆን ለእራሳችን ብለን ቆምጠጥ ማለት ይኖርብናል። እየቀለድክ የምታድግበት የስራ ዘርፍ የለም፤ እያሾፍክ የሚለውጥህ ተግባርም አይኖርም።
አዎ! ቀልድም ይሁን ቁብነገር ያማረ ፍሬን ሊያፈራ የሚችለው ስራዬ ብለህ ወገብህን ታጥቀህ ስትይዘው ብቻ ነው። አንዳንዱ አንተን አይቶ፣ ሁኔታህን አንብቦ የስራህን ጥራት ያውቀዋል፤ አንዳንዱ ከጅማሬህ ተነስቶ የት እንደምትደርስ ይገነዘባል፣ ሌላው ደግሞ ተግባርህን ብቻ ተመልክቶ ለምን እንዳደረከው ይረዳል። ዘመንህን ሁሉ እየቀለድክ ብትኖር የቀልድህን ክፍያ በአመሻሹ የህይወትህ ክፍል ታገኘዋለህ፤ ዕድሜህን በሙሉ ወሬ በማመላለስና የሰዎችን ስራ በማደማመቅ ብቻ ብታሳልፍ የወጣችልህ ጀምበር በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደምትጠልቅብህ አትጠራጠር። ህይወት በጫወታ ቢቻ የሚመራ፣ በቁብነገር ብቻም የታጠረ ጉዞ አይደለም። ሁለቱንም በማጣጣም ጎን ለጎን ማስኬድ የግድ ነው፤ ከሁሉም ከሁሉም ግን ቁብነገር በሆነው የህይወታችን ክፍል ላይ ማሾፍና መቀለድ የከፋ ዋጋ እንደሚያስከፍለን መረዳት ተገቢ ነው።
═════════❁✿❁ ═════════
ለንጋታችን
@btina21
@enkopaweyan
@enkopaweyan